Ethiopian Muslim Voice

  • Home
  • Ethiopian Muslim Voice

Ethiopian Muslim Voice Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Muslim Voice, Publisher, .

❝...ጎንደርን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ከቱርክ ሀገር በግማሽ ቢሊዬን ብር የተገዛ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያ አምጥተው ይዘንባቸዋል...❞ ይህንን የተናገሩት የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ስራ ...
05/05/2022

❝...ጎንደርን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ከቱርክ ሀገር በግማሽ ቢሊዬን ብር የተገዛ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያ አምጥተው ይዘንባቸዋል...❞ ይህንን የተናገሩት የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ናቸው። ኧረ ስለ ኒኪሉየር መስሪያው ዩራኒየምም ሳይቀር አብረው አውርተዋል..?!.
የኒኩሊየር ጦር መሳርያ ያላቸው አካላት በጣም ጥቂት ሀያላን የሚባሉ ሀገራት ናቸው። እሳቸው የጠቀሷት ቱርክ እራሱ መሳርያው የላትም..! መሳርያውም እንደ ተራ AK47 በወደብ አምጥተህ የምትገጣጥመው አይደለም። ይህ ሰውየ እንዲህ አይነት ቅጥፈትን ያለምንም ማስረጃ በአደባባይ ሲናገር ስሰማው እጅግ በጣም ነው የተገረምኩት። ለዚህ የቅጥፈት ንግግሩ የክልሉ መጅሊስ መረጃው ደርሶት ከሆነ ክስ ከፍቶ ህግ ፊት ሊገትረው ይገባል። እንዲህ አይነት የወረደ እብለት በአደባባይ የሚናገር ከሆነ ሀይማኖቱን ለምዕመኑ እንዴት አድርጎ ነበር የሚያስተምረው? የሚለው ግን ያስገርማልም፥ ያስደነግጣልም..!

ጎንደር ዛሬ ሚያዚያ 27----------------------መከላከያም ሆነ ፌደራል በከተማው ቢኖርም ሙስሊሞችን በየመንገዱ መደብደብ እና ማስፈራራቱ እንደቀጠለ ነው::ዛሬም ነጋዴዎችን ሱቅ ካል...
05/05/2022

ጎንደር ዛሬ ሚያዚያ 27
----------------------
መከላከያም ሆነ ፌደራል በከተማው ቢኖርም ሙስሊሞችን በየመንገዱ መደብደብ እና ማስፈራራቱ እንደቀጠለ ነው::

ዛሬም ነጋዴዎችን ሱቅ ካልከፈታችሁ ዛቻ ቀጥሎ ውሎ ንግድ ፈቃድ መንጠቅ 50,000 ብር ቅጣት እና ሱቅ ማሸጉን አጠናክረው ውለዋል::

አሸባሪው ቡድን በጭፍን እየተጓዘ በጥፋት ላይ ጥፋት በወንጀል ላይ ወንጀል እየደራረበ ይገኛል::

የሚገርመው ሱቅ ካልከፈታችሁ እያለ የሚያስፈራራው አሸባሪ ቡድን ዛሬ ካላንደር የሚዘጋበት ቀን መሆኑን እንኳ ማስተዋል አልቻለም::

ረፋድ ላይ የታሽጓል ወረቀት የለጠፉባቸውን ሱቆች አሁን ደሞ ልጥፉን በማንሳት ስራ ላይ ተጠምደዋል::

ፍትህ ለጎንደር ሙስሊሞች
ዛውያ ቲቪ
ተግባራዊ ዳእዋ

ፎቶ የቀበሌ 6 መስጅድ ጉዳት

05/05/2022

በየአድባራቱ የሚካሄደው መሠል የጥላቻ ንግግር ከዚህ በላይ ደም ላለማፋሰሱ ምንድን ነው ዋስትናችን?"

አሸባሪው ጋዜጠኛአብዛኛው ጋዜጠኞች በዚህ ስራ ላይ አንሳተፍም  በማለት ከደሙ ነፃ  ሲሆኑ  ይህ ብስራት መለሰ የተባለ  ቱሪ ናፋ ቦርባሬ ጋጠወጥ  ትርካውን ለኔ ተውት በማለት   በሙሉ ፍላጎ...
04/05/2022

አሸባሪው ጋዜጠኛ

አብዛኛው ጋዜጠኞች በዚህ ስራ ላይ አንሳተፍም በማለት ከደሙ ነፃ ሲሆኑ ይህ ብስራት መለሰ የተባለ ቱሪ ናፋ ቦርባሬ ጋጠወጥ ትርካውን ለኔ ተውት በማለት በሙሉ ፍላጎቱ እንደተሳተፈ አንድ ቀድሞ ፋና ውስጥ ሲሰራ የነበረ አሁን ሌላ ቲቪ ላይ የሚሰራ ጋዜጠኛ ሚስጥር አውጥቷል አብዛሀኛው ጋዜጠኞች በድርጊቱ መበሳጨታቸውንም አጋልጧል ዶክመንተሪው ሲቀናበርም ንትርክ እንደነበረም አክሎ ገልፇል
ጋዜጠኞቹም በቦታው ላይ ሳይኬድ የተለያዩ የህብረተሰብ አካላትን ቃለ_ መጠይቅ ሳይካተትበት እንደት ከሶሻል ሚዲያ ላይ ድምፆችንና ምስሎችን ሰብስቦ ዶክመንተሪ ሊሆን ይችላል? በዚህ ሰዓትስ ከጥቅሙ ጉዳቱ አያመዝንም ወይ? በህወሓት ጊዜስ እንደዚህ አይነት ዶክመንተሪዎች ምን ለውጥ አስገኝተው ነበር? መስጂድ የተቃጠለው ጎንደርና ደባርቅ ሰው የሞተውም እዛው የወራቤው ብቻስ አልገዘፈም ወይ?
የሚሉና ተያዥነት ያለው ጥያቄዎች ቢሰነዝሩም ኢትዮጲያ ፕሬስ ድርጂት ውስጥ በተሰገሰጉ ፅንፈኞች ገፋፊነት ፊልሙ አየር ላይ እንድውል ተደርጓል
✔ውስጥ አዋቂያችን እናመሰግናለን

በደሴ የተያዘው የጎንደር አሸባሪ🙈ትውልዱ ጎንደር የሆነው የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ትናንት በደሴ ከተማ የኢድ ሶላት ላይ ሁከት ሊፈጥር በገባበት በቁጥጥር ስር ውሏል!!ይህ ከታች በምስሉ ላይ የ...
03/05/2022

በደሴ የተያዘው የጎንደር አሸባሪ🙈

ትውልዱ ጎንደር የሆነው የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ትናንት በደሴ ከተማ የኢድ ሶላት ላይ ሁከት ሊፈጥር በገባበት በቁጥጥር ስር ውሏል!!

ይህ ከታች በምስሉ ላይ የምታዩት ወጣት ትናንት በደሴ ከተማ ቦሩ ሜዳ የኢድ ሶላት በሚሰግዱ ሙስሊሞች ላይ እረብሻ ለመፍጠር እንደገባ ተይዟል። ወጣቱ ትውልዱ ጎንደር ሲሆን የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነው። ወጣቱ ሲያዝ ብዙ ሆነው እንደተሰማሩም ተናግሯል ተባለ!!

ወሎ ሙስሊም-Wollo Muslims

02/05/2022

ዘመድኩን በቀለ ሙስሊሞች ጫማቸውን ጥለው ፈረጠጡ ሲል እርሱ ጀርመን ድረስ ፈርጥጦ የጠፋው የባየር ሙኒክን ጨዋታ ለመመልከት ነው የሚመስለው።

ልብ በሉና እነዚህን ከታች የተያያዙ ምሰወሎችንና መልዕክቶችን ተያያዥነትና የተጀራጀ በሚመስል መልክ ሴራ፣ ተቀናጅቶ መረጃ ለማጥፋትና ለመቅጠፍና መረጃ ለመጣፋት የተሰራ ቀሽም ድራማ።1: አዲስ...
02/05/2022

ልብ በሉና እነዚህን ከታች የተያያዙ ምሰወሎችንና መልዕክቶችን ተያያዥነትና የተጀራጀ በሚመስል መልክ ሴራ፣ ተቀናጅቶ መረጃ ለማጥፋትና ለመቅጠፍና መረጃ ለመጣፋት የተሰራ ቀሽም ድራማ።

1: አዲስ አባባ ባልደራስ አክራሪዎች ሰሩት ብሎ ለመወንጀል ከክስተቱ መፈጠር በሃላ ሰዓታት አልፈጀበትም
2: የአዲስ አበባ ፖሊስ ሀላፊነት በጎደለዉ መልኩ አንዳንድ ግለሰቦች በፈጠሩት ንብረት ጠፋ ብሉ ወነጀለ (የፀጥታ አካል መረጃ ሳያጣራ እንደአክቲፊስት አክት ማድረግ)
3: የአዲስ አበባ ከንቲባ ፅ/ቤት የአአ ፖሊስ መልዕክት እንዳለ ለጠፈ

4: አስለቃሽ ቦንቡን የተኮሰዉ የፌደራል ፖሊስ ባልደረባ በምስልና በተንቀሳቃሽ ምስል ከተያዘ በሇላና መረጃዉ ከተሰራጨ አምባርቆብኝ ነዉ አለ። እዚህ ላይ በተንቀሳቃሽ ምስለየ እንደሚታየዉ አንዲት ሴት ለፖሊሱ ጠጋ ብላ መልዕ ነገር ስትነግረዉ ይታያል። መረጃዎች እነደሚያሳዩት ወዳዉ እንደተኮሰዉ ነዉ።

ኡስታዝ Ahmedin Jebel ን   ለምን ይፈሩታል⁉ 🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀ብዙ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች የኡስታዝ አህመዲን ጀበል ስም ባልዋለበት፣ ምንም ነገር ባልተናገረበት የሱን ስም ሲያጠፉ ...
01/05/2022

ኡስታዝ Ahmedin Jebel ን ለምን ይፈሩታል⁉
🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀🎀

ብዙ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች የኡስታዝ አህመዲን ጀበል ስም ባልዋለበት፣ ምንም ነገር ባልተናገረበት የሱን ስም ሲያጠፉ በሀሰት ሲከሱት ይታያል፤ በቃ በኢስላም ላይ የደረሰ ጥቃትን የሚያወግዝ ሰልፉ ቤርሙዳ ቢደረግ ያንን ሰልፍ የጠራው ያቀነባበረውና ያሴረው አህመዲን ጀበል ነው፣ የሚል ትንታኔ የሚሰሩ ዩቱበሮች ፅንፈኛና ወገንተኛ የፖለቲካ ኤሊቶች ማዓት ናቸው። ግን ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን በዚህን ያክል ለምን ይፈሩታል⁉

ሌላው ደግሞ መሃል ሰፋሪ ነኝ ገለልተኛ ነኝ የሚል ቆዳ ቅብ ኡስታዝ አህመዲንን ከነ ምህረተአብ፣ ከነዲያቆን አባይነህ፣ ከነ ዲያቆን ሃብታሙ አያሌው ጋር ሲያወግዝና ሲያማ ታየዋለህ፤ ያው አላማው ባላንስ ሰርቷል ተብሎ ትንሽ ተቀባይነትን ለማግኜት ነው። ባሻዪ ምኝ ነህ ልበል፣ እስኪ ቢያንስ የዚህ ወር ወይም የፈለግከውን ዓመት ያክል የነዚህን ሰዎች ኦፊሻል የፌስቡክ ገፅ ዘወር ዘወር ብለህ ተመልከት፣ በኡስታዝ አህመዲን ጀበል ገፅ ሃይማኖታዊ ምክሮች፣ ግልፅ የሆኑ አንድን ግለሰብ ወይም ቡድን ወይም ብሔር አልያም ታርጌትድ ያደረገ እምነትን የኮነነበት ያጥላላበት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችን በሌላው ላይ እንዲነሳ የቀሰቀሰበት፣ ጥላቻ የሰበከበት አንዲት ሪከርድ አልያም Screen shoot ማምጣት ከቻልክ እኔ አህመዲንን አብሬህ አወግዛለሁ። በተቃራኒው በዚህ አንድ ወር ውስጥ አልያም ወደኋላ ሳብ ብለህ የመምህር ምህረተአብን አልያም የዲያቆን አባይነህ ካሴን፣ አልያም የመምህር ምህረአብን፣ አልያም የዲያቆን ሃብታሙ አያሌውን የፌስቡክ ገፅ በቅንነትና በጨዋነት ብትመለከተው መዓት የጥላቻ ንግግሮችን፣ በግልፅ በህዝቦች መካካል መተላለቅና መገዳደልን እንዲኖር ጥሪን፣ አንድን ቡድን ብሔርን አልያም እምነትን ታርጌት ያደረገ ጥላቻን፣ የክርስትና እምነት ተከታዮች በከፍተኛ ሁኔታ ፍርሃት ውስጥ እንዲወድቁ ጥጋቸውን ይዘው ርቀው እንዲቀመጡ የፍራሃት ቆፈን የሚዘሩ ፍራስትሬሽን ውስጥ የሚከቱ መልዕክቶችን ሪከርዶችን ከሁለት ጊዜ በላይ ስክሮል ሳታደርግ ታጭቆ ታገኛለህ።



ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን የት ነው፣ የምታውቁት በየትኛው መድረክና ቦታ ላይ ነው፤ እነስዩም ተሾመ የሚቃዡበትን፣ ዘመድኩን ፖስት ለማድረግ ሁልጊዜ የሱን ስም መጥራት ያስፈለገበትን በሚወነጅሉት ልክ የሰራቸው የፃፋቸው፣ ቅስቀሳ ያደረገባቸው፤ በርግጥ ተከታይህ መንጋ ከሆነ መጀመሪያውንም አይኑን አስረህ ስለሆነ የምትመራው ማስረጃ የሚጠይቅ የለም። ግን ባሻየ የሰጡህን ሁሉ አትጠጣ አሳማኝና አስረጂ ፈለግ እስኪገባህ ድረስ ጠይቅ፤ እኔ የማውቀው አህመዲን ጀበል ላመነበት ቅንጣት ታክል የማይፈራ በድብቅና በር ዘግቶ ጥላቸን የማይዘራ ግልፅ የሆኑ መልዕክቶችን የሚያስተላልፍ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚገባውን ክብርና መልካምነት በኢስላማዊ መንገድ የሚሰጥ፣ ማንኛውንም ሰው ቅንጣት ታክል የማይፈራ መንግስትን ጨምሮ የሚያውቀውን በግልፅ የሚናገርና የሚፅፍ የታሪክ ተመራማሪ እጅግ ሲበዛ ዝምተኛ ሰው ነው።

ወዳጄ ተኩላው በጫጫታ በሆይታና በውንጀላ መሪህን አሚርህን ለይቶ ለማጥቃትና አንተን ለመበተን የሚሰራውን ስራ ከወዲሁ ነቅተህ ጠብቅ

01/05/2022

የኡስታዝ አቡበከር አይረሴ መድረክ!

በገለልተኛነት ማጭበርበር ድሮ ቀረ‼      ★★★//💗// ★★★በአብዱልጀሊል ሼህ አሊ ካሳ❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄የድህረ ደርግን የኢትዮጵያ ሙስሊም– ክርስቲያን መልካም ግንኙነቶችና ግጭቶች ...
01/05/2022

በገለልተኛነት ማጭበርበር ድሮ ቀረ‼
★★★//💗// ★★★
በአብዱልጀሊል ሼህ አሊ ካሳ
❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄
የድህረ ደርግን የኢትዮጵያ ሙስሊም– ክርስቲያን መልካም ግንኙነቶችና ግጭቶች በተመለከተ በርካታ ጥናቶች ተሰርተዋል።

ከነዚያ ጥናቶች ውስጥ ያገኘሁትና በሂደት ያረጋገጥኩት ነገር የሙስሊሙና የክርስቲያኑ የፖለሚክስ ሜዳ የተለያየ እንደነበር ነው።

የኢ/ኦ/ቤተ–ክርሰስቲያን በጣት የሚቆጠሩ ምናልባትም ከሦስትና አራት ያልበለጡ መፅሔቶችና ጋዜጣዎች (አኮቴት፣ መርሀጽድቅ፣ ሐመር) ብቻ ይዛ ለሶስትና አራት አስርት አመታት ይዛ ስትዘልቅ ሙስሊሙ ደግሞ ብቅ ብለው እልም የሚሉ ከ18 ባለይ ኢስላማዊ ጋዜጦችና መጽሔቶች ነበሩት።

እንዴት የኢ/ኦ/ቤተ ክርስቲያን ከሙሰሊሙ ያነሰ ሚዲያ ሊኖራት ቻለ? የሚል ጥናት ቢጤ አደረግኩ? የዚህ ፓራዶክሰ መሳይ ጉዳይ ሲጠና ውጤቱ ሌላ ነው።

ሙስሊሙ ሚዲያውን ኢስላማዊ ብሎ፣ የሙስሊም ስም ሰጥቶ፣ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አውጆ የህዝበ ሙስሊሙን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና መንፈሳዊ ጉዳይ በነዚሁ ኢስላማዊ ሚዲያዎች በኩል ብቻ የሚያራምድ ነበር።

የኢ/ኦ/ቤተ ክርስቲያን ያሏትን ውስን መንፈሳዊ ሚዲያዎች ለመንፈሳዊና ለአስተዳደራዊ ጉዳይዋ አውላ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮቿን የምታራምደው በስምም፣ በምዝገባም በእውቅናም ሴኪዩላር ተደርገው በተገለፁ ጋዜጣዎች፣ መፅሔቶች፣ ማህበራዊ ሚዲያዎችና ሜይንስትሪም ሚዲያዎች ነበር። ዓለማዊ /ሴኪዩላር በሚል ሽፋን የሚንቀሳቀሱ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮች፣ አክቲቪስቶች፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ቢሮክራቶች በሙሉ በሚባል ደረጃ የቤተ–ክርስቲያኗ ተልዕኮ የወሰዱ ሠራዊቶች ነበሩ።

ፕ/ር ሁሴን አህመድ polemics በተሰኘው ጥናቱ ሴኪዩላር ሆነው የተመሰረቱ በመቶወች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞችና ሚዲያዎች በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና በእስልምና ላይ ተደጋጋሚ ሴራ፣ ፖለቲካዊ አሻጥር፣ የስም ማጥፋትና የውንጀላ ዘመቻዎችን ገለልተኛ መስለው በየህትመቱ የሚያራምዱ ነበሩ። ሙስሊሙ ደግሞ በኢስላማዊ መፅሔቱ እና ጋዜጣው የጋዜጠኝነትን ሥነ–ምግባር እያጣቀሰ፣ የተዛባ ዘገባና ህትመት መሰራቱን ሲቃወም ሲያስረዳ እድሜውን መፍጀቱን ይገልፃል ፕሮፌሰሩ።

ስለዚህ እነሱ በሴኪዩላር ሚዲያ/ቢሮክራሲ/ፓርቲ ሲያጠቁት ሙስሊሙ ደግሞ በኢስላማዊ ሚዲያዎቹ ነበር ሲከላከል የኖረው ።

ዛሬ ህዝበ ሙስሊሙ በተለይ በማሀበራዊ ሚዲያ መሳተፍ ሲጀምር በየቀኑ ክው ብሎ መደንገጡን ተያይዞታል። ለወትሮው በጋዜጠኛነት፣ በፖለቲከኛነት፣ በአክቲቪስትነት ወዘተ የሚያቃቸው ግለሰቦችምና ተቋማት ፀረ–ሙስሊምና ፀረ–እስላም ሆነው ሲያገኛቸው መደነቅም መወዛገብም ያጋጥመዋል። እስክንድር ነጋን የጋዜጠኛ ቁንጮ አድርጎ ሲያምን የኖረ ሙስሊም ዛሬ "እስክንድርን ምን ነካው? " ብሎ ከመወዛገብ አልፎ የስክንድር እና የመሰሎቹ የተልዕኮ ማዕከል የት እንደሆነ ማወቅ ጀምሯል።

ዩቱበሮች፣ አክቶቪስቶች፣ ቲክቶከሮች፣ ብሎገሮች፣ የሜይን ስትሪሙ ሚዲያ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ አርቲስቶች፣ አመራሮች ውስጥ አብዛኞቹ የተልእኮ ማዕከላቸው፣ አሰማሪያቸው ቤተ—ክርስቲያኗ መሆኑን ህዝበ ሙስሊሙ ዘግይቶም ቢሆን ማወቅ ችሏል።

||||ወራቤ የተፈጠረው ምንድን ነው?!  #ብዙዎቻችሁ በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን መዲና ወራቤ ከተማ የተከሰተውን ጠይቃችሁኝ ነበር። እኔም በተቻለ መጠን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ያገኟኋቸውን መረጃ...
29/04/2022

||||ወራቤ የተፈጠረው ምንድን ነው?!

#ብዙዎቻችሁ በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን መዲና ወራቤ ከተማ የተከሰተውን ጠይቃችሁኝ ነበር። እኔም በተቻለ መጠን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ያገኟኋቸውን መረጃዎች ላካፍላችሁ ወደድኩ። እንደሚታወቀው በአማራ ክልል መንግስት ስርዓት ከለላ የተሰጣቸው በፋኖ፣ ሚሊሻና መሰል ይፋዊና ህቡዕ አደረጃጀቶች ከቤተ ክህነቷም ተልዕኮ የተሰጣቸው አክራሪ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አሸባሪዎች በጎንደር ንጹሐን ሙስሊሞች ላይ የሽብር ጥቃት በተደራጀና በጦር መሳሪያ በታገዘ መልኩ መፈጸም ከጀመሩ 3ኛ ቀናቸውን ይዘዋል። በዚህ የሽብር ጥቃት ከዛሬው ውጭ በርካታ መስጂዶች መቃጠላቸው፣ ከ40 በላይ ሙስሊሞች መገደላቸው፣ 200 ገደማ የሚሆኑት ደግሞ ለከፍተኛ የአካል ጉዳት መዳረጋቸው፣ የተመረጡ የሙስሊም ሱቆችና ንብረቶች መቃጠላቸው… ይታወቃል።
ይህን የሽብር ጥቃት ተከትሎ በርካታ የሃገራችን ሙስሊሞች በሰላማዊ መልኩ ተቃውሟቸውን በመግለፅ መንግስት በአሸባሪዎቹ ላይ እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ይገኛሉ። ከነዚህም ከተሞች መካከል፤ አዲስ አበባ፣ ባህር ዳር፣ ጂማ፣ ጂጂጋ፣ ድሬዳዋና ወራቤ ይገኙበታል።

#በትላንትናው ዕለት የወራቤ ሙስሊሞች ተቃውሞ እያካሄዱ ሳለ፤ ከቀናት በፊት በወራቤ ዩኒቨርስቲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በተማሪዎች ህብረት ስም ያደራጃቸው የአማራ ክልል ተወላጅ የሆኑ የጎንደሩ የሽብር ድርጊት ፈጻሚዎች የህዝበ ሙስሊሙን ሰላማዊ ሰልፍ ለመረበሽ ሞከሩ። የወራቤ ሆስፒታልን ጨምሮ ከተማዋን በልሙጥ ባንድራ ሲያጌጡ የነበሩ በሥራ ጉዳይ ወደ ከተማዋ የገቡ ጽንፈኞችም ተጨመሩ። ሙስሊሞቹ ሰልፈኞች በወራቤ ሩፋዔል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ሲያልፉ የቤተ ክርስቲያኗ ዘበኛ ጥይት ተኩሶ አንድ ሙስሊም አቆሰለ። ሆኖም ግን ህዝበ ሙስሊሙ፣ የጸጥታ አካላትና የሃገር ሽማግሌዎች ወጣቶች ስሜታዊ ከመሆን እንዲቆጠቡ አድርገው ከተማዋ ወደ ቀድሞ ሰላማዊ መንገዷ እንድትመለስ አድርገዋል።

#በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተሰገሰጉ የጎንደሩ አሸባሪ ቡድን አጋሮች ግን የድፍረታቸው ድፍረት መስጅድ ካላቃጠልን ብለው ረብሻ ቀስቅሰው ነበር። ከፊሎቹ ወደ ጫካ ሸፍተዋል የሚልም መረጃ ደርሶኛል። በተጨማሪም እነዚህ የኦርቶዶክስ ሀይማኖት አክራሪዎች ፕሮቴስታንት ወገኖቻቸው ሙስሊሙን በመረበሽ እንዲያግዟቸው ሎቢ ሲያድርጓቸው አሻፈረን ሰላም እንፈልጋለን በማለታቸው ስልጤንና ሰላማዊውን የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮችን ከጎሮቤት ዞኖች ለማጋጨት የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን አቃጠለዋል። ይህቺን ሰበብ ያገኙ፤ የጎንደሩን የሽብር ጥቃት አድፍጠው ሲመለከቱ የነበሩ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ታዋዊ ሚዲያዎችና ገጾች ተንበጫበጩ። አሰፍስፈው እንዲህ አይነት ዜና ሲጠብቁ የነበሩት እነ መምህር ምህረተ አብ አሰፋ፣ ዲያቆን አባይነህ ካሴ፣ ዘመድኩን በቀለና መሰሎቻቸው የጎንደሩን ብልግናቸውን ለመሸፋፈን ዜናውን አሯሯጡት። የሙስሊም ደም መፍሰስ ከከተማ ገፅታ ያነሰባቸው ዋልጌዎችም ተቀባበሉት። እስከ ዛሬ ሚዛናዊ የሚመስሉን ግለሰቦችና ጋዜጠኞችም ጭምብላቸውን ሲያወልቁ ታዘብን።

#ለማንኛውም እነዚህ ወጨጌዎች አሁንም ትንኮሳ ፈጽመው ሊያስወሩ ስለሚችሉ፤ የወራቤ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በደንብ ተከታትላችሁ ለጸጥታ አካላት አሳልፋችሁ ስጡ። ስልጤ ሥራ ላይ እንጂ ሽብር ላይ አይታወቅም።

#የባድ ወልድ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው። የአማራ ክልል አሸባሪዎች ባጠፉት ጥፋት በስልጤ የሚኖሩ ሰላማዊ ክርስቲያኖች የሚገደሉበት አንዳችም ምክንያት የለም። ባይሆን ግን በከተማዋ ውስጥ ያሉ ከአማራ ክልል የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት አደብ ሊገዙ ይገባል። በእነርሱ ጽንፈኝነት የተነሳ የስልጤ ስም መጥፋት የለበትም።

#አላህ ሃገራችንን ሰላም ያድርግልን!

አንብባችሁ ሼር አድርጉት!!!
29/04/2022

አንብባችሁ ሼር አድርጉት!!!

ይህ አሸባሪ በቁጥጥር ስር ሊያውለው ይገባል ⛔️ኢትዮጵያ ህግ የሚያስከብር እውነት መንግስት ካላት ይሄን የጎንደር ሙስሊሞች ላይ የዘር ማጥፋት ያዘዘውን አሸባሪ በቁጥጥር ስር ማዋል አለበት አ...
29/04/2022

ይህ አሸባሪ በቁጥጥር ስር ሊያውለው ይገባል ⛔️

ኢትዮጵያ ህግ የሚያስከብር እውነት መንግስት ካላት ይሄን የጎንደር ሙስሊሞች ላይ የዘር ማጥፋት ያዘዘውን አሸባሪ በቁጥጥር ስር ማዋል አለበት አለበለዚያ ኢትዮጵያ መንግስት አላት አንልም።

(ሼር አድርጉ)

28/04/2022

የታሰሩት ወንድሞቻችን ይፈቱ

27/04/2022

''የፌድራል መንግስት በአስቸኳይ ገብቶ ችግሩን መፍትሄ ይስጥ ''
___ ኡስታዝ ሙሀመድ አባተ በወቅታዊ የጎንደር ጉዳይ በሼይኽ ሆጄሌ መስጅድ ያስተላለፈው መልእክት

ፆመኞችን በጥይት የምታስፈጥር ከተማ  #ጎንደር ብቻ ናት ለታሪክ ይቀመጥ።
27/04/2022

ፆመኞችን በጥይት የምታስፈጥር ከተማ #ጎንደር ብቻ ናት ለታሪክ ይቀመጥ።

በህግ ይጠየቁ እነዚህ ወንጀለኞች!!!1- ዲያቆን አባይነህ ካሴ2- ዲያቆን ዬርዳኖየእነዚህን ሰዎች ጉዳይ በንቃት ልንከታተል ይገባል !የ5መስጅዶች ቃጠሎ የ21የንፁሃን ነፍስ ግድያ ቀዳሚ ተጠያ...
27/04/2022

በህግ ይጠየቁ እነዚህ ወንጀለኞች!!!

1- ዲያቆን አባይነህ ካሴ
2- ዲያቆን ዬርዳኖ
የእነዚህን ሰዎች ጉዳይ በንቃት ልንከታተል ይገባል !
የ5መስጅዶች ቃጠሎ የ21የንፁሃን ነፍስ ግድያ ቀዳሚ ተጠያቂዎች ናቸው !

26/04/2022

መሳፍንት ተብዬው ስለ ሙስሊሞች የሰጡትን ስሙት!

ሙስሊሞች ስልጣን እንዲይዙ አንፈልግም አንፈቅድም በዚች ሀገር ላይ። ኢስላም ልብስ ናቸው ክርስቲያን ግን ውርስ ናቸው እያለ ነው ስሙት።

ሼር አድርጉት

ኦህ ጎንደር አኬልዳማ!! Hassen▬▬▬▬▬▬▬▬▬●●▬▬▬▬▬▬▬▬▬በአማራ ክልል ያለውን ሙስሊም ጠልነት ክስተቶችን እየጠበክ በመጮህ አትፈታውም። ከስማዳ እስከ ሞጣ ታላላቅ ክስተቶች ተፈጥረው...
26/04/2022

ኦህ ጎንደር አኬልዳማ!!

Hassen
▬▬▬▬▬▬▬▬▬●●▬▬▬▬▬▬▬▬▬
በአማራ ክልል ያለውን ሙስሊም ጠልነት ክስተቶችን እየጠበክ በመጮህ አትፈታውም። ከስማዳ እስከ ሞጣ ታላላቅ ክስተቶች ተፈጥረው በማግስቱ ነው የተረሱት። በክልሉ ከ30 መስጅድ በላይ ወድመው ብዙ ሰዎች ሙስሊም ስለሆኑ ብቻ ተቀጥቅጠው ተገለው አንድ ግለሰብ እንኳ ተጠያቂ አልሆነም።
በመሆኑም በክልሉ የሚታየውን ስር የሰደደ ኢስላም ጠልነት መፍትሄ እንዳገኝ መስራት እንጅ ክስተቶችን ተከትሎ ማልቀስ መፍትሄ የለውም። ይህን አይነት ስር የሰደደ ችግር መፍታት የሚቻለው ጠንካራ ተቋም መስርቶ (ጠንካራ መጅሊስ ለማለት ነው) ትግልን ተቋማዊ በማድረግ ነው። ይህ ካልሆነ መሰል ክስተቶች ይቀጥላሉ።

ሰበር ዜና...!!!ዛሬ በአፋር ሰመራ የተደረገው Grand ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር 2.7Km ርዝመት ሲኖረው በሀገራችን ደረጃ ከምርጥ 5 ተቀላቅሏል።Ahmed Habib Alzarqawiማሻአላህ❤️...
24/04/2022

ሰበር ዜና...!!!

ዛሬ በአፋር ሰመራ የተደረገው Grand ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር 2.7Km ርዝመት ሲኖረው በሀገራችን ደረጃ ከምርጥ 5 ተቀላቅሏል።

Ahmed Habib Alzarqawi
ማሻአላህ❤️❤️🙏

አላሁ አክበር  ጀግናው ገራድ አትሌት ሙክታር ኢድሪስ ለኢብኑ አባስ መስጂድና መድረሳበእናቱ ስም  50,000 ብርበአባቱ        50,000 ብርበራሱ         100,000 ብር👉 በድምሩ...
23/04/2022

አላሁ አክበር ጀግናው ገራድ አትሌት ሙክታር ኢድሪስ ለኢብኑ አባስ መስጂድና መድረሳ
በእናቱ ስም 50,000 ብር
በአባቱ 50,000 ብር
በራሱ 100,000 ብር
👉 በድምሩ 200,000 ብር
🇪🇹❤️❤️❤️❤️🇪🇹
ጀግናችን ወላሂ❤

አፍጋኒስታን Tik tok የተባለውን የእብዶች መናሃሪያ በሀገሯ አገልግሎት እንዳይሰጥ አገደች ። የታሊባን ባለስልጣናት እንዳስታወቁት እምነታችንን የሚሸረሽር እና ትዉልድን ያለ ሥነ- ምግባር ...
23/04/2022

አፍጋኒስታን Tik tok የተባለውን የእብዶች መናሃሪያ በሀገሯ አገልግሎት እንዳይሰጥ አገደች ። የታሊባን ባለስልጣናት እንዳስታወቁት እምነታችንን የሚሸረሽር እና ትዉልድን ያለ ሥነ- ምግባር የሚያስቀር ነዉ ሲሉ ገልጸዋል ። ማሻ አሏህ ሙሥሊም ሃገራቶች በሙሉ ቢያግዱ ለምሳሌ ሳውዲ አረቢያ

ወላሂ ለነዚህ ድንቅና ጀግና ፍልስጤማዊ ህፃናት ለመናገር ቃላት የለኝም 💪❤🤗🇵🇸🇵🇸አላህ ከናንተ ጋር ይሁን
23/04/2022

ወላሂ ለነዚህ ድንቅና ጀግና ፍልስጤማዊ ህፃናት ለመናገር ቃላት የለኝም 💪❤🤗🇵🇸🇵🇸

አላህ ከናንተ ጋር ይሁን

ይሄ ቁርዐን የሁለት ሀገር ብርሃን ነው።
19/04/2022

ይሄ ቁርዐን የሁለት ሀገር ብርሃን ነው።

ኢንሻአላህ በቅርቡ ❤️❤️❤️
18/04/2022

ኢንሻአላህ በቅርቡ ❤️❤️❤️

አዲስ የምስራች!!!28 የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሰራው እና 3 ልዩ ልዩ ድሮኖችን የሰራው ኢብራሂም አሊ አሁን ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ አመት ተማሪ ሲሆን ዛሬ ስራዎቹን በማ...
17/04/2022

አዲስ የምስራች!!!

28 የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሰራው እና 3 ልዩ ልዩ ድሮኖችን የሰራው ኢብራሂም አሊ አሁን ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ አመት ተማሪ ሲሆን ዛሬ ስራዎቹን በማህበራዊ ሚዲያ ለማስተዋወቅ እንዲያግዘው፣ ኔትወር ለመፍጠር እና ሌሎች ወጣቶችን ለማነቃቃት የፌስቡክ ገጽ ከፍቷል። ፎሎው አድርጉት ምን ምን ችግር ፈቺ ስራዎችን ከትምህርቱ ጎን ለጎን እንደሰራ ተመልከቱለት። ኢብራሂም ግሩም ስብዕና፣ ጠንካ የስራ ባህል ያለው እና ቪዥነሪ የሆነ ጓደኛዬ ነው።

https://m.facebook.com/IbrahimInnovations

ፍልስጤም እና አቅሳ የማን እንደሆነ ነው የሚያሳየው ይህ ምስል!
17/04/2022

ፍልስጤም እና አቅሳ የማን እንደሆነ ነው የሚያሳየው ይህ ምስል!

ሰበር ዜና!!!Dr Artist Alii Birraa በኢስላሚክ ሚዲያ ላይ በመቅረብ ወደ ዘፈኑ አለም እንደማይይመለስ ተናግሯል አላህ ተውበቱን ይቀበለው።
16/04/2022

ሰበር ዜና!!!

Dr Artist Alii Birraa በኢስላሚክ ሚዲያ ላይ በመቅረብ ወደ ዘፈኑ አለም እንደማይይመለስ ተናግሯል አላህ ተውበቱን ይቀበለው።

በዱባይ አለም አቀፍ የቁርአን ውድድር 9ኛ በመውጣት የተሸላመው ኢትዮጵያዊ ቃሪእ ኢብረህም ሼክ ኸይረድንበ ቦሌ አየር ማረፊያ በኡስታዞች አቀበበል ተድርጓወል
16/04/2022

በዱባይ አለም አቀፍ የቁርአን ውድድር 9ኛ በመውጣት የተሸላመው ኢትዮጵያዊ ቃሪእ ኢብረህም ሼክ ኸይረድን
በ ቦሌ አየር ማረፊያ በኡስታዞች አቀበበል ተድርጓወል

የ15 አመት ታዳጊው የ11ኛ ክፍል ተማሪ እና የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪው ሙሳ ከድር ገና በልጅነቱ የተለያዩ ግሩም የፈጠራ ስራዎችን አበርክቷል ድሮን፣ ገመድ አልባ የኤሌክትሪክ ቻርጀር፣ የኤሌ...
16/04/2022

የ15 አመት ታዳጊው የ11ኛ ክፍል ተማሪ እና የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪው ሙሳ ከድር ገና በልጅነቱ የተለያዩ ግሩም የፈጠራ ስራዎችን አበርክቷል ድሮን፣ ገመድ አልባ የኤሌክትሪክ ቻርጀር፣ የኤሌክትሪክ ሃይል ማከማቻ ፓውር ባንክ ሲስተም እና ቫኪዩም ክሊነር ከብዙዎቹ ተጠቃሾች ናቸው። ይህ ታዳጊ ከፈጠራ ስራዎቹ በተጨማሪ የጠፈር ሳይንስ ምርምሮችን ያደርጋል ለዛ የሚያግዙት መጽሃፎችን ያነባል። እኔ ሙሳን ለመጀምሪያ ጊዜ ያየሁት ከነ ህጻን እንቁበሃሪ ጋር ከሰባት ወር በፊት የአንድሮሜዳ ዝግጅት ስለ ኳንተም ፊዚክስ ገለጻ ሲሰጥ ነበር።

ይህ ታዳጊ አሁንም ግሩም የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ከዛ በተጨማሪ ሁለት መጽሃፍቶችን እየጻፈ ይገኛል። የመጀመሪያ እና ዋነኛው መጽሃፉ ሰዎች አስትሮኖሚን መማር ቢፈልጉ የሚከተሏቸው ቅድም ሁኔታዎች ያካተተ የመመሪያ መጽሃፍ ሲሆን 70 ገጽ የሚሆን እርዝማኔ አለው። ይህ መጽሃፍ ታዳጊው እንደገለጸው ለህትመት የደረሰ ሲሆን ለማተም ድጋፍ እንደሚፈልግ ገልጾአል።

ሙሳ ለፈጠራ ስራዎቹ እና ስፔስ ሳይንስ ምርምሩ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ኢንስቲትዩት፣ አንድሮሜዳ መጽሃፍት እንዲሁም ሌሎች በርካታ የውድድር እና በዘርፉ የእውቅና መድረኮች ላይ ሰርተፊኬት ማግኘት ችሎአል።

ባልተመቻቸ ሁኔታዎች ዉስጥ ሆኖ እነዚህን የፈጠራ ስራዎች፣ ድርሰት፣ ምርምር እና ትምህርትን በከፍተኛ ደረጃ ማስኬድ መቻል ልፋቱ እንዲሁም የሚያስከፍለው መሰዋዕትነቶች ሁሉ በግሌ አውቀዋለሁኝ የሙሳን ግን ልዩ ነው ምክኒያቱም ሙሳ የፈጠራ ስራዎች ማበርከት እና ከፍተኛ ምርምርን የጀመረው አቻዎቹ ጨዋታ ላይ እያሉ ነበር በጣም በልጅነቱ ነው።

ተማሪ ሙሳ ለሚሰራቸው የፈጠራ ስራዎቹ የእቃ አቅርቦት እና ሌሎች ድጋፎች እንደማያገኝ እና ድጋፍ ቢያገኝ የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንደሚችል በግል አውቃለሁኝ: ታዳጊውን መደገፍ እና ማበረታታት ለምትፈልጉ
Email: [email protected]
Phone: +251936291040 በኩል ማግኘት ትችላላችሁ።

የተማሪ ሙሳ ኢንተርቪው በአንድሮሜዳ በባላገሩ ቴሌቪዥን:-
https://youtu.be/DjAz46iJhjY

የተማሪ ሙሳ ኢንተርቪው በናሁ ቲቪ:-
https://youtu.be/o_75WnI2Sjo

Photo Credit: Nahoo Tv / YomTech With Ermias

 #ፍልስጥኤም የወራሪዋ እስራኤል ወታደሮች የአልአቅሷ መስጅድ ላይ ጥቃት ፈፅመው የፈጅር ሶላት ላይ የነበሩ በርካታ ምእመናንን አቁስለዋል ። ከዚህ በፊት ከተደረገው ሁሉ በከፋ መልኩ እስራኤል...
16/04/2022

#ፍልስጥኤም

የወራሪዋ እስራኤል ወታደሮች የአልአቅሷ መስጅድ ላይ ጥቃት ፈፅመው የፈጅር ሶላት ላይ የነበሩ በርካታ ምእመናንን አቁስለዋል ። ከዚህ በፊት ከተደረገው ሁሉ በከፋ መልኩ እስራኤል ራሷ የተስማማችባቸውን ስምምነቶች ሳይቀር በመጣስ የሙስሊሞች ሶስተኛ ቅዱስ ቦታ የሆነውን አልአቅሷን በተኩስ ሲያደበላልቁት ውለዋል ። አልአቅሷ መስጅድም የመስገጃና ማምለኪያ ቦታ ሳይሆን የጦር ሜዳ ሆኖ ውሏል ።

# ህንድ

በ ናሬንድራ ሞዲ የሚመራው ኢስላም ጠሉ የህንድ መንግስት የሙስሊሞችን ቤት ልክ እንደ እስራኤል ሲያፈራርስ ውሏል ። በርካታ ቡልዶዘሮችም የሙስሊሞችን ቤት በጅምላ ሲያፈራርሱ ውለዋል አሁንም ሞጥሏል ።

ጉዳዩ እንድህ ነው የሂንዱ እምነት አማኞች ሀይማኖታዊ በአላቸው ከቀናት በፊት ነበር ። እናም ሂንዱዎቹ በአላቸውን ለማክበር በከፍተኛ ጭፈራና የአምልኮ ዝማሬ ወደ መስጅዶችና የሙስሊም ቤቶች ይገባሉ ። በዚህም ከሙስሊሞች ጋር ከፍተኛ ፀብ ይፈጠራል ። ሙስሊሞቹ ራሳቸውንና መስጅዶቻቸውን ለመከላከል ሞከሩ ።

የህንድ መንግስትም ሙስሊሞቹን ለምን ራሳቸውን ተከላከሉ በማለት የቅጣት እርምጃ ይወስናል ቅጣቱም " ቤታቸውን በጅምላ አፍርሱ " የሚል ነበር ። እናም ተፈፀመ ።

አንድት ቤቷ የፈረሰባት ሙስሊም ለ BBC ስትናገር " ዶዘሩ ሲመጣ ስናይ ተደናገጥን በመቶዎች በሚቆጠሩ የፀጥታ ሀይሎች ተከቧል እባካችሁን ንበረታችንን እንኳ እናውጣ አልናቸው እምቢ አሉን እሺ ከቤት ውስጥ ያለውን ቁርአን እንኳ እናውጣ አልናቸው እምቢ ብለው ከነንብረታችን ከነ ቁርአናችን አፈራረሱት " ብላለች ።

ህንድ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ካሽሚራዊያንን የቁም እስረኛ አድርጋ እያሰቃየች ያለች ኢስላም ጠል ሀገር ናት ።

#ስዊድን

የስዊድን ፖለቲከኛ በዛሬው እለት ቁርአንን በአደባባይ ሲያቃጥል ውሏል ። ሙስሊሞች በሚበዙበት አካባቢ ሄዶ ቁርአንን ሲያቃጥል የነበረው ፖለቲከኛ ከሙስሊሞች ጥቃት እንዳይደርስበት በፀጥታ ሀይሎች ሲጠበቅ ነበር ። በስዊድን የኢስላም መስፋፋት የሚያሰጋቸው ኢስላም ጠል ፖለቲከኞች ቁርአንን ማቃጠላቸውና የኢስላም ውድ ነብይ የሆኑትን ሙሀመድን ሰ.ዐ.ወ መዝለፍ የተለመድ ሆኗል።

ኢንሻአላህ ሁሉም የእጁን ያገኛል ሙስሊም ሳነኩት ይጠነክራል እንጂ አይላላም

የሙስሊም ተማሪዎች ሊግየተማሪዎችን ሊግ እናጠናክር!ሙስሊሙ ተማሪ ስለ ሃይማኖቱ ያለው ግንዛቤ እንዲያድግና ከተለያዩ ማህበራዊና ሞራላዊ ስንክሳሮች ተላቆ ሀገር በመገንባትና በማሳደግ ሂደት ውስ...
16/04/2022

የሙስሊም ተማሪዎች ሊግ

የተማሪዎችን ሊግ እናጠናክር!

ሙስሊሙ ተማሪ ስለ ሃይማኖቱ ያለው ግንዛቤ እንዲያድግና ከተለያዩ ማህበራዊና ሞራላዊ ስንክሳሮች ተላቆ ሀገር በመገንባትና በማሳደግ ሂደት ውስጥ ጉልህ ሚና እንዲጫወት ማስቻል ያስፈልጋል።

በመሆኑም በሁሉም እርከን ላይ የሚገኘውን የተማሪ እና ወጣቱ ክፍልን ለማነጽ እና አምራች ትውልድ ለመፍጠር በሚደረገው ሃገራዊ ርብርብ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ለማድረግ፣ እንዲሁም ሲወርድ ሲዋረድ የመጠውን የተለያዩ እምነቶች እና ህዝቦች የመቻቻል፣ የመተሳሰብ፣ የመተጋገዝ እና በሰላም ተከባብሮ የመኖር መልካም እሴቶችን ለማጎልበት ”የሙስሊም ተማሪዎች ሊግ“ የተሰኘ ተቋም ከተቋቋመቋ እነሆ 4ኛ አመቱን እያስቆጠረ ነው።

እስካሁንም በርካታ ስራዎች ሲያከናውን ቆይቷል። በመሆኑም በቀጣይነት ዘርፈ ብዙ ተግባሮችን ለማከናወን ይህን ሀገረ አቀፍ የተማሪዎች ሊግ እናግዝ!

በዱባይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ኢትዮጵያን በመወከል በውድድሩ የተሳተፈው ኢብራሂም ኸይረዲን 9ተኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀቀ በዱባይ በዘንድሮ ረመዷን ‎ኢንተርናሺናል የቁር...
15/04/2022

በዱባይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ኢትዮጵያን በመወከል በውድድሩ የተሳተፈው ኢብራሂም ኸይረዲን 9ተኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀቀ

በዱባይ በዘንድሮ ረመዷን ‎ኢንተርናሺናል የቁርዓን ውድድር ለ25ተኛ ዙር የተካሄደ ሲሆን በዘንድሮው የቁርዓን ውድድር ተሳታፊ የሆነው ኢብራሂም ኸይረዲን 9ተኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቋል ።

ሃሩን ሚዲያ ሚያዝያ 7 ፣ 2014

ኮምቦልቻ ለሚያዚያ 9 ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር" ሙስሊም ነኝ ሰላቴ ሕይወቴ " ❤🙏
15/04/2022

ኮምቦልቻ
ለሚያዚያ 9 ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር
" ሙስሊም ነኝ ሰላቴ ሕይወቴ " ❤🙏

😭😭😭አምና በደሴ የተከናወነው የጎዳና ላይ ኢፍጧር 1 ላይ ዋና አስተባባሪ የነበረው ወንድማችን ኢንጂነር ካሊድ እጅጉ ነገ በከተማችን የሚከናወነው ኢፍጧር ፕሮግራም ላይ ከጎናችን ባይኖርም ከእ...
14/04/2022

😭😭😭

አምና በደሴ የተከናወነው የጎዳና ላይ ኢፍጧር 1 ላይ ዋና አስተባባሪ የነበረው ወንድማችን ኢንጂነር ካሊድ እጅጉ ነገ በከተማችን የሚከናወነው ኢፍጧር ፕሮግራም ላይ ከጎናችን ባይኖርም
ከእርሱ መልካምነትን ቅንነትን እና ለወንድም ሀጃ መቆምን ተምረናል እና ስርክ እናስታውስዋለን‼️

ካሊዶ በልባችን ሁሌም ህያው ነህ ቀብርህን ኑር ያድርግልህ‼️
ahmed

ማሻአላህ.🙏የደረጃ መውጫ ዊልቸር(Stair Climber Wheelchair) ፈጣሪ እና የባለ ብዙ ጥቅም ጠረጴዛ (Smart Table) የፈጠራ ሃሳብ አመንጭ የሆነችው የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴ...
14/04/2022

ማሻአላህ.🙏

የደረጃ መውጫ ዊልቸር(Stair Climber Wheelchair) ፈጣሪ እና የባለ ብዙ ጥቅም ጠረጴዛ (Smart Table) የፈጠራ ሃሳብ አመንጭ የሆነችው የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ...!

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአዳዲስ የፈጠራ ስራዎች መፍለቂያ እና የኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል ለመሆን እየተጋ እና እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ተማሪዎቹን በልዩ የፈተና ውጤት በመቀበል በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የራሳቸውን ተሰጥኦ እንዲያዳብሩ እና የፈጠራ ባለቤት እንዲሆኑ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
የአዲስ አባባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ አመት ተማሪ የሆነችው አፍራ ሁሴን ሰይድ የፈጠራ ውድድር አሸናፊ ያደረጋትን ደረጃ መውጣት የሚያስችል ዊልቸር ፈጠራ በመስራት አሸናፊ ሆናለች፡፡ ይህ የፈጠራ ስራ ተማሪዋ ከአስራ አንደኛ ክፍል ጀምራ የሰራችው እና በአምሳለ ምርት (proto type) ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ገልፃ ለአቅመ ደካሞች እና ተሸከርካሪ ወንበር(wheelchair) ተጠቃሚ ለሆኑ ግለሰቦች ደረጃን ያለምንም ችግር መውጣት እና መውረድ የሚያስችል መሆኑን ገልፃለች፡፡ አፍራን ይህን ተሸከርካሪ ወንበር (wheelchair ) ለመስራት የተነሳሳችበትን ምክንያት ስትገልፅ አቅመ ደካሞች እና ተሸከርካሪ ወንበር ተጠቃሚዎች በተደጋጋሚ ደረጃዎችን ለመውጣት ፤ለመቆም ፤ሚዛናቸውን ለመጠበቅ ሲቸገሩ በመመልከቴ እና ችግሩን ለመፍታት በማሰብ ነው ብላለች፡፡
በዚህ ፈጠራ በእ.ኤ.አ 2019 ስቴም ፓወር እና ትምህርት ሚኒስተር በአዘጋጀው የፈጠራ ስራ ውድድር ላይ በመሳተፍ አሸናፊ መሆኗን አስታውሳ የፈጠራ ስራው የተለያዩ የርቀት ፤የከፍታ እና የፍጥነት መቆጣጠሪያ ሴንሰር የተገጠመለት በመሆኑ አቅመ ደካሞች የርቀት ፤የከፍታ እና የፍጥነትን መቆጣጠሪያ ሴንሰሮችን በመጠቀም ከአደጋ እና መሰል ጉዳቶች መጠበቅ እንደሚያስችል ገልፃለች፡፡
በሌላ በኩል አፍራን በትምህርት ቤቶች አካባቢ የሚታየውን ችግር ለመፍታት በማሰብ ባለብዙ ጥቅም ጠረጴዛ(smart table) የፈጠራ ሃሳብ በማመንጨት በእ.ኤ.አ 2022 አይከን አፍሪካ (ICON AFRICA) የተባለው ድርጅት በአዘጋጀአው የፈጠራ ሃሳብ ውድድር ተወዳድራ አሸናፊ ሆናለች፡፡ የፈጠራ ሃሳቡ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ያለውን የላብራቶሪ እና የቤተ-መፅሃፍት አገልግሎት እጥረት ለመቅረፍ እና ተማሪዎች በቤታቸው ሆነው ትምህርታቸውን ማጥናት እንዲችሉ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ቴክኖሎጂ ነው፡፡ በመሆኑም እንደ ፈጠራ ሃሳብ ባለቤቷ ገለፃ ከሆነ ይህ ጠረጴዛ ሁለት ገፅ ያለው እና ቁልፎች የተገጠሙለት በመሆኑ የተለያዩ ዶክመንቶችን ስካን ማድረግ የሚችል እና የሰዓት በቆጣጠሪያ ገፁን በመጠቀም ደግሞ ተማሪዎች ሰዓታቸውን በአግባቡ መጠቀም አለምጠቀማቸውን ይቆጣጠራል፡፡ የተማሪዎችን ስነ- ልቦናዊ ሁኔታ በመረዳት ሌሎች ተጨማሪ ትምህርቶችን መስጠት የሚያስችል እና የተማሪዎችን የእለት ከዕለት እንቅስቃሴ ለቤተሰብ ሪፖርት ማድረግ የሚያስችል የፈጠራ ሃሳብ ነው በማለት ገልፃለች፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በቤተ-መፅሃፍት ቤቶች አካባቢ ያለውን የኮምፒውተር እጥረት ለመፍታት ተማሪዎች የራሳቸውን የሚነበቡ ፋይሎች በፍላሽ ይዘው በመምጣት ማንበብ የሚችሉበትን ሁኔታ ይፈጥራል ስትል ተናግራለች ፡፡
ተማሪ አፍራ የፈጠራ ስራ በባህሪው የጋራ ርብርብን የሚጠይቅ እና ለብቻ የሚሰራ አለመሆኑን ጠቅሳ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የተለያዩ እውቀት ያላቸው ምሁራን እንደመኖራቸው የእውቀት እና የቴክኒክ ድጋፎችን እንደምትፈልግ አስረድታለች፡፡
በመጨረሻም ከልጅነት ጊዜዋ ጀምሮ አዳዲስ ሃሳቦችን እንድታመነጭ እና የፈጠራ ስራዎችን እንድትሰራ ያበረታቷትን እና አሁንም የሚያበረታቷትን አባቷን ዶ/ር ሁሴን ሰይድ እና ወላጅ እናቷን ወ/ሮ ሁሲኒያ ዳምጠውን አመስግናለች፡፡
ህዝብና አለምአቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

 ||♥   ||♥ ታላቁ ድግስ !ወሎ በታላቋ፣በጨረቃዋ፣በከዋክብቷ፣በአትጠየፍ  || የፊታችን ጁምዐ በወሎ ደረጃ ታላቅ የሆነ ድግስት ተደግሶ የኢፍጣሩ ሶደቃ ይጋፈራል።ጁምዐ ከሁሉም የወሎ ከተሞ...
14/04/2022

||♥ ||♥ ታላቁ ድግስ !

ወሎ በታላቋ፣በጨረቃዋ፣በከዋክብቷ፣በአትጠየፍ || የፊታችን ጁምዐ በወሎ ደረጃ ታላቅ የሆነ ድግስት ተደግሶ የኢፍጣሩ ሶደቃ ይጋፈራል።

ጁምዐ ከሁሉም የወሎ ከተሞችና ወረዳወች ምዕምናኑ ይተማል!!
እርሰወ በዚህ ፕሮግራም ላይ ባይገኙ ይቆጫሉ!!

 አሁን ደሞ ይህን ጎዳን በአቢዘር እንዲሰየም ምትስማሙ ሰዎች ቻለንጁን ትቀላቀላላቹ🙌
14/04/2022



አሁን ደሞ ይህን ጎዳን በአቢዘር እንዲሰየም ምትስማሙ ሰዎች ቻለንጁን ትቀላቀላላቹ🙌

ተራዊህ ሶላት በሀገረ ሞሮኮ 🇲🇦❤
13/04/2022

ተራዊህ ሶላት በሀገረ ሞሮኮ 🇲🇦❤

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Muslim Voice posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Muslim Voice:

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share