23/09/2023
Contact with inbox or call 0991712716
Ethiopian Media Service (EMS) is publicly funded satellite television station broadcasting 24 hours Sales At Ayat Real Estate
Contact with inbox or call 0991712716
ዘመናዊ ከተማ በሽያጭ ላይ!
3000 ሱቆች በአንድ ጣራ ስር
ለገበያ በማያስቡበት ሲኤምሲ
ለንግድዎ የበለጠ ስኬት
ከኪራይ ይልቅ የራስዎትን ሱቅ መግዛት
ለበለጠ መረጃ:
☎️ 0991712716
የሽያጭ ቢሮዎቻችን ፡
ቦሌ መድሃኔአለም አውሎ ቢዝነስ ሴንተር
ይጎብኙን!
አያት ዞሮ መግቢያዬ!
Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipisicing elit, sed do eiusmod tempor incididunt ut labore et dolore magna aliqua. Ut enim ad minim veniam, quis nostrud exercitation ullamco laboris nisi ut aliquip ex ea commodo consequat. Duis aute irure dolor in reprehenderit in voluptate velit esse cill...
Ayat Real Estate
Contact :- 0991712716
Ayat Real Estate Sales
Contact Mobile No:- 0991712716
ኢትዮጵያ ቡና ከ ባህርዳር ከነማ Live / Ethiopian coffee vs Bahirdar kenema Live
ኢትዮጵያ ቡና ከ ባህርዳር ከነማ Live / Ethiopian coffee vs Bahirdar kenema Livepage :- https://www.facebook.com/zembabatube
የ ኮንዶሚኒየም ዕጣ ውጤት በቀላሉ በስልካችን ለማየት 2015 / How to see the condominium result of 2015_Ethiopia
የ ኮንዶሚኒየም ዕጣ ውጤት በቀላሉ በስልካችን ለማየት 2015 / How to see the condominium result of 2015_Ethiopiapage :- https://www.facebook.com/zembabatube
በቤትሰራተኛ የተሰረቀው ህፃን እዉነታውን ተናገረpage :- https://www.facebook.com/zembabatube
በቤትሰራተኛ የተሰረቀው ህፃን እዉነታውን ተናገረpage :- https://www.facebook.com/zembabatube
ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና Zehabesha Daily News september 8 - 2022
ዘ-ሀበሻ ኦርጂናል ተመልሷል ሰብስክራይብ (Subscrib) እያደረጋችሁ 2022 | Ethiopia Ze-Habesha
አረጋኸኝ ወራሽ አስገራሚ ፐርፎርማንስ በሚኒሶታ ፌስቲቫል
አረጋኸኝ ወራሽ አስገራሚ ፐርፎርማንስ በሚኒሶታ ፌስቲቫል 2022
ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና Zehabesha Daily News september 6 - 2022page :- https://www.facebook.com/zembabatube
የነዋይ ደበበ ልደት( Surprise) በዘ-ሐበሻ ቤት ሲከበር | Neway Debebe Birthday surprise 2022 Zehabeshapage :- https://www.facebook.com/zembabatube
የጀዋር መሐመድ መልዕክት ስለኬንያ ምርጫ!..
በኬንያ ኘረዝደንታዊ ምርጫ በፍርድ ቤት እልባት ማግኘቱን ተከትሎ ጀዋር መሐመድ በሶሻል ሚድያ ገፁ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያስተላለፈው መልዕክት (ትርጉም በድሬቲዩብ)
***
ዊልያም ሩቶ የኬንያ 5ኛ ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጣቸው እንኳን ደስ አላችሁ። በአገርዎ ዴሞክራሲን ከማጠናከር በተጨማሪ የእርስ በርስ ጦርነትን ለማስቆም፣ የኢትዮጵያን ሰላም ለመመለስ እና በክልላችን መረጋጋት እንዲሰፍን ፕሬዝዳንት ኬንያታ የጀመሩትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተስፋ እናደርጋለን።
ሚስተር ራይላ ኦዲንጋ፣ ለኬንያ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የማይተካ ሚና ተጫውተዋል። ለአስርት አመታት ያንተ አስደናቂ ፅናት እና ለምርጫው ሂደት ቁርጠኝነት ለኬንያውያን ዴሞክራሲያዊ ፖለቲካን ለማጠናከር አስችሏል። ከእርስዎ ብዙ የምንማረው ነገር አለ።
የምርጫ አካሉ የምርጫውን ሂደት እና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ድህረ ምርጫን ክርክር ሲዳኝ ያለው አካሄድ የማይታመን ነው። የሁለቱ አካላት ሙያዊ ብቃት፣ ገለልተኝነት እና ቅልጥፍና አሁንም ሰላማዊ፣ ተአማኒ እና ፍትሃዊ የምርጫ ሂደትን ለማስፈን ለሚታገሉ ሀገራት አርአያ የሚሆን ነው።
ኬንያውያን እንኳን ደስ አላችሁ። ከረዥም ውጣ ውረድ በኋላ ወደ ምርጫ ዴሞክራሲ ደርሳችኋል። ይህን እንደ ቀላል አትውሰዱት!.. ጠብቁት፣ አጠናክሩት!
Ethiopia: ዘ-ሐበሻ 3 የአሁን መረጃዎች | Zehabesha |page :-https://www.facebook.com/zembabatube
ዘ-ሐበሻ የዕለቱ ዜና Zehabesha Daily News september 2 - 2022
Ethiopia: ዘ-ሐበሻ 3 የአሁን መረጃዎች | Zehabesha 3 Mereja |
Zehabesha Original Intro - ዘ-ሐበሻ ኦሪጂናል መግቢያ
subscribe the new YouTube account
Zehabesha Original Intro - ዘ-ሐበሻ ኦሪጂናል መግቢያ
ሰበር ዜና!
*********
መቀሌ የሚገኘው የትግራይ ቴሌቭዥን ማሰራጫ ጣቢያ በአየር ጥቃት ወ*ደመ።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዛሬ ረፋድ ላይ በሰነዘረው ወታደራዊ ጥቃት መቀሌ ከተማ የሚገኘውን የሀሰት ፕሮፓጋንዳና የጦርነት ምታ ነጋሪት መጎሰሚያ የትግራይ ቴሌቭዥን ማሰራጫ ጣቢያን ማ*ውደሙን አስታወቀ።
ዶ/ር ደብረፂዮን ለላኩት ደብዳቤ ጠቅላይ ሚንስትሩ ምላሽ ሰጡ 2022
የአፈ ጉባዔው እና የ ዶ/ር ደሳለኝ ፍጥጫ
የ5ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ የቅድመ ገበያ የሙከራ አገልግሎት በአዲስአበባ በስድስት ጣቢያዎች ተጀመረ
"እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!"
ኢትዮ ቴሌኮም የመጨረሻውን የኔትዎርክ ትውልድ 5ጂን የቅድመ-ገበያ የሙከራ አገልግሎት የአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ ከግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በስድስት ጣቢያዎች ማስጀመሩን በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካኼደ መርሐግብር ይፋ አደረገ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ የቴክኖሎጅው መጀመር በማስመልከት ለደንበኞቻቸው እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ ያለን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።
እጅግ ፈጣን፣ አስተማማኝ፣ ዳታ የማስተላለፍ መዘግየትን (Ultra low latency) እጅግ በላቀ ሁኔታ የሚቀንስ፣ በርካታ ዲቫይሶችን በአንድ ጊዜ በማገናኘት ለአይ.ኦ.ቲ (Internet of Things) አጋዥ የሆነውን እና ለማምረቻ ፋብሪካዎች፣ ግብርና፣ ህክምና፣ ለመሳሰሉ ኢንዱስትሪዎች እጅግ የላቀ ፋይዳ ያለውን እንዲሁም አሽከርካሪ-አልባ ተሽከርካሪዎች (self-driving vehicles) የመሳሰሉ ቴክኖሎጂዎችን እውን የሚያደርገውን፣ በውስን ሃገራት ብቻ የተሞከረውን የ5ጂ አገልግሎት ተግባረዊ በማድረጉ ኢትዮ ቴሌኮም ኩራት እንደሚሰማው ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ የኩባንያው ዋና ሥራአስፈፃሚ ለመገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል።
የ5 ጂ አገልግሎት በተለይም ወሳኝ ተልዕኮ ላላቸው እና በተመሳሳይ ወቅት ሥራቸውን ማከናወን ለሚፈልጉ አገልግሎቶች ለአብነት ያህል የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች፣ ግብርና፣ ሕክምና ለመሳሰሉ ዘርፎች እጅግ የላቀ ፋይዳ እንዳለው ዋናሥራ አስፈፃሚዋ አስረድተዋል።
ኢትዮቴሌኮም የ5 ጂ ኔትወርክ ቅድመ ገበያ የሙከራ አገልግሎት በአዲስአበባ ከተማ ያስጀመረ ሲሆን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እስከ 150 የ5 ጂ ጣቢያዎችን በመትከል በክልል ከተሞች ጭምር ማስፋፊያ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
በ5 ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር በተበሰረበት መርሐግብር ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የኩባንያው የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተገኝተዋል።
ሰሜን ኮሪያ የባለስቲክ ሚሳኤል አስወነጨፈች
ሰሜን ኮሪያ የባለስቲክ ሚሳኤል ወደ ምስራቃዊ የባህር ዳርቻ ማስወንጨፏ ተሰማ፡፡
የአሁኑ የሚሳኤል ሙከራ የሃገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን የሃገራቸውን የኒውክሌር የጦር መሳሪያ አቅም በማሳደግ በጠላቶቻችን ላይ እንጠቀማለን ካሉ ከቀናት በኋላ የተደረገ ነው።
የደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ አዛዦች በሰጡት መግለጫ ሚሳኤሉ ከሰሜን ኮርያ ዋና ከተማ ምስራቃዊ የባህር ዳርቻ መተኮሱን አረጋግጠዋል።
በመግለጫቸው ተጨማሪ የሚሳኤል ሙከራዎች መኖሩን እየተከታተልን ነው ማለታቸውን ቲ አር ቲ ዘግቧል።
ሰሜን ኮሪያ በዚህ አመት እያደረገች ያለው ያልተለመደ እና ተደጋጋሚ የጦር መሳሪያ ሙከራ የኒውክሌር መሳሪያ አቅሟን ለማዘመን እና በኒውክሌር ድርድሩ በዋሺንግተን ላይ ጫና ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ይነገራል።
ከ446 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ማቆማቸው ተረጋገጠ
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በክልሎች ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅንቄ ከ446 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ማቆማቸውን መለየት መቻሉን ገለጸ፡፡
በክልሎች ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ሚያዝያ 29 እንደሚካሄድ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በሰጡት መግለጫ የንቅንቄው ዋነኛ ዓላማ አምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ ያሉ ችግሮችን ለመለየት፣ ሥራ ያቆሙ ኢንዱስትሪዎችን ለመለየትና ወደ ሥራ ለመመለስና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ ነው ብለዋል።
ከዚህ አንፃር በክልሎች ደረጃ ሲካሄድ የቆየው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ችግሮችን ከመለየት አንፃር ውጤት እንደተገኘበትም ጠቅሰዋል። በንቅንቄው ከ446 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ማቆማቸውን መለየት ተችሏልም ብለዋል።
ሚኒስትሩ የግብዓት፣ የፋይናንስ፣ የመሰረተ ልማት፣ ብቁ የሰው ኃይል እጥረትና የተቀናጀ የመንግሥት ድጋፍ አለመኖር ምርታማነትን ላይ እክል እንደፈጠረ የገለጹ ሲሆን 50 በመቶ የሆነውን የእምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ማሻሻል ሌላው አላማ ነው ብለዋል።
እነዚህን ችግሮች ለመፍታትም ንቅናቄው የአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን የረጅም ዓመታት ንቅናቄ በመሆኑ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል ብለዋል።
በንቅናቄው የውይይት መድረክ፣ ኤግዝቢሽንና አርአያ የሚሆኑ አምራች ኢንዱስትሪዎችን እውቅና የመስጠትና ሌሎችም መርኃ ግብሮች ይኖሩታል ተብሏል።(ኢሚ)
በአዲስአበባ በተከበረው በኢድአልፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ አካባቢ የአድማ ብተና የጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ፍርድ ቤት ቀረበ።
የፌደራል ፖሊስ አድማ ብተና ዘርፍ አባል የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ከትናንት በስቲያ ሰኞ በአ/አ በተከበረው የኢድአልፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ የሰማዓታት መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ ከፈነዳው የአድማ በታጭ የጭስ ቦንብ ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውሎ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ዛሬ ረፋድ ላይ ቀርቧል።
መርማሪ ፖሊስ ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በኢዳል አፍጥር በዓል ዕለት በተመደበበት ወንጀል የመከላከል ምደባ ላይ እያለ የታጠቀውን አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ በአግባቡ መታጠቅ ሲገባው በአግባቡ ባለመታጠቅ የጭስ ቦንቡ እንዲፈነዳና ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርጓል ያለው መርማሪ በዚህ በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ የመንግስትና የግለሰብ ንብረት ጉዳት መድረሱንም አብራርቷል።
በተጠረጠረበት ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ወንጀል ለተጨማሪ ማስረጃ አሰባስቦ ለመቅረብ 14 ቀን እንዲሰጠው መርማሪው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
ተጠርጣሪው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በበኩሉ በዕለቱ አስቀድሞ በተመደበበት ቦታ ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ እንደነበር እና በሰዓቱ በቦታው ላይ የነበሩ ሰዎች ቁጥር መጨመርና መጨናነቁን ተከትሎ ከታጠቀው ሶስት አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ ውስጥ አንደኛው በማያውቀው ሁኔታ መሬት ላይ ወድቆበት በድንገት መፈንዳቱን ገልጿል።
ሆኖም ምንም አይነት ተንኮልም ሆነ ክፋት በውስጤ አልነበረም ወድቆ ሲፈነዳ እኔ እራሴ ደንግጬ ነበር ሲል እያለቀሰ ሁኔታውን ለችሎቱ አስረድቷል።
በተጨማሪም ተጠርጣሪው ወላጆቹን በሞት ማጣቱን ገልጾ እህትና ወንድሙን በሱ እርዳታ እያስተማራቸው እንደሆነ እና ከለሊት 7:00 ጀምሮ ለጥበቃ ስራ ከመሰማራቴ ውጪ ሌላ ክፋት በውስጤ የለም ሲል ለችሎቱ አብራርቷል።
ጉዳዩን የተከታለው ፍርድ ቤቱ ለተጨማሪ ምርመራ ለፖሊስ 14 ቀን ፈቅዷል።
ለግንቦት 10 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።
Via Tarik Adugna
ems ህወሓት ከአፋር አካባቢ ለቅቄ ወጥቻለሁ ማለቱን ተከትሎ የመንግስት ምላሽ April 2022የEMS ቋሚ ወርሃዊ ክፍያ አባል በመሆን ይመዝገቡ! በ https://www.payal.com/dnate/?host
EMS Eletawi Apr 2022 Part 2የEMS ቋሚ ወርሃዊ ክፍያ አባል በመሆን ይመዝገቡ! በ https://www.papal.com/doate/?host
EMS Eletawi Apr 2022 Part 2የEMS ቋሚ ወርሃዊ ክፍያ አባል በመሆን ይመዝገቡ! በ https://www.paypl.com/donate/?host
የራይድ ታክሲ አገልግሎት ታሪፍ በመንግሥት የማይተመን ከሆነ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ አይሆኑም
• ድጎማው ሲነሳ ነዳጅ በሊትር ከ60 ብር ሊያልፍ ይችላል ተብሏል፣
በተለምዶ ራይድ ወይም የሳሎን ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች የሚያስከፍሉት ታሪፍ በመንግሥት የማይወሰን ከሆነ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ እንደማይሆኑ ተጠቆመ።
ለሕዝብ ፋይዳ ካላቸው የትራንስፖርት ሰጪዎች በስተቀር፣ ለሁሉም ተሽከርካሪዎች የሚነሳው የነዳጅ ድጎማ ከሁለት ወራት ተኩል በኋላ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፣ ከዚያም የነዳጅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያው የሚተመን ይሆናል።
የታለመ የነዳጅ ዋጋ ድጎማ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፣ በተመረጡ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የሚውል፣ በጊዜ የተገደበ ድጋፍ እንደሆነ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው የውሳኔ ሐሳብ ያሳያል።
የአዲሱን አሠራር ሒደት የሚተነትነው የውሳኔ ሐሳብ የማዘጋጀት ሒደቱ ላይ የተሳተፉና ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ ኃላፊ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የነዳጅ ድጎማው በተመረጡ ተሽከርካሪዎች ላይ መተግበር ያስፈለገው የመንግሥት ወጪ ለመቀነስና አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ለመርዳት እንደሆነ ተናግረዋል።
የሥራ ኃላፊው ለሪፖርተር እንደተናገሩት ከመንግሥት ሥምሪት ውጭ የሆኑ ታሪፋቸውም በገበያ የሚመራ ተሽከርካሪዎች የድጎማው አካል የማይሆኑ ሲሆን፣ ይህም ምንም እንኳን መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ላይ መጠነኛ ጫና ያሳድራል የሚል ፍራቻ ቢጭርም አስፈላጊ ውሳኔ መሆኑን አክለዋል።
ሪፖርተር ከውሳኔ ሐሳብ መረዳት እንደቻለው ድጎማው ሲነሳ የዓለም ነዳጅ ውጤቶች ገበያ ሁኔታን ያገናዘበ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ የሚደረግ ሲሆን፣ ይህም ከአምስት ዓመታት ላልበለጠ ጊዜ ተግባራዊ ይደረጋል።
በውሳኔው መሠረት በመንግሥት ቁጥጥር ሥር በሚሆን ታሪፍና ሥምሪት ለመሥራት ከተስማሙ የትራንስፖርት ሰጪዎች በተጨማሪ፣ በማኅበር ታቅፈው የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎቶች የሚሰጡ አሽከርካሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ።
የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች፣ ኮድ 1 እና 3 ሚኒባሶች፣ የከተማ አውቶብሶች፣ አገር አቋራጭ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎችና የመጫን አቅማቸው እስከ 47 የሆኑ የሕዝብ ትራንስፖርት ሰጪዎች የድጎማው ተጠቃሚ ይሆናሉ።
የሳሎን ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች መካከል የሆነው የዛይ ራይድ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ታደሰ፣ ድጎማው መሰል አገልግሎት ሰጪዎችን ባለማካተቱ ቅር እንደተሰኙ የተናገሩ ሲሆን፣ የትራንስፖርት እጥረትን ሊያባብስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
አቶ ሀብታሙ እንደተናገሩት የትራንስፖርት እጥረት ሳይቀረፍ የራይድ ታክሲ አገልግሎት ከድጎማው ተጠቃሚ እንዳይሆን ማድረግ ያለውን ችግር ከማባባስ ባሻገር በዚህ አገልግሎት ሰጪዎች የሚሰበሰበውን የታክስ መጠን ሊቀንሰው እንደሚችልና የዘርፉን ዕድገት ሊያቀጭጨው እንደሚችል ሥጋታቸውን ለሪፖርተር አጋርተዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት ከ40 በላይ የሳሎን ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ገበያውን የተቀላቀሉ ሲሆን፣ ከ30 ሺሕ በላይ ተሽከርካሪዎች በሥራቸው አቅፈዋል ተብሎ ይገመታል። በአሁን ወቅት በአማካይ አሥር ብር በኪሎ ሜትር ያስከፍላሉ።
ድጎማው ሲነሳ አንድ ሊትር ነዳጅ አሁን ባለው ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ መሠረት ከ60 ብር በላይ የሚደርስበት ዕድል ሰፊ በመሆኑ የታሪፍ ማስተካከያ ማድረጋቸው የማይቀር መሆኑን የሚያነሱት አቶ ሀብታሙ ይህም ወደ ሌሎች ዘርፍ ሊዛመት ስለሚችል ዋጋ ግሽበትን ሊያባብስ ይችላል ብለዋል።
በተመሳሳይ የራይድ ታክሲ ባለቤት የሆኑት አቶ ተመስገን አራጌ የተባሉ ግለሰብ በበኩላቸው መንግሥት ድጎማውን ካነሳ በዘርፉ የተሰማሩ አሽከርካሪዎች ከገበያ ሊወጡ የሚችሉበት ዕድል ሰፊ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፣ መንግሥት ውሳኔውን በድጋሚ ሊያጤነው እንደሚገባ ተናግረዋል።
ምንጭ፡- ሪፖርተር
EMS Mereja April 2022የEMS ቋሚ ወርሃዊ ክፍያ አባል በመሆን ይመዝገቡ! በ https://www.paypl.com/donte/?hoste
EMS Eletawi Apr 2022የEMS ቋሚ ወርሃዊ ክፍያ አባል በመሆን ይመዝገቡ! በ https://www.paypl.com/donte/?hoste
# በአዲስ አበባ ት/ቤቶች ኦሮምኛን በግዳጅ የሥራ ቋንቋ ለማድረግ የተጀመረው እንቅስቃሴ ግጭት እየፈጠረ ነው!
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ መንግሥታዊ ትምህርት ቤቶች ከመምህራን፣ ከተማሪዎች እና ከወላጆች ፈቃድ ውጭ በግዳጅ የኦሮምኛ ቋንቋን የማስተማሪያና የሥራ ቋንቋ ለማድረግ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ግጭቶች እየፈጠሩ ናቸው።
ግጭቱ በተለይም በአዲስ አበባ ዳርቻ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ቀደም ብሎ የተጀመረና እየተባባሰ የመጣ ሲሆን፣ በቅርቡ ደግሞ ወደ መሀል አዲስ አበባ ትምህርት ቤቶችም ተስፋፍቷል።
እንደ ምንጮች ገለፃ፣ የግጭቱ ምንጭ የኦሮሚያ ክልል ሰንደቅ ዓላማን በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሰቅለው በማውለበለባቸው እና በሌሎች ትምህርት ቤቶች ደግም ለመስቀል ሙከራ በማድረጋቸው ነው። ከኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ መዝሙር ውጭ የአዲስ አበባ ተማሪዎችም ሆኑ መምህራን የማያውቁትን መዝሙር በኦሮምኛ የሚዘመረው እና ለመዘመር የሚደረገው ሙከራም ተቃውሞ እየገጠመው ነው። እንደሚታወቀው፣ የኦሮሚያ ክልል ሰንደቅ ዓላማም ሆነ የክልሉ መዝሙር በብዙሃኑ የኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም።ከኢትዮጰያ ውጭ ባለው የኦሮሞ ዳያስፖራ ዘንድ የክልሉ ሰንደቅ ዓላማ እንደ ክህደት አርማ ስለሚታይ ፈፅሞ አይለወለብም፣ የክልሉ መዝሙርም ጨርሶ አይታወቅም።
እውነታው ይህ ሆኖ እያለ፣ በእነ ወ/ሮ አዳነች እና ሽመልስ አብዲሳ ቅንጅት የተጀመረውንና ብዙሃኑን ኦሮሞ የማይወክለውን እንቅስቃሴ ለማሳለጥ ያመች ዘንድ፣ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ከሚገኙ የኦሮሞ መስተዳድር ከተሞች ተማሪዎችን በግዳጅ እና በጥቅማ ጥቅም በመደለል ወደ አዲስ አበባ ማምጣት ተጀምሯል።
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ
ትምህርት ሚኒስቴር የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ አድርጓል።
የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ምደባ ተደርጓል።
ከዚህ በፊት በተገለጸዉ የመቁረጫ ነጥብ እና ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋርና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ የሚያስገኝላቸው ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡
በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተመደቡበትን ዩኒቨርስቲ ለማየት በድህረገፅ፡-https://result.ethernet.edu.et ፣ በSMS፡- 9444 እንዲሁም በቴሌግራም፡- መጠቀም ይችላሉ።
ተማሪዎች ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችው ማንኛውም ጥያቄ በድህረገፅ https://complaint.ethernet.edu.et በማመልከት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ሚያዝያ 24/2014 ዓ.ም ድረስ ተገቢዉን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሃ ግብር የሚያሳዉቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ጥሪ ያቀርባል፡፡(ትምህርት ሚ/ር)
EMS በኢኤምኤስ ዕለታዊ ዝግጅት ላይ ከአቶ ጀማል የከሚሴ ዞን የኮሚንኬሽን ሀላፊ ጋር የተደረገ ቆይታ Apr 2022
EMS Mengedachin ሰሞነኛ ጉዳዮች Apr 2022የEMS ቋሚ ወርሃዊ ክፍያ አባል በመሆን ይመዝገቡ! በ https://www.paypl.com/donte/?hoste
Be the first to know and let us send you an email when Ayat Real Estate - Betoche posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.
Want your business to be the top-listed Media Company?