24/08/2022
#ሰበር ዜና
በፌደራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል ዳግም ግጭት ተቀሰቀሰ።
# # # # # # # # # #
ከፌደራል መንግሥት የተገኘ መረጃ እንደሚጠቁመው የጦርነት ጉሰማውን የጀመረው ህወሓት ነው ። በተደጋጋሚ የሚያደርጋቸው ትንኮሳዎች ውጤት ስላላመጡለት ጦርነቱን ፈልጎታል። እንደ
ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ለመጮህ እየሞከረ ነው ብሏል።
ኢትዮጵያ ለሰላም ሁሉንም አድርጋለች። ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለመደራደር መንግሥት ወስኖ ተግባራዊ እንቅስቃሴ አድርጓል።
ሕወሓት ከጦርነት እንጂ ከሰላም ስለማያተርፍ የአፍሪካ ኅብረትን
አልተቀበለም፣ ተደራዳሪዎቹን አላሳወቀም፣ ቅድመ ሁኔታ ይደረድራል። (መጀመሪያ 11 ቀጥሎ 5 ቀጥሎ 3)፣ ተኩስ አቁም ፈርሷል ብሎ አውጇል፣ ተደጋጋሚ ትንኮሳ በምዕራብና ደቡብ ግንባር ፈጽሟል ሲል ከሷል።
ኢትዮጵያ ለሰላማዊ መፍትሔ አሁንም ቁርጠኛ ናት። ከተጠቃች ግን ሁሉንም ዐቅም ትጠቀማለች ሲል ለጉዳዩ ቀርበት ያላቸው ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የትግራይ ሰራዊት ወታደራዊ ኮማንድ በሰጠው መግለጫ በፌደራል መንግስት ጦር ተወርሬአለሁ ብሏል።
በደቡባዊ ግምባር በዛ ግምባር ከቆዩትና ከሌሎች አከባቢዎች ያሰባሰባቸው የአማራ ልዩ ሀይል ክፍለጦሮች፤የወሎ ፋኖ እና ሚሊሻዎችን ባለፉት አምስት ቀናት እያዘጋጀ ከቆዬ በኋላ የፌደራል መከላከያ ሀይል አካላት የሆኑት 6ተኛ እና 8ተኛ እግረኛ እዞችና የ2ተኛ 6ተኛ እና 8ተኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦሮችን ጨምሮ ዛሬ ነሓሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም ከማለዳው 11 ሰዓት ጀምሮ በጩቤበር፤ ጃኖራ፤ ጉባጋላ እና ያሎው አቅጣጫዎች ወደ አላማጣ ባላና ብሶበር ሰፊ የማጥቃት ዘመቻ ጀምረ