Boro Media Service

  • Home
  • Boro Media Service

Boro Media Service ኢትዮጵያዊነት አሸናፊነት !

በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚደንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ልዑክ በሻንጋይ የተለያዩ ተቋማትን ጎበኘ**************በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚደንት አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ ል...
17/11/2023

በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚደንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ልዑክ በሻንጋይ የተለያዩ ተቋማትን ጎበኘ
**************
በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚደንት አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በቻይና ሻንጋይ ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን እና ተቋማትን ጎብኝቷል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላት የሁዋዌ ቴክኖሎጂ ማዕከልን፣ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን፣ የሻንጋይ ከተማን እቅድና ዲዛይን እንዲሁም ደረቅ ቆሻሻን እንደገና ጥቅም ላይ የሚያውል ፕሮጀክትን መጎብኘቱ ተገልጿል፡፡

የጉብኝት መርሐ ግብሩ በሻንጋይ ከተማ ከሚከናወኑ ፕሮጀክቶች እቅድ፣ ትግበራ እና አፈጻጸም ልምድ ለመቅሰም ያለመ ሲሆን፤ ጉብኝት ካደረጉባቸው ተቋማት አመራሮች ጋርም የልምድ ልውውጥ ውይይት ማካሄዳቸው ተጠቁሟል፡፡

የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በሻንጋይ ከተማ የተመለከቷቸውን ፕሮጀክቶች በኢትዮጵያ መተግበር የሚያስችል ተሞክሮ ማግኘታቸውን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

በመተከል ዞን እየለሙ የሚገኙ ሰብሎች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ ከማሳደግ  ባለፈ ለገበያ መረጋጋት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የመተከል ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ተናገሩ።  በምክትል አስተዳዳሪው የሚ...
17/11/2023

በመተከል ዞን እየለሙ የሚገኙ ሰብሎች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ ከማሳደግ ባለፈ ለገበያ መረጋጋት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የመተከል ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ተናገሩ።

በምክትል አስተዳዳሪው የሚመራ የአመራሮችና የባለሙያዎች ቡድን በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በመኸር እርሻ የለሙ ሰብሎችን ምልከታ አድርገዋል።
የመተከል ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ግዛቱ ባልዳ በቀጠናው የተገኘውን ሰላም ተክትሎ የለሙ ሰብሎች የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ ለማሳደግ አይነተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

አቶ ግዛቱ አክለው በዞኑ በተያዘው የመኸር እርሻ 479ሺ ሄክታር መሬት በሰብል ለመሸፈን ታቅዶ 322ሺ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈናቸውን አብራርተዋል።
በቀጠናው ያለውን ሰላም ተከትሎ በዞኑ እየተመረተ ያለው ምርት እንደ ሀገር እየተስተዋለ ያለውን የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገልጿል።
በወረዳው በመደበኛ የመኸር እርሻ በኩታ ገጠም እየለሙ የሚገኙ ሰብሎች አበረታች ናቸው።

18ኛ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በቡለን ወረዳ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አብዮት በከኖ አሳዉቁ ። 18ኛ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በቡለን ወ...
16/11/2023

18ኛ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በቡለን ወረዳ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አብዮት በከኖ አሳዉቁ ።

18ኛ የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በቡለን ወረዳ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አብዮት በከኖ አሳዉቁ ። ዋና አስተዳደሪ አቶ አብዮት በከኖ በዓሉን አስመልክቶ በሰጡት ጋዘጣዊ መግለጫ በቡለን ወረዳ ደረጃ ከወትሮ በተለየ መልኩ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ገልጿል ።

የ2016 ዓ/ም የአገሪቱ ሕግ መንግስት የጸደቀበትና የብሔር ብሐረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በወረዳ ደረጃ በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅት የተጀመረ መሆኑን በመግለጽ በአገራችን በነበረዉ ሪፎርምና እንደ አከባቢያችን ተፈጥረዉ በነበረዉ ጸጥታ ችግር ለሶስት ዓመታት ያክል እስከ ወረዳና ቀበሌዎች ድረስ በዓሉ አለመከበሩን በመጠቆም በአከባቢዉ ተፈጥረዉ የነበረዉ የጸጥታ ችግር በእልህ አስጨራሽ ትግል በአሁኑ ሳዓት ቀጠናዉ ሙሉ በሙሉ ወደ ሰላም በመመለሱ እንደ ክልላችን አብሮነትና አንድነት በሚያጠናክር መልኩ በመተከል ዞን በግልገል በለስ ከተማ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር አቶ አብዮት በከኖ በመግለጫዉ ገልጿል ።

የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ በቡለን ወረዳ እና ከስሩ ባሉት ቀበሌዎች በዓሉን ሕብረ ብሕራዊ እንድነት በሚያጠናክር መልኩ በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በ04/2016 ዓ/ም የአራት አቢይ ኮሚቴዎች እቅድ በማጽደቅ ስራ ዉስጥ የተገባ ሲሆን በቀን 05/2016 ዓ/ም በተዋረድ ሁሉም የበዓሉ ዝግጅት ንዑስ ኮሚቴዎች አባላት እቅዳቸዉን ለአቢይ ኮሚቴዉ አቀርበዉ በመተቸት እና በማጽደቅ ወደ ስራ ዉስጥ የተገባ ሲሆን ከነገ 07/2016 ዓ/ም ጀምሮ የከተማ ጽዳት ስራዎች እና የቅስቀሳ ስራዎች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ አስተዳደሪዉ አቶ አብዮት በከኖ በመግለጫዉ ተናግረዋል ።

በመግለጫዉ በቀጣይ ቀናት በሚዘጋጀዉ ሰነድ ላይ ሙህራን ዉይይት በማድረግ ገንቢ ሐሳቦች እንዲያነሱ የማድረግ ስራዎች ፣ የደም ልገሳ ስራዎች እና በወረዳችን የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች በደማቅ ሁኔታ በዓሉን እንዲያከብሩ የማድረግ ስራዎች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪዉ አቶ አብዮት በከኖ ገልጿል ።

Subscribe
👇👇👇👇👇

https://www.youtube.com/channel/UCMeOTKKtNUctTZ7-13SQL_A

18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በግልገል በለስ ከተማ ለማክበር  የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን የመተከል ዞን አስተዳደር አስታወቀ)በሀገር አቀፍ ደረጃ  ለ18...
15/11/2023

18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በግልገል በለስ ከተማ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን የመተከል ዞን አስተዳደር አስታወቀ

)በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በግልገል በለስ ከተማ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን የመተከል ዞን አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋወያ አስታውቀዋል።

የዞኑ አስተዳዳሪ ይህን ያሉት የክልሉ ምክር ቤት የበዓሉ አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ ከዞኑ አመራሮችና ከከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር በዓሉን በማስመልከት ባደረጉት የጋራ ውይይት መድረክ ላይ ነው።
የዞኑ አስተዳደር ፣የግልገል በለስ ከተማ አስተዳደርና ሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት የተካተቱበት ዐቢይና ንዑስ ኮሚቴ ተቋቁሞ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመሩን ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።

ለእንግዶች ማረፊያ የሚሆኑ ሆቴሎችን፣የተለያዩ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን የመለየት ሥራ እየሰሩ መሆኑን የገለፁት አስተዳዳሪው የሎጅስቲክ እጥረት እንዳያጋጥም ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስተዋፅኦ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል ።
የክልሉ ምክር ቤት የንግድ ኢንዱስትሪ ከተማ ልማት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና የበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴ የሆኑት የተከበሩ አቶ ሉቅማን አብዱልቃድር በበኩላቸው በዓሉ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ባሻገር በዞኑ የመጣውን ሠላም ይበልጥ ለማረጋገጥ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።

የክልሉ ምክር ቤት የኢኮኖሚ ዘርፍ አማካሪና የበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴ የሆኑት ወይዘሮ አስካል አልቦሮ እንዳሉት በዓሉን በዞኑ ለማክበር እየተሰሩ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አበረታች መሆንኑን ገልፀው በዓሉ በክልሉ የሚገኙ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች መካከል በብዝኃነት ላይ የተመሰረተ አንድነት ሥር እንዲሰድና እንዲዳብር ትልቅ ጠቀሜታ ያለው ስለሆነ ያልተሰሩ ቀሪ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈፀሙ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ክልላዊ የማጠቃለያ በዓሉ "ብዝሀነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ ከቀጣይ ሳምንት በኋላ በግልገል በለስ ከተማ ህብረ ብሔራዊ አንድነትን በሚያጎላ መልኩ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እንደሚከበር በመድረኩ ተገልጿል።
በመጨረሻም በዓሉን ለማክበር በተሰሩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችና ያልተሰሩ ሥራዎች ቀጣይ በሚሰሩበት አግባብ ዙሪያ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ አስተያያትና ግብዓት ተሰጥቶ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ውይይቱ ተጠናቋል ፡፡

15/11/2023

Together We Can Change The World !!

15/11/2023

Together We Can Change The World !!

መተከል ቡለንበቡለን ወረዳ ለ18ኛ ጊዜ በሚከበረዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አስመልክቶ በተዘጋጀዉ መሪ እቅድ ዙሪያ ከወረዳ ሴ/መ/ቤት ሃላፊዎች ጋር ዉይይት ተደረገ።***********...
14/11/2023

መተከል ቡለን

በቡለን ወረዳ ለ18ኛ ጊዜ በሚከበረዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አስመልክቶ በተዘጋጀዉ መሪ እቅድ ዙሪያ ከወረዳ ሴ/መ/ቤት ሃላፊዎች ጋር ዉይይት ተደረገ።
***********

በቡለን ወረዳ ለ18ኛ ጊዜ በሚከበረዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አስመልክቶ በተዘጋጀዉ መሪ እቅድ ዙሪያ ከወረዳ ሴ/መ/ቤት ሃላፊዎች ጋር ዉይይት ተደረገ። ለ18ኛ ጊዜ በሚከበረዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን መሪ እቅድ ያቀረቡት የቡለን ወረዳ ምክር ቤት በጀትና ፋይናስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ታረቀኝ ዱፈራ ሲሆኑ በዓሉ የሚከበረዉ ,ቡዙሃንነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት ,በሚል መሪ ቃል በደማቅ ሁኔታ በወረዳችን እስከ ህዳር 15/2016 ዓ/ም እንደሚከበረና በክልል ደረጃ በመተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ በህዳር 22/2016 ዓ/ም ለሚከበረዉ የብሔር ብሔረሰብ ቀን ቀድመ ዝግጅት ማድረግ እንዳለበት በሰነዱ ገልጿል ።

ሰነድ አቀራቢዉ አቶ ታረቀኝ አክለዉም በወረዳ ስራዉን ለማሳካት የተቋቋመ አብይና ንዑስ ኮሚቴዎች ተግባራትና ሃላፊነታቸዉን በማቅረብ በተለይም በዓሉን በተፈለገ ደረጃ ለማክበር የገቢ አሰባሰብ ስራዎች እስከ ቀበሌዎች ድረስ ተጠናክረዉ መሰራት እንደሚያስፈልግ በመሪ እቅዱ ሰነድ አቀርበዋል ።

ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አስመልክቶ በተዘጋጀዉ መሪ እቅድ ዙሪያ የተደረገዉን ዉይይት መድረክ የመሩት የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አብዮት በከኖ እና የቦሮ ሽናሻ ብሔረሰብ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ የሆኑት ወ/ሮ ዳሳሽ ብፍቱ ሲሆኑ የተቋቋመዉ የበዓሉ አከባበር አስተባባሪ ንዑስ ኮሚቴ አባላት በዓሉን በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ሁሉም ኮሚቴዎች ከዛሬ ቀን ጀምሮ ወደ ስራ ዉስጥ በመግባት በማህበረሰብ ዉስጥ እና በትምህርት ቤቶች ላይ ሰፊ የንቅናቄ መድረክ በመፍጠርና በዓሉ በተለያዬ ስፖርታዊ ቲርዕት ፣ ተማሪዎች ስነ-ጹህፍና ግጥም በማቅረብ ፣ በወረዳችን የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች ክነት ቡድን አባላት የተለያዪ ባህላዊ ጭፈራዎች በማቅረብ እና የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን አጠናክረዉ በማስቀጠል በዓሉ እንድነት እና አብሮነትን በሚያሳይ መልኩ በደማቅ ሁኔታ እንዲከበር ንዑስ ኮሚቴዉ የበኩላቸዉን ድርሻ ዉስደዉ መስራት እንዳለባቸዉ አመራሮች በመድረኩ ገልጿል ።


የዉይይቱ ተሳታፊ የጽ/ቤት ሃላፊዎች በበኩላቸዉ በተደራጁት ንዑስ ኮሚቴ መሰረት ወደ ስራ ዉስጥ በቁርጠኝነት በመግባት በቡለን ወረዳ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን በስኬተማነት እንዲከበር የማድረግ ስራዎች በተቀመጠዉ መሪ እቅድ ተግባር መሰረት እንደሚሰሩ ገልጿል ።

በመጨረሻም የተደራጀዉ የበዓሉ አከባበር ንዑስ ኮሚቴዎች ከዛሬ ቀን ጀምረዉ የስራ እቅዳቸዉን በማዘጋጀት እና በሁሉም ቀበሌዎች ላይ ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ በመፈጠር በዓሉ በደማቅ ሁኔታ ተከብረዉ እንዲዉል የማድረግ ስራዎችን መስራት እንዳለባቸዉ በመጠቆም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች በዓል የሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ስለሆነ በወረዳችን የሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች የየራሳቸዉ ባህላዊ ጭፈራ በማሳየትና ለበዓሉ መሳካት የበኩላቸዉን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸዉ የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አብዮት በከኖ መልዕክታቸዉን በማስተላለፍ የእለቱ ዉይይት የተጠናቀቀ መሆኑን ተገልጿል ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሾች ያነሷቸው ዋና ዋና ሃሳቦች (ምዕራፍ 2) 1. የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያን በተመ...
14/11/2023

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሾች ያነሷቸው ዋና ዋና ሃሳቦች

(ምዕራፍ 2)
1. የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያን በተመለከተ
- ባለፉት አመስት ዓመታት በሰውሰራሽና የተፈጥሮ ችግሮች ውስጥ በማለፍ ትክክለኛ የኢኮኖሚ አቅጣጫ በመከተል የሀገሪቱ ጥቅል ዓመታዊ ምርት በእጥፍ ማሳደግ ተችሏል፡፡ የለውጡ መንግስት ሲመጣ የሀገሪቱ ዓመታዊ ጥቅል ምርት 84 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን፤ አሁን 164 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።የሰዎች የነፍስ ወከፍ ገቢ ከ882 ዶላር ወደ 1 ሺህ 549 ዶላር አድጓል፡፡
2. ግብርናን በተመለከተ
- በግብርናው ዘርፍ መንግስት በወሰዳቸው እርምጃወች ስር ነቀል ለውጥ አምጥቷል፡፡ ባለፈው ዓመት ብቻ 20 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት ከ600 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን፤ በዓመቱም ግብርናው የ6 ነጥብ 3 በመቶ እድገት አስመዝግቧል፡፡የዘንድሮው ዓመት 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬትን በበጋ መስኖ ስንዴ ለማልማት እየተሰራ ነው፡፡

3. የኢንዱስትሪ እድገትን በተመለከተ
- ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ከመጀመራችን በፊት የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም 47 በመቶ የነበረ ሲሆን በንቅናቄው አማካኝነት በአጭር ጊዜ ወደ 55 በመቶ ማሳደግ ተችሏል፡፡ ይህ ተስፋ ሰጪ ስራ ነው፡፡ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

4. የባንኮች የብድር አቅርቦትን በተመለከተ
- በአጠቃላይ ባንኮች ለብድር ካቀረቡት 547 ቢሊዮን ብር ውስጥ 86 በመቶው ለግሉ ዘርፍ የቀረበ ነው፡፡ ለግሉ ዘርፍ ከቀረበው ብድር ውስጥ አርሶ አደሩ 15 በመቶ ድርሻ አለው፡፡ ከዚህ ቀደም ከፍተኛው ብድር የሚወስደው መንግስት የነበረ ሲሆን ይህንን ትርጉም ባለው መልኩ መቀየር ተችሏል፡፡

5. የእዳ ጫናን በተመለከተ
- ኢትዮጵያ የአገር ውስጥን ጨምሮ ያለባት እዳ አሁን ላይ 31 በመቶ የደረሰ ሲሆን፤ ከዚህም ወስጥ የውጭ እዳችንን ወደ 14 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል፡፡ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታትም ከ10 በመቶ በታች ዝቅ ለማድረግ እንሰራለን::

6. የውጭ ምንዛሬን በተመለከተ
- በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት በአጠቃላይ 23 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ አግኝተናል፤ ከዚህም ውስጥ ከ7 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚሆነውን ከአገልግሎት ዘርፍ ያገኘነው ነው፡፡ ይህን ወደ 25 ቢሊዮን ብር ለማድረስ እየሰራን ነው፡፡

7. የዋጋ ግሽበትን በተመለከተ
- የዋጋ ግሽበት የኢትዮጵያ ችግር ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ችግር ነው፡፡ ዋጋ ግሽበቱ አምና 37 በመቶ ነበር:: ዘንድሮ መስከረም ወር ላይ ወደ 28 በመቶ ወርዷል፡፡ በዚህ ዓመት እና በሚቀጥለው ዓመት ይበልጥ ይወርዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የዋጋ ግሽበቱ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ወገኖቻቸን ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለመቀነስ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በዋናነት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል የዋጋ ንረቱን ለመቀነስ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተጨማሪም ድጎማና ለአቅመ ደካማ ዜጎች የምገባ አገልግሎት እየተሰጠ ነው፡፡ የእሁድ ገበያ ማዕከላትን ማስፋፋትም የዚሁ ስራ አካል ነው፡፡ በቀጣይም በከተሞች ያለውን የቤት ኪራይ ሁኔታ በህግ ለመግራት ይሰራል፡፡

8. የስራ ዕድል ፈጠራን በተመለከተ
- በተያዘው በጀት ዓመት ለ3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዜጎች ስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል፡፡ እስከ አሁን ባለው ሂደት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል፡፡በተጨማሪም በውጭ አገራት በህጋዊ መንግድ 100 ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ ዕድል እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡

9. ሌብነትን በተመለከተ
- ሌብነት ተቋም የሚያፈርስ ምስጥ ነው፡፡ ውስብስብ ችግር በመሆኑም ብርቱ ትግል ይጠይቃል፡፡ሌብነትን የሚጸየፍ ባህልን ከመገንባት ባሻገር ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ የሆነ ዲጂታል አሰራርን ማስፋት ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አኳያ ገቢ መሰብሰብን ጨምሮ 190 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ዲጂታል ማድረግ ተችሏል፡፡ ነገር ግን ሌብነትን የመታገሉ ስራ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡

10. አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በተመለከተ
- አርተፊሻል ኢንተለጀንስ የዓለምን ሁኔታ ይወስናል፡፡ ትውልድ ላይ አበክረን የምንሰራው፣ የምናስተምርው ጥፋቱንም ልማቱንም አስተካክለው መጠቀም እንዲችሉ ነው፡፡ ይህንን ለመረዳትም ቴክኖሎጂውን ማወቅ እና መጠቀም ይገባል፡፡ በተለያዩ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋማት አዳዲስ ፈጠራ ያላቸው ወጣቶች እየወጡ ነው፡፡ በቅርቡ የነበረው ውድድርም ይህንን ያመላከተ ነው፡፡ ይህ ነገር እየሰፋ መሄድ አለበት፡፡

11. ዲፕሎማሲን በተመለከተ
- የኢትዮጵያ የዲፕለማሲ ዋና መስፈሪያው ከሌሎች አገራት ጋር ተጋግዞና ተባብሮ መስራት ነው፡፡ ብሪክስ ከገባን በኋላ አንዳንድ ነገሮች ይደመጣሉ:: ብሪክስ የገባነው አንደኛውን ወገን ተተን አንደኛውን ወገን ደግፈን እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ይህ ትክክል አይደለም ፡፡ ወደ ብሪክስ የገባነውም የጋራ ትብብርን ለማጠናከር እንጂ የትኛውንም አገር ለመጉዳት አይደለም፡፡

12. ወደብን በሚመለከት
- የወደብ ጉዳይን አዲስ ጥያቄ አድርገው የሚያነሱ አሉ፤ የጎረቤት አገራትን ሉዓላዊነት ለመጉዳት የተነሳም አስመስለው የሚያቀርቡ አሉ፡፡ ነገር ግን የማንንም አገር ሉዓላዊነት የመጉዳትና የመውረር ፍላጎት የለንም፡፡ ኢትዮጵያ ያልተገባ ጥያቄ ከህግ ውጪ አልጠየቀችም፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ጎረቤት አገራት አንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎትም የላትም፡፡ ነገር ግን በህግና በቢዝነስ ማእቀፍ እንወያይ ነው ያልነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ እያደገ ነው፤ በመሆኑም ጉዳዩ ጊዜ ሳይሰጠው አሁኑኑ መፍትሄ ሊበጅለት ይገባል ብለን እናምናለን፤ ረሃብ፣ ችግር ሳይመጣ ተነጋግረን ህጋዊ መፍትሄ እናበጅ ነው ያልነው፡፡ ጥያቄውን ማንሳታችን እንደ ነውር ሊቆጠርም አይገባም፡፡
#የጠሚሩምላሾች

Office of the Prime Minister-Ethiopia

ምክር ቤቱ በነገው እለት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል፡፡6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር በተገኙበት ህዳር...
13/11/2023

ምክር ቤቱ በነገው እለት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል፡፡

6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር በተገኙበት ህዳር 04 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ ያካሂዳል፡፡
ምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራል መንግስት ባለስልጣናትን ለጥያቄ የመጥራትና የሕግ አስፈጻሚውን አካል አሠራር የመመርመር ሥልጣን እንዳለው በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ 17 ተደንግጓል፡፡

በዚህም መሰረት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት በሚካሄደው የምክር ቤቱ 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በመገኘት፤ ክብርት ፕሬዘዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ መስከረም 28 ቀን፣ 2016 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ያቀረቡትን የፌደራል መንግስቱን ዓመታዊ ዕቅድ የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ የሚሰጡ ይሁናል፡፡ በተጨማሪም ምክር ቤቱም የድጋፍ ሞሽኑን ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ናሁ ቴሌቭዥን ከምክር ቤቱ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

በነገው ዕለት በሚካሄደው የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ የሐይማኖት አባቶች ተወካዮች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ ተጠሪዎች፣ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሃገራት ዲፕሎማቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ አክሏል።

መልካም ዜናበመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ተመለሱ።  በዞኑ ማንዱራ ወረዳ በጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ  ታጠቂ...
12/11/2023

መልካም ዜና

በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጉህዴን ታጣቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ተመለሱ።

በዞኑ ማንዱራ ወረዳ በጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጠቂዎች የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ
ሰላም ተመልሰዋል።
በማንዱራ ወረዳ ታጣቂዎች የሰላምን አማራጭ ተቀብለው ሲገቡ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና የሀገር ሽማግሌዎች በገነተ ማሪያም ከተማ በመገኝት አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለሜሳ ዋውያ እነዚህ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭ በመቀበል ወደ ህብረተሰቡ መመለሳቸው የቀጠናውን ሰላም በዘላቂነት የተረጋጋ እንዲሆን ያደርገዋል ብለዋል።
አቶ ለሜሳ አክለው ተመላሾችን በተማሩበትና ፍላጎታቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት በተለያዩ የግብርና ዘርፎች ለማሰማራት መንግስት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በመኩሪያው ዚፋሃ እና በመኮነን ፋኖ በሚባሉ ግለሰቦች ሲመራ የነበረው የጉህዴን ታጣቂዎች ቡድን በተደረገው ከፍተኛ ጥረት ውይይት ተደረጎ የሰላም ስምምነት መደረጉ ተገልጿል።
ይህ ታጣቂ ሃይል በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ጫካ ውስጥ መቀመጫቸውን አድርገው በአዋሳኝ አካባቢዎች ስጋት ሲፈጥሩ የነበሩ ሲሆን በውይይት መምጣቸው ለህብረተሰቡ ሰላምና ልማት ለመግባት የሀገር ሽማግሌዎችና አመራረፐች በተገኙበት ከሰላም ተመላሾች ጋር በጉሙዝ ብሄረሰብ ባህላዊ የእርቅ ስነ ስርዓት አካሂደዋል።

የመንግሥት አመራሮች ሥልጠና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ የማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው። ከኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የመጡ የመንግሥት አመራሮች ሥልጠና በአሶሳ የማስጀመ...
10/11/2023

የመንግሥት አመራሮች ሥልጠና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ የማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።

ከኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የመጡ የመንግሥት አመራሮች ሥልጠና በአሶሳ የማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።
ከልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለሥልጠና ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገቡ መሪዎች አቀባባል እንደተደረገላቸው እና በክልሉ ዋና ከተማ አሶሳ የሚሰጠው ሥልጠናም የማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።
በመሪዎች ሥልጠና የማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ላይ የፖለቲካና ሪዕዬት ዘርፍ ም/ ኀላፊ ክቡር አቶ ሙሳ አህመድ፣ የብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ክቡር አቶ ይስሀቅ አብዱልቃድር እና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በየደረጃው የሚገኙ የሀገሪቱ የመንግሥት አመራሮች ለቀናት ሥልጠና እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

 #የተማሪዎች  #ምድባትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጠ ጥቅምት 21/2016 (አዲስ ዋልታ) ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ...
01/11/2023

#የተማሪዎች #ምድባ

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጠ
ጥቅምት 21/2016 (አዲስ ዋልታ) ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጠ፡፡
የሚኒስቴሩ ማብራሪያ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡
የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡-
1. 1000 ለሚሆኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፡- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል።
2. ውጤት፡- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡
3. የዩኒቨርሲቲ ምርጫ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፡፡ መረጃው የተሰበሰበው https://portal.etherenet.edu.et ላይ ነው፡፡
4. በተማሪዎች የተመረጡ ተቋማት ያላቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
5. ጾታ ፡- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ ተደርጓል፣
6. የትምህርት ቤት ተዋጽኦ ፡- የምደባ ስርዓቱ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚመደቡ ተማሪዎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ እንዲሆን ያግዛል፡፡ይህም ከአንድ ት/ቤት የወጡ ተማሪዎች በአንድ ዩኒቨርሲቲ ወይም ፕሮግራም ውስጥ እንዳይታጨቁ ይደርጋል፡፡
7. የውጤት ተዋጽኦ ፡-የምደባ ስርዓቱ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ታሳቢ ያረገ ሲሆን ይህም ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች አንድ ላይ እንዳይመደቡ በማድረግ የተለያየ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎችን ቀላቅሎ ለማስተማር ያግዛል፡፡
8. ወሊድን በተመለከተ፡- የምደባ ስርዓቱ እንደ ወሊድ ያሉ ልዩ ሁኔታዎችን ያማከለ ነው፡፡ በመሆኑም በመሰል ሁኔታ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመቀጠል የሚቸገሩ ከሆነ ትክክለኛ ለውጥና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡ መረጃዎቹ የተሰበሰቡት https//student.ethernet.edu.et ላይ ነው፡፡
•አስፈላጊ ማስረጃዎች: - ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የህጻናት የክትባት ካርድ
9. ትክክለኛ የሕክምና ቦርድ ማስረጃዎች፡- በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል፡፡
• አስፈላጊ ማስረጃዎች፡ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና ከህዝብ ጤና ተቋማት የህክምና ምስክር ወረቀት በሶስት ዶክተሮች እና በህክምና ዳይሬክተሩ የጸደቀ።
• የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et በመጠቀም ነው።
10. ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች (identical twins) ፡- በተማሪዎቹ መካከል ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች ካሉ የምደባ ስርዓቱ ከፍተኛ ነጥብ ያገኘው/ችው ተማሪ ከተመደበበት/ችበት የትምህርት ተቋም ቀሪው መንትያ ደግሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ ይመድባል። የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et ላይ ነው።
• አስፈላጊ ማስረጃዎች፡- ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የልደት የምስክር ወረቀት፣
11. የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች:- የምደባ ሲስተሙ የአካል ችግር ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምትውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል።
የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et በመጠቀም ነው።
• አስፈላጊ ማስረጃዎች፡ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የአካል ችግር ያለበትን የሰውነት ክፍል የሚያሳይ ፎቶግራፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
ማሳሰቢያ፣ ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርብ ተማሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከምደባ ውጭ የሚሆን መሆኑን እንገልጻለን፡፡

Follow Boro Media Service YouTube Channel
30/10/2023

Follow Boro Media Service YouTube Channel

Together We Can Change The World !!

 #መተከል  #ቡለንበቤ/ጉ/ክ/መ/ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር በአቶ  #መንግስቱ  #ላሎ እና በቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ በአቶ  #አብዮት  #በከኖ የተመራዉ የቡለን ወረዳ ...
29/10/2023

#መተከል #ቡለን

በቤ/ጉ/ክ/መ/ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር በአቶ #መንግስቱ #ላሎ እና በቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ በአቶ #አብዮት #በከኖ የተመራዉ የቡለን ወረዳ አመራር ሉዑካን ቡድን ከኤማንጅ ቀበሌ እስከ ባዶሬ ያለዉ በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰራዉን የመንገድ ስራ ጉብኘት አደረጉ ። በጉብኝቱ አመራሮች የልማቱ ተሳታፊ በመሆን ማህበረሰብን ያበረታቱ መሆናቸዉን ተገልጿል ።
*********

በቤ/ጉ/ክ/መ/ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር በአቶ መንግስቱ ላሎ እና በቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ በአቶ አብዮት በከኖ የተመራዉ የቡለን ወረዳ አመራር ሉዑካን ቡድን ከኤማንጅ ቀበሌ እስከ ባዶሬ ያለዉ በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰራዉን የመንገድ ስራ ጉብኘት አደረጉ ። በጉብኝቱ አመራሮች የልማቱ ተሳታፊ በመሆን ማህበረሰብን ያበረታቱ መሆናቸዉን ተገልጿል ።

የኤማንጅና ጎጃ ቀበሌ ዋና አስተዳደሪ አቶ አድሱ ኑቁሶ እንደገለጹት በወረዳችን ተፈጥሮ በነበረዉ ጸጥታ ችግር የነበረዉ መንገድ ተከታትለዉ ባለመጠገኑ መንገዱ የተበላሸ ሲሆን የማህበረሰብ እርስ በእርስ ያለዉን ግንኙነት ለማጠናከር በልማት መንገድን ያሰሩ መሆኑን በመጠቆም በቀጣይ በህብረተሰብ ታሳትፎ የልማት ስራዎች በመስራት ህዝቡ የመንግስት የልማት አጋርነትን የሚያሳይ መሆኑን ገልጿል ።

የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ አብዮት በከኖ እንደገለጽት በወረዳች ተፈጥረዉ በነበረዉ በጸጥታ ችግር የመንገድ መሰረተ ልማት ሳይሰራ በመቆየቱ ማህበረሰቡ የወረዳ መንግስት በማሽን እስከሚሰራ በማህበረሰብ ተሳትፎ ከኤማንጅ ቀበሌ ማዓከል እስከ ባዶሬ ቀበሌ ያለዉን መንገድ የመጠገንና የማጽዳት ስራዎች የሰሩ መሆናቸዉን መጠቆም በቀጣይም የቀበሌዉ ማህበረሰብ ከወረዳ መንግስት ጎን በመሆን የልማት አጋርነትን እንደሚያረጋግጡ በመግለጽ ሰላም በማህበረሰብ እጅ በመሆኑ ህዝቡ በአንድነት ለሰላም ዜብ በመቆም አሁን ያለዉን ሰላም በዘላቂነት ማስቀጠል እንዳለባቸዉ ገልጿል ።

የቤ/ጉ/ክ/መ/ ስነ መግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ መንግስቱ ላሎ እንደገለጹት በወረዳ ተፈጥረዉ በነበረዉ ጸጥታ ችግር የመንገድ መሰረተ ልማት ጥገና ባለመደረጉ መንገዶች የተበላሹ በመሆናቸዉ ማህበረሰብ መንግስት መንገድ እስከሚጠግን ደረስ ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር በዛሬ እለት ከኤማንጅ ቀበሌ ማዓከል እስከ ባዶሬ ቀበሌ ያለዉን መንገድ በማህበረሰብ ተሳትፎ የማጽዳትና የመጠገን ስራዎችን የሰሩ መሆናቸዉ በመግለጽ ማህበረሰብ የመጣዉ ሰላም ወደ ሃላ እንዳይመለስ አንድ ላይ በመደራጀት ሰላምን በዘላቂነት በማስቀጠል እና የአንድነትና የአብሮነት እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ልማት ስራዎችን ሰርተዉ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባቸዉ ገልጿል ።

 #የቤኒሻንጉል  #ጉሙዝ ክልል  #ከፍተኛ  #አመራሮች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎበኙ*******************የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ ከፍተኛ አመራሮች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ...
29/10/2023

#የቤኒሻንጉል #ጉሙዝ ክልል #ከፍተኛ #አመራሮች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎበኙ
*******************
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ ከፍተኛ አመራሮች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎበኙ።
የክልሉ መንግሥት የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያውን ሩብ ዓመት የአፈጻጸም ግምገማ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ - ጉባ አካሂዷል።
የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ከግምገማው ጎን ለጎን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።
አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ በኢትዮጵያዊያን አንድነት እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለሀገራችን ከሚሰጠው ግዙፍ የኃይል አቅርቦት ባሻገር ጠንካራ ሀገራዊ አንድነት የገነባንበት ፕሮጀክት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን የታላቁ ሕዳሴ ግድቡ ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ የሚያደርጉትን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል ።

 #የመደመር  #ፅንሰ  #ሀሳብ(ማን ይደምር? መቼ እንደመር? የት እንደመር? ባንደመርስ?)---------"ያለመደምርን ዳፋና ሰቆቃ በመፍረስ አፋፍ ላይ ሆነን ስላየነው፤ መደመርን አማራጭ የሌ...
29/10/2023

#የመደመር #ፅንሰ #ሀሳብ
(ማን ይደምር? መቼ እንደመር? የት እንደመር? ባንደመርስ?)
---------
"ያለመደምርን ዳፋና ሰቆቃ በመፍረስ አፋፍ ላይ ሆነን ስላየነው፤ መደመርን አማራጭ የሌለው ምርጫ አድርገን ማየቱ ተገቢ ነው!
መደመርንም የግዴታ ፖለቲካ ሳይሆን የውዴታ እንቅስቃሴ ብናደርገው ተደማሪዎች በፍጥነትም በቁጥርም ይበዛሉ!"
1. ማን ይደመር (Person) - መደመር ማንንም የሚያገልል ማንንም የሚያስገድድ ሂደት አይደለም። እርቅና ሰላምን የመረጠ፣ ፍቅርና አንድነትን የወደደ ብሎም ለነጻነትና እኩልነት፣ ለብልጽግናና ሰብዐዊነት የቆመና የቆረጠ ሁሉ ተደማሪ ሊሆን ይችላል። የመደመር ሜዳው ሰፊ፣ እድሉ ብዙ መንገዱም ልዩ ልዩ ነው። ስለዚህም አልፈልግም አሻፈረኝ ከሚልና ለግል ጥቅሙና አላማው ማስፈጸሚያ ፈልጎ ልደመር ከሚል በቀር የመደመር በር ለሁሉ ክፍት ነው። ህጻናንት በፍቅራቸው፣ ወጣቶች በብርታታቸው፣ ጎልማሶች በልምዳቸው አዛውንቶችም በጥበባቸው ሊደመሩ ይችላሉ። ነጋዴ በገንዘቡ፣ መምህር በእውቀቱ፣ ገበሬ በምርቱ፣ ዳኛ በፍትሁ፣ ከያኒ በጥበቡ ሊደመር ይችላል። አፋሩ ከጋንቤላው ጋር፣ ቤንሻንጉሉ ከሶማሌ፣ አማራው ከአደሬው፣ ትግራዋዩ ከሀድያ፣ ኦሮሞውም ከጉራጌው ቢደመር ተጠቃሚው ሁላችንም ደግሞም የምወዳት ሀገራችን ናት። ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከመበጣጠስ ቢጣመሩ፣ቤተ እምነቶች ልዩነታቸውን አክብረው በሀገር፣ በግብረገብና በዜጎቻችን ጉዳይ ላይ እጅ ለእጅ ቢያያዙ የማይደመር ላይኖር ነው። መደመር አግላይነትና ሌላውን ጥላሸት ከመቀባት የራቀ ነው።
2. መቼ እንደመር (Program) - የመደመር ሀሳብ በክስተትነቱ ያስደመመንን ያህል ተግባራዊነቱ ሂደትና አንዳንዴም እልህ አስጨራሽ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። ፈጥኖ በመደመር ስሌት ውስጥ በጭፍን ከመቀላቀል ተረድቶና ሁለንተናን ሰጥቶ ጊዜን ወስዶ መደመር የተሻለ ውጤት ሊኖረው ይችላል። የተደመሩ ሲበዙ መደመሩ እየቀለለ ይመጣል። መደመርን የግዴታ ፖለቲካ ሳይሆን የውዴታ እንቅስቃሴ ብናደርገው ተደማሪዎች በፍጥነትም በቁጥርም ሊበዙ ይችላሉ። ከላይ በመሪዎች ደረጃ፣ ከታችም በማህበረሰብ ደረጃ የመደመር ጽንሰ ሀሳብና ተግባራዊ መንገዶቹ እየተብራሩ ሲመጡ መደመር ሁሉንም የሚስብ ማግኔት ይሆናል። ዛሬ ያለው የመደመር ጅረቶች ተዋህደው ትልቁን ወንዝ የሚፈጥሩበት ጊዜ እስኪመጣ ግን ትዕግስትና የማያቋርጥ ጥረት ይጠይቃል።
3. የት እንደመር (Platform) - በመደመር የእመርታዊ ለውጥ ሀሳብ ውስጥ አንዱ የተደማሪዎች ፈተናና መደናገር ሊሆን የሚችለው ምኑ ላይ ወይም ከማን ጋር ነው የምደመረው የሚለው ሊሆን ይችላል። እራስን አጽድቆና አትልቆ ሌላውን ደግሞ አኮስሶና አዋድቆ የማየት ችግር ስላለብን ነው። ለራሳችን ካለን በጎነትና መልካም እይታ ቀንሰን ለሌሎች በመስጠት፣ በሌሎች ላይ ካለን አብጥልጥሎና አብጠርጥሮ የመፈተሽ ልምድ ደግሞ ቀንሰን በራሳችን ላይ ብንተገብረው ከማንም ጋር ለመደመር ዝግ አንሆንም ነበር። ከሌብነትና ከዘቀጠ ስራ ጋር መደመር መቀነስ ነው። ከጥላቻና ከጥፋት ጋር መደመር መውረድ ነው። ይቅርታና እርቅ፣ ሰላምና አንድነት፣ በጎነትና ቅንነት፣ መልካም ስራና ልማት፣ ፍቅርና እኩልነት መግባቢያ ቋንቋና የመደመር ልኬቶች በሆኑበት ቦታ ሁሉ መደመር ያስፈልጋል። በሀገራችን የተፈጠሩትን የመከፋፈል ሰው ሰራሽ ድንበሮች ለማፍረስ፣ በቡድን አስተሳሰብና በስማ በለው የተፈጠሩ የጅምላ ጥላቻና ፍረጃን ለማስቀረት በተጀመሩ እንቅስቃሴዎችና ጅማሮዎች ሁሉ መተባበር ትክክለኛው የመደመር ቦታ ነው። የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና የስራ ፈጠራ ተግባራትን መደገፍም ሆነ መሳተፍ ትክክለኛው የመደመር ቦታ ነው። መጪውን ትውልድ አንድ ጥልቅ አገራዊ ፍቅር እንዲኖረውና የሰውን ሁሉ እኩልነትና የሰብዕና ልዕልና ማስተማርና ማቀራረብ ባለበት ቦታ ድርሻን መወጣት ትክክለኛው የመደምር ቦታ ነው። ያለንን የስራ ባህል ለመለወጥ፣ የንጽህናና አካባቢን የመንከባከብ ልምድ ለማዳበር በሚደረጉ ተግባራት መሳተፍና የበኩልን እገዛ ማድረግ የመደመር ከፍታ ነው።
4. ባንደመርስ (Problems) - መደመር የግልም ሆነ የቡድን ምርጫችን መሆኑ እሙን ነው። ሌላው አማራጭ ደግሞ አለመደመር ሲሆን ያለመደምርን ዳፋና ሰቆቃ በመፍረስ አፋፍ ላይ ሆነን ስላየነው መደመርን አማራጭ የሌለው ምርጫ አድርገን ማየቱ ተገቢ ነው። ከይቅርታ ይልቅ ቂም፣ ከእርቅ ይልቅ በቀል፣ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻና ፍርሃት፣ ከሰላምም ይልቅ ጠብ፣ ግጭትና ጦርነት በመደመርና ባለመደመር መሀል ያለውን ልዩነት የሚያሳዩ የምርጫዎቻችን መንገዶች ናቸው። ውጤታችውም እንደመንገዱ ሁሉ ብርሃን ከጨለማ እንደሚለይ የተለያዩ ናቸው። ይህም ያለመደመር ውጤቶች ከነጻነት ይልቅ የሰብአዊ መብት ጥሰትና የፍርሃት ኑሮና ሽሽት፣ ከብልጽግና ይልቅ ድህነትና ጉስቁልና፣ ከእኩልነት ይልቅ ኢፍትሃዊነት፣ አድልዎና ቡድንተኝነት ይሆናል። ይህም ወደማያቋርጥ መከፋፈልና መፈራረስ የሚያመጣ ጎዳና ሊሆን ይችላል። የመምረጥን ነጻነትና መብትን ባለመደመር ለመግለጽ መሞከር ሌላውን ሳይሆን ራስንም ወደ ጥፋት የሚወስድ አፍራሽ ጎዳና ነው።

ቤኒሻንጉልበክልሉ የሠላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች የተሻለ ውጤት ታይቶባቸዋል-ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  አቶ አሻድሊ ሀሰንና የክ...
29/10/2023

ቤኒሻንጉል

በክልሉ የሠላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች የተሻለ ውጤት ታይቶባቸዋል-ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንና የክልሉ ካቢኔ አባላት በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመገኘት በክልሉ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተከናወኑ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ገምግመዋል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ቀልቤሳ ኦልጅራ የክልሉን የሶስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡የቀረበው ሪፖርት እንደሚያሳየው በክልሉ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን የተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤት አሳይተዋል፡፡

በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እና በተለያዩ የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና መልካም አስተዳደራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅደው የተከናወኑ ስራዎችም ተስፋ ሰጪ ውጤት እንደታየባቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በሩብ ዓመቱ በተከናወነው ቅንጅታዊ የገቢ አሰባሰብ ስራ 897 ሚሊዮን 150 ሺህ ሁለት መቶ ስምንት ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 777 ሚሊዮን 754 ሺህ ስድስ መቶ ሃያ አራት ብር መሰብሰቡም ተገልጿል፡፡ይሁን እንጂ ክልሉ ወርቅን ጨምሮ በማዕዲን ሀብት የበለፀገ ቢሆንም ከዘርፉ የሚጠበቀውን ውጤት ከማግኘት አንጻር ክፍተቶች መኖራቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

መተከል ድባጢ በመተከል ዞን ድባጢ ወረዳ የሰላም ተመላሾች  በ66 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም የተለያዩ ሰብሎችን እያለሙ ነው።  በድባጢ ወረዳ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ልማ...
26/10/2023

መተከል ድባጢ

በመተከል ዞን ድባጢ ወረዳ የሰላም ተመላሾች በ66 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም የተለያዩ ሰብሎችን እያለሙ ነው።

በድባጢ ወረዳ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ልማት የገቡ ወጣቶች በግብርና ስራ ተሰማርተው እያለሙ ነው።
የክልል እና የወረዳ አመራሮች በድባጢ ወረዳ በሞጋ ቀበሌ በሰላም ተመላሾች አማካኝነት በኩታ ገጠም የለሙ የአኩሬ አተርና የበቆሎ ሰብሎችን ጉብኝተዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር መለሰ በየነ፤የሰላም ተመላሾችን ፍላጎትና አቅም መሰረት ባደረገ መልኩ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ የክልል መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በወረዳው 36 የሚሆኑ የሰላም ተመላሾች 66 ሄክታር መሬት በአኩሬ አተር፣በበቆሎና በጤፍ ሰብሎችን እያለሙ መሆኑን የድባጢ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አንተነህ ንጉሴ ተናግረዋል።
በወረዳው የተገኘውን ሰላም በመጠቀም የሰላም ተመላሾችን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማሰማራት አበረታች ስራዎችን እያከናወኑ መሆናቸውን አቶ አንተነህ አክለው ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የሰላም ተመላሾችን ወደ ስራ ለማስገባት 28 ማህበራትን በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለማሰማራት ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
ወጣት ሃይሌ አብዲሳ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል በሞጋ ቀበሌ ከጓደኞቹ ጋር በመደራጀት የአኩሬ አተር ሰብልን በኩታ ገጠም በማልማት ላይ ይገኛል።
በጦርነት የሚመጣ ልማት አለመኖሩን በመረዳት በሞጋ ቀበሌ 9 ሆነው በመደራጀት በ12 ሄክታር መሬት ላይ በአኩሪ አተር 17 ሄክታር መሬት ላይ ደግሞ የበቆሎ ሰብሎችን እያለሙ መሆኑን ወጣት ሃይሌ ገልጿል።
በቀጣይ የጀመሩትን ስራ አጠናክረው ላመስቀጠል መንግስት የግብዓትና የትራክተር ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ተናግረዋል።

26/10/2023
ኢትዮጵያኢትዮጵያ በኃይል እና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው አንዳች ነገር የለም -የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)116ኛውን የሠራዊት ቀን ንግግር ያደረጉት...
26/10/2023

ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ በኃይል እና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው አንዳች ነገር የለም -የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

116ኛውን የሠራዊት ቀን ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በኃይል እና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው አንዳች ነገር የለም ብለዋል፡፡
ከቅርብ ከጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ ውይይት ያስፈልጋታል ስትል ወራራ ሊካሄድ ይችላል የሚል ስጋት ይደመጣል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመላው ኢትዮጵያውያን እና ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ማረጋገጥ የሚፈልገው ኢትዮጵያ በኃይል እና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው አንዳች ነገር የለም ብለዋል፡፡
ለጋራ ጥቅም ለጋራ ዕድገት ለጋራ ብልፅግና ሁሉም አሸናፊ በሚሆንበት መንገድ የጋራ ጥቅማችንን ለማስከበር እንሰራለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
በወንድሞቻችን ላይ ቃታ የማንስብ መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በንግግራቸው፡፡
116ኛውን የሠራዊት ቀን "በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር ቆይቷል።
በዛሬው ዕለት ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተከበረ ይገኛል።

 #ትግራይየኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ስራ ለመጀመር የሚያስችለውን የመጀመሪያ ውይይት በመቀሌ ከተማ አካሄደ፡፡ በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የተመራው...
26/10/2023

#ትግራይ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ስራ ለመጀመር የሚያስችለውን የመጀመሪያ ውይይት በመቀሌ ከተማ አካሄደ፡፡
በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ የተመራውና ሌሎች 4 ኮሚሽነሮችን ያካተተው የኮሚሽኑ ልዑካን ቡድን ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ መቀሌ ጉዞውን አድርጎ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል፡፡
ኮሚሽኑን ወክሎ የተጓዘው ቡድን ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እና ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተወካዮች ጋር ተገናኝቶ የተወያየ ሲሆን በቀጣይ በክልሉ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶችን ለመተግበር የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ አሰራር ኮሚሽኑ መተግበር እንደሚገባው ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
በውይይቶቹም ላይ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ኮሚሽኑ እስካሁን ስላከናወናቸው ተግባራት ገላፃ አድርገው ከእነዚህ ባለድርሻ አካላት ሊደረግላቸው የሚገቡ ትብብሮችን ጠቅሰዋል፡፡
በቀጣይም ኮሚሽኑ በክልሉ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ደረጃ በደረጃ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ማከናወን እንደሚገባው በውይይቱ የተመላከተ ሲሆን የክልሉ መንግስት ኮሚሽኑ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

ቤኒሻንጉል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ የሳታላይት ቴሌቪዥን የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት መደበኛ ስርጭት በይፋ ጀመረ*****************የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ...
25/10/2023

ቤኒሻንጉል

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ የሳታላይት ቴሌቪዥን የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት መደበኛ ስርጭት በይፋ ጀመረ
*****************
የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ የሳታላይት ቴሌቪዥን መደበኛ ስርጭትን በይፋ አስጀምረዋል፡፡
የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ዶክተር ተመስገን ዲሳሳ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ የሳታላይት ቴሌቪዥን መደበኛ ስርጭት መጀመሩን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የክልሉ ቴሌቪዥን መደበኛ ስርጭት መጀመሩ ህዝብንና መንግስትን ይበልጥ የሚያቀራርብ ነው ብለዋል፡፡
መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለመስጠት ዕድል የሚሰጥ ከመሆኑም ባለፈ በሁሉም ዘርፎች ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ ያግዛልም ብለዋል፡፡
በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማስፈን በሚሰራው ስራ የሳታላይት ቴሌቪዥኑ ሚና የላቀ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
ሁሉም የክልሉ ህዝብና ተቋማት ለሚዲያው አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰጡም አሳስበዋል፡፡
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው ክልሉ ከተቋቋመበት ወቅት ጀምሮ የክልሉ ሚዲያ እውን እንዲሁን በርካታ ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን አስታውቀዋል፡፡
ክልሉ የራሱ ቴሌቪዥን ጣቢያ ባለመኖሩ ሳቢያ ዝቅተኛ የነበረው የክልሉ ህዝብ መረጃ የማግኜት ዕድሉ አሁን ላይ ምላሽ መሰጠቱን ገልፀዋል፡፡
ተቋሙ በሰው ኃይል፣ በሎጅስቲክስና በሌሎች ግብዓቶች እንዲሟላ የክልሉ መንግስት ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማጠናከር ይሰራል ብለዋል፡፡
የሚዲያው የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ኢስሃቅ አብዱልቃድር እንዳሉት ደግሞ የክልሉ ማህበረሰብ በጉጉት ሲጠብቅ የነበረው የሳታላይ ቴሌቪዥን እውን በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
7 ቋንቋዎች የሚተላለፉበት ብዝኃነት የሚንፀበረቅበት ሚዲያ መሆኑን የገለፁት ቦርድ ሰብሳቢው ሚዲያው አሁን ካለበት ደረጃ ለመድረስ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ዓባይ ለሁለት ቀናት የሚቆየው 3ኛው ዙር የዓባይ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር በካይሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ ደንቦችና መመሪያዎች ዙሪያ...
24/10/2023

ዓባይ

ለሁለት ቀናት የሚቆየው 3ኛው ዙር የዓባይ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር በካይሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ ደንቦችና መመሪያዎች ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መካከል የሚደረገው 3ኛው ዙር የሦስትዮሽ ድርድር በግብጽ መዲና ካይሮ የሁለተኛ ቀን ምክክር እየተካሄደ ነው።
በድርድሩ ባልተፈቱ የቴክኒካል እና የሕግ ማእቀፍ ጉዳዮች የተሻለ ውጤት ላይ ለመድረስ ትኩረት እንደሚያደርግ አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ በማህበራዊ ትስሰር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል፡፡
አምባሳደር ስለሺ፣ ተደራዳሪዎቹ ቀደም ሲል ባካሄዷቸው ድርድሮች ባልተፈቱ "የቴክኒካል" እና "የሕግ ማዕቀፍ" ጉዳዮች ላይ የተሻለ ውጤት ላይ ለመድረስ ትኩረት አድርገው እንደሚደራደሩ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በ2015ቱ የመርኾዎች መግለጫ ስምምነትንና ፍትሃዊና ምክንያታዊ የኾነ የውሃ አጠቃቀም መርኾችን መሠረት ያደረገ ውጤት ላይ ለመድረስ ጥረት እንደምታደርግም ስለሺ አረጋግጠዋል።
ከዚህ ቀደም በነሃሴ ወር 2015 ላይ የግድቡ ተደራዳሪ የቴክኒክ ባለሙያዎች በግብጽ ካይሮ ተገናኝተው የተወያዩ ሲሆን፤ ኹለተኛው ዙር የቴክኒክ ባለሙያዎች ውይይት ደግሞ በመስከረም ወር በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወሳል፡፡
በዚህም መሰረት በኹለተኛው ዙር ውይይት ላይ ሦስተኛው የአገራቱ ድርድር ጥቅምት ወር ላይ በግብጽ ካይሮ እንዲካሄድ ስምምነት ላይ መደረሱን ተከትሎ፤ ድርድሩ በትላንትናው እለት በግብጽ ዋና ከተማ ካይሮ ተጀምሯል፡፡

23/10/2023

ታላቁ ትርክት -በቅርብ ቀን
ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም

ቤኒሻጉል ካማሺ   የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ወለጋ ዞን እና በቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ከካማሺ ዞን አመራሮች ጋር ተወያዩ።ውይይቱ በሁለቱ ዞኖች መካከል ያለውን የህዝብ...
21/10/2023

ቤኒሻጉል ካማሺ

የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ከምዕራብ ወለጋ ዞን እና በቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ከካማሺ ዞን አመራሮች ጋር ተወያዩ።
ውይይቱ በሁለቱ ዞኖች መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። በሸኔ ምክንያት ችግር ገጥሞት የነበረው የሁለቱን ህዝቦች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት በአጭር ጊዜ ወደነበረበት መመለስ እንደሚገባ ውይይቱን የመሩት የምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ብርጋዲየር ጄኔራል አማረ ባህታ ተናግረዋል።
በሁሉም ዘርፍ የምንገኝ አመራሮች ከእያንዳንዳችን የሚጠበቀውን ሁሉ በሃላፊነት መንፈስ መወጣት ከቻልን የማንፈታው ችግር አይኖርም ያሉት ጄኔራል መኮንኑ፤ በየተቋሙ ያሉ አመራሮች ሊወጡት የሚገባቸውን የስራ ድርሻ ቆጥረው በመረከብ ወደ ተጨባጭ የተግባር ስራ መግባት እንደሚገባቸውም በአፅንኦት ገልፀዋል።
ከሁሉም በፊት የተቋረጡ መሰረተ ልማቶች ለህዝብ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል መሥራት እንደሚገባ የተናገሩት ብርጋዲየር ጄኔራል አማረ ባህታ በየትኛውም አካባቢ የሚኖረው ህዝብ በሰላም ወጥቶ በሰላም መግባት እንዲችልና ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ እንዲሠራ ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ብለዋል።
(FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት )

የኢሬቻ  በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ላይ መካሄድ ጀመረ በኦሮሞ ብሄረሰብና በኢትዮጲያ ህዝብ በስፋት የሚታወቀው   የኢሬቻ በዓል በዚህ ሰዓት  በአሶሳ ከተማ መካሄድ ጀመረ ።...
21/10/2023

የኢሬቻ በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ላይ መካሄድ ጀመረ

በኦሮሞ ብሄረሰብና በኢትዮጲያ ህዝብ በስፋት የሚታወቀው የኢሬቻ በዓል በዚህ ሰዓት በአሶሳ ከተማ መካሄድ ጀመረ ።
በዓሉ የብሄረሰቡ አባላቶች በሚኖሩበት አከባቢ በየ አመቱ በድምቀት የሚከበረው ይህ ታላቅ በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ላይ በአሁኑ ሰአት በፓናል ውይይት መካሄድ ተጀምሯል።
በበአሉም የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጌታሁን አብዲሳን ጨምሮ በርካታ የክልል ከፍተኛ አመራሮች ፣ አባ ገዳዎች ፣ አዳ ስንቄዎች፣ የብሄረሰቡ አባላቶች ሌሎች ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል።
በዓሉም እስከ 3 ቀን በተለያዩ ኩነቶች እንደሚከበር ታውቋል።

ቤኒሻንጉል"በልማት የታጀበ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና እኩልነት መፍጠር ይገባናል"፤  የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አፈጉባኤ የተከበሩ  ተመስገን ዲሳሳ(ዶ/ር)።(ዜና ምክርቤት፤ ጥቅምት 9/2016)...
20/10/2023

ቤኒሻንጉል

"በልማት የታጀበ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና እኩልነት መፍጠር ይገባናል"፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አፈጉባኤ የተከበሩ ተመስገን ዲሳሳ(ዶ/ር)።
(ዜና ምክርቤት፤ ጥቅምት 9/2016)ዓ.ም፤ በልማት የታጀበ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና እኩልነት መፍጠር ይገባናል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አፈጉባኤ የተከበሩ ዶ/ር ተመስገን ዲሳሳ ገለፁ።
18ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል መሪ ዕቅድ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዓብይ ኮሚቴ የመጀመሪያውን ውይይት አድርጓል።
በመሪ ዕቅዱ ላይ የኮሚቴው ተግባርና ሀላፊነት ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በዓብይ ኮሚቴው ሥር ንዑሳን ኮሚቴዎችም ተዋቅረዋል።
ውይይቱን የመሩት የክልሉ አፈጉባኤ የተከበሩ ተመስገን ዲሳሳ(ዶር) እንደገለፁት የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ማክበር የራስህን ባህልና ወግ በማሳደግ እና የሌላውንም በማወቅ ሕብረ ብሔራዊነትን ለማጠናከር ጥቅሙ ብዙ ነው ብለዋል።
በዓሉ እንደ ሀገር ከበፊቱ በተሻለ መልኩ እንዲከበር እንቅስቃሴ እየተደረገ ስለሆነ ኮሚቴውም ዕቅዱን በመውሰድ በክልል ደረጃም በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ክቡር አፈጉባዔው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የበዓሉ ኮሚቴዎችም መሪ ዕቅዱ የሚያሰራ እንደሆነና እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ የበዓሉ ፋይዳና አከባበር ግንዛቤ ሊፈጠር እንደሚገባ በውይውቱ ሀሳብ ሰጥተው ዕቅዱን በመውሰድ ወደ ሥራ እንደሚገቡ መግባባት ላይ ደርሰዋል።
18ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል እንደ ሀገር በሶማሌ ክልል " ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ሕዳር 29/2016/ዓ.ም ይከበራል።

(የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ጽ/ቤት)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቻይና የቼንግዱ ከተማ ያደረጉት ጉብኝት (በፎቶ)ENA
20/10/2023

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቻይና የቼንግዱ ከተማ ያደረጉት ጉብኝት (በፎቶ)ENA

 #እርምጃ  #ወስደናል #በቤኒሻንጉል  #ጉሙዝ  #ክልል በህገወጥ የንግድ ሥራ ላይ በተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደበቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገወጥ የንግድ ሥ...
19/10/2023

#እርምጃ #ወስደናል

#በቤኒሻንጉል #ጉሙዝ #ክልል በህገወጥ የንግድ ሥራ ላይ በተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገወጥ የንግድ ሥራ ላይ በተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የንግድና ገበያ ልማት ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ ታሪኩ ኩመራ፣ ቢሮው ዛሬ ለ5 ወር የሚቆይ የኑሮ ውድነት ቅነሳ ዕቅድ አዘጋጅቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።
መንግስት የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ በንግድ ሥርዓቱ ውስጥ የሚስተዋለውን የህገወጥ ደላሎች እንቅስቃሴና የንግድ ሰንሰለት ለመቆጣጠር የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።
እስካሁን በተከናወኑ የቁጥጥር ሥራዎች በህገወጥ የንግድ ሥራ ላይ በተሳተፉ ከ1 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን አቶ ታሪኩ ገልጸዋል።(የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ)

 #መተከል  #ቡለን #የቡለን  #ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም 1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ አደረገ ። የቡለን ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም 1ኛ ሩብ...
19/10/2023

#መተከል #ቡለን

#የቡለን #ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም 1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ አደረገ ።

የቡለን ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም 1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ አደረገ ። የቡለን አስተዳደር በ2016 ዓ/ም በአንደኛ ሩብ ዓመት የህዝብ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ሰፊ የህዝብ ለህዝብ ግንኝነት ስራዎች እንደሰሩ ምቹ ሁኔታዎችን በማመቻቸት አበረታች ስራዎችን የሰራ ሲሆን በተለይም የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበርን በማስተባበር ለአቅመ ደካማ ማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎችን እንዱያደርጉና የወረዳ መንግስት እና የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር የማህበረሰብ አጋርነትን እንዲያሳዩ አበረታች ስራዎች በጽ/ቤቱ በኩል መሰራቱን በሪፖርት ግምገማዉ ተገልጿል ።

የቡለን ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ለወረዳ ካቢኔ የሚቀርቡ አጀንዳችን በመቅረጽና ለዉሳኔ በማቅረብ የወረዳ ካቢኔ ዉሳኔዎችን ለሚመለከታቸዉ አካላት በማሰራጨት ዉጤታማ ስራዎችን የሰራ ሲሆን አቤቱታዎች በመያዝ ወደ አስተዳደር ምክር ቤት የሚመጡ ባለጉዳዮች ያለምንም መጉላላት እንዲስተናገዱ ማድረጉን በመጠቆም የወረዳችን የባለሙያዎች የኮምፒዉተር ክህሎት ለማሳደግ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመተባበር በየሰክተር መ/ቤት ለተወጣጡ ባለሙያዎች የኮፒዉተር ስልጠና በመስጠት የቡለን ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት በሩብ አመቱ ዉጤታማ ስራዎችን መስራቱ የቡለን ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ #አሰፋ #ኤሾ ገልጿል ።

19/10/2023

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ ከተማ የሚገኘው የሌጲስ ኢኮ ቱሪዝም መንደር በዓለም ድንቅ የቱሪዝም መንደርነት የእውቅና ሽልማት አግኝቷል፤

ተጠንተው ይቅረቡለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዝቅተኛ መሆን ምክንያቶች ተጠንተው ይቅረቡ- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት ...
18/10/2023

ተጠንተው ይቅረቡ

ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዝቅተኛ መሆን ምክንያቶች ተጠንተው ይቅረቡ- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ።
በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2016 እቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ቀደም ሲል ሲሰጡ የነበሩ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤቶች የተማሪዎችን ትክክለኛ ችሎታ ያሳዩ አልነበሩም ብለዋል።
የፈተና አሰጣጡን በመቀየር የተመዘገበው የተማሪዎች ውጤት በዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ ችግሮች ማሳያ መሆናቸውን ጠቁመው ለዚህም ከወላጆች ጀምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተጠያቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትምህርት ጥራት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰው እየተካሄዱ ያሉ የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ መርኃ ግብሮችና የመምህራን አቅም ግንባታ ሥራዎችን ለአብነት አንስተዋል።
በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ ሚኒስቴሩ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መምጣት ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ አይቻልም ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር የማስተማርና ፈተና የማስፈተን ተልዕኮ ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተቋም ለተገኘው ውጤት ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባልም ነው ያሉት።
ትምህርት ሚኒስቴርን ጨምሮ ተጠሪ ተቋማትና የትምህርቱ ዘርፍ ተዋንያን ለውጤቱ የነበራቸው ድርሻ ተለይቶ መቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል።
ለተማሪዎች ዝቅተኛ ውጤት ማጣት ምክንያት የሆኑ ሌሎች ችግሮችም በጥናት ተለይተው ሊቀርቡ እንደሚገባም ዶክተር ነገሪ ተናግረዋል።

18/10/2023


#ዜና #ትንታኔ🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

18/10/2023

የዘንድሮ ጋሪ ዎሮ በአሶሳ

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Boro Media Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share