Ibnu murad

Ibnu murad የኢትዮጵያዊያን ፍላጐትና እውነታው?

22/11/2020

የኢትዮጵያ ባንድራ ሰማይ ላይ አለ እሚል አዝማሪ ባለባት ሀገር
ፈጣሪ የኛ ዘር ነው የኛ ሰፈር ልጅ ነው የሚል ዘግናኝ አስተሳሰብ ያላቸው ማህበረሰብ ያሉባት ሀገር
መሪዋ ከፈጣሪ ጋር ግኑኝነት አለኝ እያለ ሲቀጣጥፍ ተከታይ ባገኘባት ሀገር
በ አመት 365 ቀናት ባዕል ተብሉ እማይሰራበት ሀገር
መፅሀፍ ቅዱስ መኖሩን እንጅ ምን እንደተፃፈበት ማንበብ እማይቻልበት ሀገር (ካነበቡ) የተፃፈው ከልብ ወለዶች ጋ ስለሚጋጭ ) በነዚህ አስተሳሰብ ውስጥ ያለ ሰው ለሀገሬ ሰላም እታገላለው ሀገሬ ለምን አልበለፀገችም ሲል አያስቅም? እረ ባካችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን የምር ኖረን እንሙት ለ ነፍሳችንም እንዘንላት ለምን 1+1 = 11 ነው እኛ ያለንው ካልሆነ እንላለን ለማንኛውም ራሳችሁን በትክክለኛው የፈጣሪ ቃል መዝኑ

19/11/2020

ሽብርተኝነትና ሙስሊሞች‼️
===================
✍ A German Muslim scholar when he was asked about TERRORISM and Islam.
አንድ ጀርመናዊ ሙስሊም ምሁር ስለ ሽብርተኝነትና እስልምና በተጠየቀ ጊዜ፤ He said, እንዲህ አለ:
*
❶) "Who started the first world war? Not Muslims!!
የመጀመሪያውን የዓለም ጦርነት የጀመረው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❷) Who started the second world war? Not Muslims!!
የሁለተኛውን የዓለም ጦርነት የጀመረው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❸) Who killed 6 million Jews in the Holocaust ? Not Muslims.
በሆሎካስት 6 ሚሊዮን አይሁዳዊያንን የገደለው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❹) Who killed about 20 millions of Aborigines in Australia ? Not Muslims!!
በአውስትራሊያ 20 ሚሊዮን ገደማ አቦርጅኖችን የገደለው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❺) Who sent the nuclear bombs of Hiroshima and Nagasaki? Not Muslims!!
ወደ ሒሮሽማና ናጋሳኪ የኒዩክሌር ቦምብ የላከው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❻) Who killed more than 100 millions of Indians in North America? Not Muslims!!
በሰሜን አሜሪካ ከ100 ሚሊዮን በላይ ህንዳዊያንን የገደለው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❼) Who killed more than 50 million of Indians in south America? Not Muslims!!
በደቡብ አሜሪካ 50 ሚሊዮን ህንዳውያንን የገደለው ማነው⁉️ ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
❽) Who took about 180 millions of African people as slaves and 88% of them died and were thrown overboard into Atlantic ocean? Not Muslims!!
180 ሚሊዮን ገደማ የሚጠጉ አፍሪካውያን በባርነት እንዲወሰዱ ያደረገውና ከነርሱም ውስጥ 88% የሚሆኑት እንዲሞቱና ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ እንዲጣሉ ያደረገው ማነው⁉️
ሙስሊሞች አይደሉም‼️
*
√ First of all, You will have to define terrorism properly.
ከሁሉም በፊት መጀመሪያ "ሽብርኝነትን" በሚገባ ልትገልፅ ይገባል።
If a non-Muslim does something bad. It is crime. But if a Muslim commits the same. He is a Terrorist.
አንድ ሙስሊም ያልሆነ ሰው "እንደ ሙስሊም" ተመሳሳይ መጥፎ ነገር ሲሠራ "ወንጀል" ነው። ነገር ግን ሙስሊም ይህን ተመሳሳይ ሲፈፅም እርሱ "አሸባሪ" ነው።
So first remove this double standards. Then come to the point. I am proud to be a MUSLIM !!
ስለዚህ መጀመሪያ ይህን ፍርደ ገምድለት አስወግድና ወደ ቁም ነገሩ ና! እኔ ሙስሊም በመሆኔ እኮራለሁ‼️

19/11/2020

የ አላህ በደሎኞችን ከ ኢትዮጵያ በቃችሁ በላቸው

02/05/2020

አስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ለማስፈፀም የወጣውን የትራንስፖርት ዘርፍ አፈፃፀም
መመሪያ ተከትሎ በተደረገ ቁጥጥር ከተፈቀደላቸው ቀን ውጭ ሲንቀሳቀሱ
በተገኙ ኮድ 2 አሸከርካሪዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ፖሊስ
ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ ቁጥጥር መምሪያ የቀጠና ኃላፊ
ኮማንደር በኃይሉ ደጀኔ እንደገለፁት መመሪያው ከወጣ በኋላ በተለያዩ
አማራጮች የግንዛቤ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል፡፡
ሚያዚያ 23 ቀን 2012 ዓ/ም ብቻ ማዕከልን ጨምሮ በ10ሩም ክፍለ ከተማ
በተደረገው ቁጥጥር 1 ሺህ 351 አሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸው ተራ ቀን ውጭ
ሲያሽከረክሩ በመገኘታቸው በህጉ አግባብ አስፈላጊው እርምጃ ተወስዶባቸዋል
ማለታቸውን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
በሰሌዳ ተራቸው መሰረት በማይንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ላይ የሚወሰደው
እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የኮቪድ-19 ወረርሽኙን ለመከላከል ለመቆጣጠርና
የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ የወጣውን የአስቸኮይ ጊዜ አዋጅ ክልከላን
በመተላለፍ በትራንስፖርት አሽከርካሪዎች ላይ በተደረገው ቁጥጥር ከተፈቀደው
የተሳፋሪ ቁጥር በላይ ጭነው የተገኙ 392 እና ከታሪፍ በላይ ሲያስከፍሉ በተገኙ
292 አሽከርካሪዎችም ላይ እርምጃ መወሰዱን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
ከሚያዚያ 09 ቀን 2012 ዓ/ም ጀምሮ የሰሌዳቸው የመጨረሻ ቁጥር ሙሉ
ወይም ዜሮ የሆኑት ማክሰኞ፣ ሀሙስ፣ ቅዳሜ፣ መንቀሳቀስ እንደሚችሉና ሰኞ፣
እሮብ እና አርብ ደግሞ የሰሌዳቸው የመጨረሻ ቁጥር ጎዶሎ የሆኑ ኮድ 2
ተሸከርካሪዎች እንዲያሽከረክሩ ሲፈቀድ የሳምንቱ የመጨረሻ ቀን እሁድ
ለሁሉም ተሸከርካሪዎች ነፃ ቀን መሆኑ በመመሪያው መደንገጉ የሚታወቅ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ካላንደር በሚዘጋቸውም ይሁን በሌሎች የበዓል ቀናት ከእሁድ
በስተቀር ከተፈቀደለት ተሸከርካሪ ውጭ ማሽከርከር እንደማይፈቀድ
በመመሪያው ተገልጿል፡፡

02/05/2020

በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት ዓለም አቀፋዊነት ላይ የሚሰራ ፎረም ለመመስረት በሚያስችሉ
ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተካሄደ።
ውይይቱን የከፈቱት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ፕሮፌሰር
አፈወርቅ ካሱ በከፍተኛ ትምህርት ዓለም አቀፋዊነት ዙሪያ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ
ከዓለም አቀፍ፣ ቀጠናዊ እና ሃገራዊ ምልከታዎች ጋር አያይዘው አቅርበዋል።
ፕሮፌሰር አፈወርቅ ፎረሙን ለማቋቋም ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ያለውን
ቁርጠኝነት ገልፀው በቀጣይ ሂደቶች ላይም አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
በውይይቱ በዓለም አቀፋዊነት ላይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየተከናወኑ ያሉ
የፖሊሲ እና ስትራቴጂ የማርቀቅ ስራዎች ያሉበት ሁኔታም ቀርቧል።
በውይይቱ ቀጣይ ስራዎችን በመለየት እና ለታቀዱ ስራዎች ማጠናቀቂያ የጊዜ
ገደብ በማስቀመጥ የተጠናቀቀ ሲሆን በፎረሙ ምስረታ፣ በመጠናቀቅ ላይ ያሉት
የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ሰነዶችን በውይይት አዳብሮ በማጽደቅ እና በከፍተኛ
ትምህርት ዓለም አቀፋዊነት ላይ የግንዛቤ ማሳደግ ስራዎች ቅድሚያ
ተሰጥቷቸው እንደሚሰሩ ተገልጿል።
የአዲስ አበባ፣ ሃዋሳ፣ መቐለ፣ ጅማ፣ ጅግጅጋ፣ ባህርዳር እና ሰመራ
ዩኒቨርሲቲዎች የዓለም አቀፍ ቢሮ ዳይሬክተሮች እና አመራር አባላት፣ የጅግጅጋ
ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሁም የአዲስ አበባ
ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት መሳተፋቸውን ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት
ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር
ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ
እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

02/05/2020

ከኮሮናቫይረስ ታማሚዎች ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው 2,516 ሰዎች ተለይተው
ክትትል እየተደረገላቸው ነው-የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
**************
ኮሮናቫይረስ በሀገራችን ከመጋቢት 03 ቀን 2012 ዓ.ም ይፋ ከተደረገበት ጀምሮ
እስከ ዛሬ ድረስ በኮሮና ቫይረስ መታመማቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ጋር የቅርብ
ንክኪ የነበራቸው 2,516 ሰዎች ተለይተዋል ሲል የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና
ኢንስትቲዩት ገለጸ።
ከእነዚህ መካከል 1,953 ሰዎች ክትትላቸውን አጠናቅቀው ወደ ኅብረተሰቡ
እንዲቀላቀሉ የተደረጉ ሲሆን፣ 521 ሰዎች ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛሉ
ብሏል።
በሀገራችን እስካሁን በቫይረሱ መታመማቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ውስጥ 42ቱ
(31%) የቅርብ ንክኪ የነበራቸው ሰዎች መሆናቸው ተረጋግጧል ሲል ገልጿል።
በኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኅብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ
ማስተባበሪያ ማእከል የኮቪድ-19 ቅድመ ዝግጅት እና ምላሽ የቅኝት ክፍል
አስተባባሪ አቶ መስፍን ወሰን፣ አንድ ሰው ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የቅርብ
ንክኪ አለው ሲባል በኮሮናቫይረስ የታመመ ሰው ምልክቱን ማሳየት ከመጀመሩ
ሁለት ቀናት በፊት በአንድ ሜትር ርቀት ውስጥ ሆኖ ከ15 ደቂቃ በላይ ቆይታ
ሲኖራቸው ሲሆን፣ በተጨማሪም የግል የጤና መከላከያ መሣሪያዎችን
ሳይጠቀሙ በበሽታው የተያዘን ሰው እንክብካቤ ሲያደርጉ ነው ብለዋል።
በዚህም መሠረት በበሽታው መታመማቸው ከተረጋገጡ ሰዎች ጋር የቅርብ ንክኪ
የነበራቸውን ሰዎች በመለየት በጤና ባለሞያዎች ለ14 ቀናት ክትትል
እንደሚደረግላቸው ገልጸዋል። በመሆኑም የቅርብ ንክኪ የነበራቸውን ሰዎችን
በመለየት ክትትል ማድረጉ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል እና ወረርሽኙም
እንዳይስፋፉ እገዛ አድርጓል ብለዋል።
በሀገራችን ማኅበራዊ ግንኙነታችንና የአኗኗር ባሕላችን የጠነከረ በመሆኑ፣ አንድ
በቫይረሱ የታመመ ሰው መታመሙ በሕክምና እስከሚረጋገጥ ድረስ ከሰዎች ጋር
ከሚኖረው ንክኪ በተጨማሪ የሚጠቀምባቸው መገልገያዎች ሌሎችም
ሊጠቀሙበት ስለሚችሉ ቫይረሱ በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው እንዲተላለፍ
ያስችለዋል በማለት ተናግረዋል።
ኅብረተሰቡ በሽታው በቀላሉ የሚተላለፍ በመሆኑ ሳይዘናጋ የሚተላለፉ
መልእክቶችንና መከላከያ መንገዶችን ተግባራዊ በማድረግ የበሽታውን ምልክት
የሚሳዩ ሰዎች በሚያገኝበትም ወቅት በተዘረጉ የነፃ የስልክ መስመሮች
በመደወል እንዲያሳውቅ እና የበሽታውን ስርጭት በመቆጣጠር በኩል
የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
በተጨማሪም ለተለያዩ ጉዳዮች በአንድ ቦታ መሰባሰብን በማስወገድ፣ እጅን
አዘውትሮ በመታጠብ፣ በመተው፣ ሰዎች በሚሰበሰቡበት ቦታዎች ላይ የአፍንና
የአፍንጫ መሸፈኛ በማድረግ፣ በአካል ንክኪ የሚደረግ ሰላምታን በመተው እና
አካላዊ መራራቅን ተግባራዊ በማድረግ የበሽታውን ስርጭት እንዲከላከል ጥሪ
አቅርበዋል።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 በመደወል ወይም
በኢ-ሜይል አድራሻችን [email protected] በመጠቀም ወይም ባሉበት
ክልል በተዘጋጁ ነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወይም
በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት በስልክ እንዲያሳውቁ ኢንስቲትዩቱ ጠይቋል።

24/12/2019

ወቅታዊ የኢትዮጵያ ሰላም፤ በአማራ ክልል እርምጃ ይወሰናል‼️
==============================================
✍️ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ በሙስሊሞች ላይ የደረሰውን አሳዛኝና አሳፋሪ ጥቃት አስመልክቶ፤ ሰሞኑን ሃገራችን ኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ በተቃውሞ እየተናጠች ነው።
ይህ ተቃውሞ ለጊዜው አነስተኛ እንደሆነና ወደፊት ግን ከዚህ በላይ ሊሆን እንደሚችል ታውቋል።
አሁን ላይ ይሄውም ሆኖ ህዝቡ ረገብ ያለው፤ የክልሉ መንግስት የሚወስደውን እርምጃ በግልጽ እስካሁን ድረስ ስላላሳወቀ ነው።
የክልሉ አስተዳደር የሚያወጣውን መግለጫ በርካታ የሃገሪቱ ህዝቦች በጉጉት እየጠበቁት ይገኛሉ።
የክልሉ መንግስት በትናንትናው ዕለት ጥቃቱ በተፈጸመባት የሞጣ ከተማ ከፌዴራልና ከክልል ከተውጣጡ የኃይማኖት አባቶችና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የወደሙ ንብረቶችን ጎብኝቷል፤ ከአካባቢው ህዝብ ጋርም ተወያይቷል።
ጥቃት የደረሰባቸውን መስጅዶች፣ የንግድ ማዕከላትና በሐሰት ጥቃት ደርሶበታል የተባለውን ቤተ ክርስቲያንም ጭምር ጎብኝተዋል።
እስካሁን ድረስ ግን ያወጣው መግለጫ የለም።

ይህን የክልሉን መንግስት መግለጫ በተለይም የሶማሌው ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ሙስጠፌ ዑመርና ህዝባቸው፣ የአፋር ክልል ህዝብ፣ የኦሮሚያ ክልል ህዝብ፣ የስልጤና ሐላባ ህዝብ፣ የወሎና የሸዋ ህዝብ፣ የመዲናችን የአዲስ አበባ ህዝብና ሌሎችም አካባቢዎች በጉጉት እየጠበቁት ነው።

በአጭር ቋንቋ ወቅታዊው የሃገራችን ሰላም በአማራ ክልል መንግስት እጅ ላይ ነው።
የክልሉ መንግስት ለተፈጸመው ዘግናኝ ጥቃት የተለመደውን ቸልተኝነቱንና ማድበስበሱን ወደ ጎን ጥሎ፤
ተመጣጣኝ እርምጃ ከወሰደ፤ ሃገሪቱ ሰላም ትሆናለች።
አለበለዚያ ግን ሰላሟ አሁን ካለችበት በባሰ መልኩ፥
መደፍረሱ የማይቀር ነው።

||
ስለሆነም የአማራ ክልል መንግስት ከሌቦች ጋር ሁኖ የጠፋውን እቃ ከመፈለግ ይልቅ፤
ያለ ምንም መለማመጥና ማድበስበስ ግልጽ የሆነ ሥራ ሊሠራ ግድ ይለዋል።
የሞጣ ከተማ ሚሊሻ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ይባላል። ተወልዶ ያደገው እዚያው ሞጣ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ "ወፈጥ" የሚባል ሰፈር ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ የሙስሊሞች ሱቆች ብቻ እየተመረጡ ሲቃጠል እና ሲዘረፍ በሞተር ሳይክል እየዞረ ሲያስተባብር እና ሲያዘርፍ ነበር። ለዝርፊያውና ለቃጠሎው ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፤ የሆነ ምግብ ቤት አለው። በከተማው የህገወጥ መሳሪያ እንቅስቃሴዎችም እያወቀ ተባባሪ የሆነ ሰው ነው።
ነገር ግን የአማራ ክልል መንግስት እስካሁን ድረስ ይህን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋል ሲገባው፤
ጭራሽ እንደ ደህነኛ ሰው ሌሎች ጥፋተኞችን ጠቁመኝ ብሎ አብሮት እየሠራ የሚገኘው ከዚህ ሰርቆ አሰራቂ በስልጣኑ ባላጊ ግለሰብ ጋር ነው። ክልሉ በዚሁ ማሾፉ ከቀጠለ፤ ከመግባባት ላይ አንደርስም። አቃጥለው የሚጨፍሩ ኋላ ቀር ሺህ መንጋዎችን ታቅፎ ይዞ፤ 5 ሰው፣ 15 ሰው፣ ወይም 22 ሰው በቁጥጥር ሥር አድርጊያለሁ እያለ ማስመሰሉን ያቁም።
*
የክልሉ መንግስት ሚዲያ በሚሠራው የተዛባ የዜና ዘገባ ላይ፤ ቤተ ክርስቲያንም የተቃጠለ አስመስሎ የሙስሊሞችን ትኩስ ጉዳይ በቀዝቃዛ ውሃ ለመቸለስ የሚያደርገውንና መቻቻል ገለመሌ እያለ የሚተርከውን ነገር ትቶ፤
እውነታውን ብቻ ሊዘግብ ግድ ይለዋል።
*
አለበለዚያ ግን የክልሉ መንግስት ልክ እንደስካሁኑ በእንዝህላልነት ጉዳዩን አለባብሼ አልፈዋለሁ ብሎ ከሞከረ፤
ለማንኛውም በሃገሪቱ ውስጥ ለሚፈጸም ዘግናኝ ችግር ሁሉ ኃላፊነቱን ሙሉ በሙሉ ይወስዳል።
ከክልሉ መንግስት ባሻገር፤
የክልሉን መንግስት ቸልተኝነት ቁሞ እየተመለከተ ሃገር እስክትተራመስ የሚጠብቀው የፌዴራሉ መንግስትም ቀላል የማይባል ዋጋ ይከፍላል።

ይህ ከመከሰቱ በፊት የክልሉ መንግስት የሚከተሉትን ነገሮች ይፈጽም።
1) በመጀመሪያ ደረጃ በርካታ የተቀናጀ መንጋ ተሰባስቦ መጥቶ አቃጥሎ የቃጠሎውን እሳት እየጨፈረ ሳለ፤
አንድ ጊዜ አምስት ሰዎችን ሌላ ጊዜ አሥራ አምስት ሰዎችን በቁጥጥር ሥር አድርጊያለሁ እያለ በቁስል ላይ እንጨት እየሰደደ የሚሳለቀውና ሙድ የሚይዘው በስልጣኑ የሚባልገው የክልሉ መንግስት፤
ከልቡ በተደጋጋሚ የሞጣ ከተማ ሙስሊሞችን፣ መላውን የአማራ ክልል ሙስሊም፣ መላውን የሃገሪቱን ሙስሊም ማኅበረሰብ በይፋ ይቅርታ ይጠይቃል።
2) የተቃጠሉ መስጅዶችን አሻሽሎ ይገነባል።
3) የተቃጠለውን ሆቴል በውስጥ አብረው ከወደሙ ንብረቶች ጋር በተሻለ መልኩ ይተካል።
4) የተቃጠሉ የገበያ ማዕከላትና ሱቆችን መልሶ ይተካል።
5) የተዘረፉ ንብረቶችን ይተካል።
6) በአጠቃላይ ለተጎጂዎች የሞራል ካሳ ከመደበኛው ንብረታቸው በተጨማሪ ይክሳል።
7) በዚህ ጥፋት ላይ ቀንደኛ ተዋናኝ የነበሩ አካላትን፤ ከቀስቃሽ አክቲቪስት፣ የፖለቲካ መሪና የኃይማኖት አባቶች ጀምሮ እስከ ድርጊቱ ፈጻሚ መንጋዎች ድረስ ከባድና የማያዳግም እርምጃ በሁሉም ላይ ይወስዳል።
8) ይህ ድርጊት ሲፈጸም ቁመው የተመለከቱ፣ አስቀድመው ኔትወርክ ያጠፉ፣ መነኻሪያውን ያመቻቹ፣ የሞጣ ከተማ መላው የመንግስት ባለ ስልጣንና የክልሉ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊዎች ከስልጣናቸው ላይ ይነሳሉ፤ ተጠያቂም ይደረጋሉ።
9) የአማራ መገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞችና የዜና ወኪል አቅራቢዎች በሙሉ ከኃላፊነታቸው ተነስተው ተጠያቂ ይደረጋሉ።
10) የአማራ መገናኛ ብዙሃን (AMMA) እያስተላለፈው ለነበረው አሳፋሪ ዘገባ፤
በሚዲያው ስም መላውን ሙስሊም ማኅበረሰብና ተጎጂዎችን በአደባባይ ይቅርታ ይጠይቃል።

ይህን ሲያደርግ እንታረቃለን።
||
በተረፈ ግን፤ የህዝቡን ስሜት በመነካካት ሸሪዓው ያላዘዘውን እርምጃ እንዲወስድ የምትገፋፉት ሙስሊሞች አላህን ፍሩ።
ህዝቡ እንኳን ስሜታዊ አድርጋችሁት እንዲሁም ስሜታዊ ነውና ነገሮችን ዑለማዎችን ከፊት በማስቀደም በሸሪዓዊ ዕውቀት እናስኪዳቸው።
ከትዕግስት ጋር የምሁራዊ አካሄድን ተላብሰን፤ ሸሪዓችንን ሳንጥስ የበላይነትንና ዲልን በዲናችን ውስጥ እናገኛለን።
ከትርፉ ጉዳቱ የሚያመዝንን ሥራ ከመፈጸም እንቆጠብ።
||
ግልባጭ፦
=====
Office of the Prime Minister-Ethiopia
Amhara Democratic Party /ADP/ CC office
Amhara Mass Media Agency
Amhara Communications
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ National Movement of Amhara


========
ታህሳስ 14, 2012 E.C

24/12/2019

ኢትዮጵያን ሆይ ሀገራችን ወደማትወጣበት አዘቅት እየገባች ነው ሁላችንም ልንጠነቀቅላት ይገባል !!?

24/12/2019

ዛሬ በጂጅጋ ከተማ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጎ በሰላም
ተጠናቆኣል። ፕሬዝዳንት ሙስጠፌ ቤተክርስቲያን እና መስጊዶችን እንዲሁም
የገበያ ቦታዎችን፣ ባንክና ህንፃዎችን በከፍተኛ ጥበቃ ስር በማድረግ በሳል
አመራር አሳይቷል። ጠዋት ትንሽ ውጥረት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ጂጂጋ
ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ትገኛለች።

24/12/2019

ጁምአ ላይ የሚጠበቀው ሰልፍ ሊራዘም ይችላል የሚባል ወሬ አለ
----------
በሞጣ ከተማ የተደረገው የማጋየት ዘመቻ ከጎጃም እስከ አዲሳበባ ባለ መረብ
መሆኑ ታወቀ !
******************
ራድዮ ነጋሺ
በሞጣ ከተማ የተደረገው መስጂድንና የሙስሊሙን ንብረት በጅምላ የማጋየትና
የማዉደም ብሎም የመዝረፍ ዘማቻ የተቀናበረው ከጎጃም እስከ አዲሳበባ ድረስ
በነበረ የጥፋት መረብ መሆኑን የራድዮ ነጋሺ ታማኝ ምንጮች ለዝግጅት
ክፍላችን አሳወቁ፡፡
የሞጣዉን የጅምላ ቃጠሎ በማስፈጸም ረገድ የሞጣ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ
ፖሊሶችም ተባባሪ እንደነበሩ የገለጹት ምንጮቻችን / ፖሊሶች በእለቱ ለእሳቱ
ማቀጣጠያ የሚሆን ቤንዚን ሲያቀርቡና ሲያቀብሉ እንደነበር ተደርሶበታል
ብለዉናል፡፡
እንደ አስተማማኝ የዉስጥ ምንጫችን መረጃ ከሆነ በዚህ የሙስሊሙንና የሃገር
ሃብትን በጅምላ የማጋየት ሂደት ከጎጃም እስከ አዲሳባ ያሉ ባለሃብቶችም
መሳተፋቸው ሊታወቅ ችሎዋል፡፡
ይህ እኩይ ተግባር ታቅዶና ሃገር አቀፍ መረብ ዘርግቶ ሙስሊሙ ላይና
በአጠቃላይም ሃገር ላይ የተደረገ ዘመቻ አንደኛው ምእራፍ መሆኑ በመረጃ
የተረጋገጠ ስለመሆኑ ከዚሁ ከአስተማማኝ ምንጫችን ለማወቅ ችለናል፡፡
ጉዳዩ በዚሁ ሳያበቃ በአስደንጋጭ መልኩ ለዚህ እኩይ ምግባር ሽፋን የሚሰጡ
በአማራ ክልልና በፌዴራል ደረጃ በከፍተኛ የሃላፊነት ደረጃ ላይ የተቀመጡ
የመንግስት ባለሥልጣናትም እንዳሉ ይኸው የደረሰን መረጃው ይጠቁማል፡፡
ይህ ወደሃገር ደህንነት የሚያመራ የሚመስለው አደገኛ ዘመቻ በቂ ዝግጅትና
እቅድ ያለው በሚመስል ቡድን እየተፈጸመ በመሆኑ የታቀዱ ሌሎች ሀገር
አዉዳሚ ዘመቻዎች በሃገር አቀፍ ደረጃ ከመተግበራቸው በፊት መንግስት ፣
የደህነንት አካላትና የሚመለከታቸው ሁሉ ከፍተኛ የክትትልና የማጣራት ስራ
በመስራት የተዘረጋዉን ሰፊ የሽብር መረብ በጊዜ ምንጩን በመቆጣጠር
ሃገራችንን መታደግ የሁሉም ዜጋ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ማሳሰብ እንሻለን!!
ከዚሁ ጋር በተያያዘ
---------------
መጅሊስ በነገው እለት መግለጫ እንደሚሰጥ ታወቀ
*****************
በሞጣ የተደረገውን መስጂዶችንና የሙስሊ ንብረቶችን በጅምላ የማጋየትን
የተቀነባበረ ዘመቻ በመቃወም በአዲስ አበባ ከተማ በመጪው አርብ ሊደረግ
የታቀደውን ሰላማዊ ሰልፍ በሚመለከት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ዋና ጽ/
ቤት (መጅሊስ ) በነገው እለት እረቡ መግለጫ ለመስጠት እንደተዘጋጀ የደረሰን
መረጃ የሚያመለክት ሲሆን ምናልባት በዝግጅት ጊዜ መጣበብ ሰበብ ሰላማዊ
ሰልፉ ለፊታችን እሁድ ሊዘዋወር እንደሚችልም ነው መረጃችን የሚያሳየው፡፡

24/12/2019

መልዕክቴ ለአማራ ክልል ሙስሊሞች‼️
=======================
(ይህቺን መልዕክቴን ለአማራ ክልል ሙስሊሞች አድርሱልኝ።)
||
✍️ የአማራ ክልል ሙስሊሞች ሆይ!
እንደሚታወቀው በክልላችሁ ውስጥ በተለያዩ ጽንፈኛ፣ አክራሪና አሸባሪ በሆኑ ከፊል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስቲያኖች የተለያዩ ጥቃቶች እየተሰነዘሩባችሁ ነው።
ጥቃቶች ከበፊቱ የአጼው ስርዓት ጀምሮ የተወጠኑ ሲሆን፤ እስካሁን ድረስም በተለያዬ መልኩ የጥፋት ሌጋሲዎቻቸው ዘልቀዋል። በቦምብ መግደል፣ ማፈናቀል፣ እምነታችሁንና የእስልምና ስማችሁን እንዲትቀይሩ ማስገደድ፣ ኢስላማዊ አለባበስ እንዳትለብሱ ማስገደድ፣ ንብረታችሁን መዝረፍ፣ መስጅዶቻችሁንና ሌሎች ኃይማኖታዊ ተቋሞቻችሁን ማቃጠልና ማውደም፣ ከተለያዩ ማኅበራዊ፥ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎዎች እንድትርቁ ማድረግና የመሳሰሉት መልካቸውንና ይዘታቸውን የቀያየሩ ጥቃቶች ተፈጽመውባችኋል።
ይህን ጥቃት የፈጸመባችሁ የተወሰነው የማኅበረሰብ ክፍል ነው።
ግን ሌላኛው ቀሪው ደግሞ በብዛት በተዘዋዋሪ አለበት፤ ወይም በሚደርስባችሁ ጥቃት በውስጡ ይደሰታል ማለት ነው።

በቅርብ አመት ብቻ እንኳ 21 መስጅዶቻችሁን አጥታችኋል።
ሺዎች ተፈናቅለዋል፣ ተዘርፈዋል።
✔️ ከቀናት በፊት በሞጣ ከተማ 4 መስጅዶች በውስጣቸው ከያዙት ንብረት ጋር በእሳት ጋይተዋል።
✔️ አንድ ባለ አራት ፎቅ ሆቴል በውስጡ ካለው ንበረት ጋር ሙሉ በሙሉ ወድሟል።
✔️ ከ307 በላይ ሱቆች ተቃጥለዋል፣ ተዘርፈዋል።
✔️ 27 ተሽከርካሪዎችና ባጃጆች የሙስሊም መሆናቸው በደንብ ተጠንቶ ተቃጥለዋል።
||
ይህ ሁሉ ጥቃት ሲፈጸም የከተማው አስተዳደርና የጸጥታ አካላት እየዞሩ ጥቃቱን ሲያስተባብሩ ነበር። ከጥቃቱ በፊት በመነኻሪያና በመሳሰሉት አካባቢዎች ቅድመ ዝግጅቶች ተደርገዋል።
ታዲያ ይህ ሁሉ ጥቃት ሲፈጸምባችሁ "ለምን?" ብሎ ያዘነላችሁና የታፈነውን ጩኸታችሁን እያሰማላችሁ ያለው፤
እዚያው በክልላችሁ ውስጥ የአብራካችሁ ክፋይ የሆነውና በብሄር ገመድ የተጋመዳችሁት የአማራው ኦርቶዶክስ አይደለም።
ምንም እንኳ ጥቃት ፈጻሚው ከፊሉ ራሱ ቢሆንም፤ ከፊሉ ደግሞ ለናንተ መቆርቆሩ ቀርቶ፤ እየተቆረቆረላችሁ ያለውን የሌላውን ክልል ማኅበረሰብ ጭራሽ እየኮነነ ይገኛል።
ስለዚህ ይህ ህዝብ ጥላታችሁ እንጅ ወዳጃችሁ አይደለም።
መቼም ቢሆን ከዚህ ህዝብ ጋር ካላችሁ የብሄር ዝምድና ይልቅ፤ ከሌላው ህዝብ ጋር ያላችሁ ኢስላማዊ ገመድ ይበልጥባችኋል።
ኦሮሚያው፣ አፋሩ፣ ሱማሌው፣ ሐረሩ፣ ሐላባው፣ ወሎዬው፣ ከሚሴው፣ ሁሉም በየ ቦታው ከናንተ ጎን ቁሟል።
እነዚያ ኩፋሮች ግን እስካሁን ዝም ብለዋችኋል። ጭራሽ እንዳውም ሌላው "ለምን ስማችንን ያነሳል?" እያሉ እየተጋጋጡ ነው። እናንተን ማገዛቸው ቀርቶ፤ ጭራሽ ለምን ታገዙ የሚሉ ግብዞች ናቸው።
ይህ የጥላቻቸው ሥር ምን ያክል ወደ ውስጥ ሰርጎ የተተከለ መሆኑን ያመላክታል።
አንዳንዶቹ አሁንም እናንተን ለመሸወድና ላለማስነቃት፤ የሆነች አጥጋቢ ያልሆነች ነገር ጫጭረዋል። እርሷንም ቢሆን እናንተ ስትቆጡ ያዩ ጊዜ ነው እንጅ፤ ከልባቸው ተቆርቋሪ ሁነው አይደለም። ለማስመሰል ነው።

እናንተ አንዳንዶቻችሁ ግን፤ የነርሱን ታቦት ስትሸኙ፣ ለመስቀል የእርድ እንስሳትን ስታበረክቱ፣ በዚሁ ጥቃት በደረሰበት በሞጣ ከተማ እንኳ አዲስ ቤተ ክርስቲያን ተገንብቶ ሲመረቅ ለእርድ በሬ ስትሰጡ ወዘተ ነበር። የነርሱ ሰልፍ ጊዜም ጀለቢያችሁን ለብሳችሁ ከነርሱ ጎን ነን ብላችሁ አብራችሁ ተሰልፋችሁ ነበር።
ምንም እንኳ በርካታ ጫናዎች፣ በቂ ዲናዊ ዕውቀት አለመኖር እና መሰል ምክንያቶች ቢኖሯችሁም፤ ይህን ማድረግ ግን አልነበረባችሁም። ዙሮ ዙሮ ያለፈው አልፏል፤ ላለፈ ክረምት ቤት አይሠራም፤ ለወደፊቱ ግን ማስተዋል ነው።
የሚያሳዝነው ነገር በዚሁ በሞታ ከተማ ውስጥ አንድ በሬውን ሲሰጡ የነበሩ በሞጣ ከተማ ነዋሪ የነበሩ እድሚያቸው ገፋ ያለ ሙስሊም ባለሃብት የሆኑ አባት፤
ባለፈ አመት በሬ ሰጥተው፤ አሁን ከቀናት በፊት በደረሰው ጥቃት ግን ሙሉ በሙሉ ንብረታቸው ወድሞባቸው በአንድ ቀን አዳር ከባለሃብትነት ወደ ነጭ ድሃነት ተምዘግዝገዋል።

አያችሁ?! የጭቃኔያቸው ጭካኔ የባለፈ አመቱ ውለታ እንኳ አልያዛቸውም።
እነርሱ እንደሆኑ ሰው በላ አረመኔዎች ናቸው።
ቢላልን ከሐበሻ፣ ሰልማንን ከፋሪስ፣ እነ አቡበከርን ከዚያው ከዐረብ ያገናኛቸው ብሄር ሳይሆን እስልምና ነው።
ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር ከአብራኩ ክፋይ ከእናቱ ልጅ ሙስሊም ካልሆነው ከወንድሙ ይልቅ፤
ሙስሊም የሆኑት በስጋ የማይዛመዱት ሌሎች ባዳዎቹ "ወንድሞቼ እነርሱ ናቸው!" ብሏል።
እናንተም በብሄር ሰበብ የሌሎች ክልል ወንድሞቻችሁን እንድትጠሉ የአማራ ብሄርተኞች ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም።
በርግጥ በወቅቱ ብዙዎቻችሁንም ሸውዴዋችኋል።
ዛሬ ግን አል-ሐምዱ ሊላህ፣ ሰው የሚለካው በመከራና በችግር ጊዜ ነውና፤
ይህን አጋጣሚ ትክክለኛ ወዳጃችሁንና ጠላታችሁን የምትለዩበት ሁኗል።

ስለዚህ ለወደፊቱ ከማን ጎን መቆም እንዳለባችሁ እወቁ።
በተረፈ አብሽሩ።
ብቸኝነትና ባይተዋርነት አይሰማችሁ።
ይሄው በየቦታው ተነቃንቆ ሃገሪቱን እያናወጣት ያለው የናንተ ነው፤ ለናንተ ብሎ ነው።
ልትኮሩ ይገባል።
ካለፈ ስህተታችሁ ግን ተማሩ። እንዳይለመዳችሁ!
በአንድ እባብ ሁለት ጊዜ እንዳትነደፉ።
ሙእሚን በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ሁለት ጊዜ አይገባም ብለዋል ነቢያችን።

አብሽሩ። አላህ ያግዛችሁ።
||
ወንድማችሁ፦ ሙራድ ታደሰ
========
ታህሳስ 14, 2012 E.C
||
t.me
||
ማሳሰቢያ፦
~~~~~~~
[በርግጥ ምክር ከማንም ይምጣ ከማንም መቀበል አለበት።
ግን ምናልባት ሌላ ጥርጣሬ ውስጥ ደግሞ እንዳትገቡ፤
እኔም የዚሁ ክልል እምብርት ከሆነቺው ቦታ የተወለድኩ የናንተው የአብራክ ክፋይ ነኝ።
ይህን ያልኩት አንዳንዶቻችሁ ውስጣችሁ ከጥርጣሬ እንዲጠራ ብዬ ነው።] copied

24/12/2019

በሞጣ ከተማ የተከሰተውን የኃይማኖት ተቋማት ጥቃት ተከትሎ
የጥፋቱ ተሳታፊዎች በአስቸኴይ ለሕግ እንዲቀርቡ መሰራት አለበት!!!

24/12/2019

ኃይማኖት በመንግስት ጣልቃ አይገባም፤ መንግስትም በኃይማኖት ጣልቃ አይገባም ማለት ነው።
ነገር ግን አንድን የቤተ ክህነት ሰባኪ ዲያቆን የቤተ መንግስቱ አማካሪ አድርጎ የሚሾም መንግስት፤
ሴኩላር ነኝ ከሚለው ሃሳቡ ጋር ገና ከመሠረቱ ይጋጭበታል።
በስያሜ ደረጃ "ሴኩላር !"ቢልም፤
ተግባሩ ግን ከተቃረነ ዋጋ ቢስ ነው።

ስለዚህ መንግስት ከህዝበ ሙስሊሙ ዘንድ በአሠራሩ አመኔታ ይጣልበት ዘንድ፤
በቤተ መንግስቱ ውስጥ በአማካሪነት ደረጃ የሾመውን የአንድ ኃይማኖት ሰባኪ ሊያስወጣ ይገባል።

አለበለዚያ ግን "ሴኩላር ነኝ!" የሚለው ጽንሰ ሃሳቡ፤ ከባዶ መፈክርነት የዘለለ አይሆንም።

ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፤
"አክራሪና የሃገር ስጋት ነው!" ብሎ ለሚያስበው ሙስሊም ማኅበረሰብ አማካሪ ሊሆን አይችልም።
ከግማሽ በላይ የሚሆን የአንድት ሃገር ህዝብ፤
"አክራሪ ነህ!" ብሎ በፈረጀው ግለሰብ ሊመራ አይገባም።

በፍጹም‼️
ዲያቆኑ ከቤተ መንግስቱ ውስጥ ከመባረሩም ባሻገር፤
በዚህ ጸብ አጫሪ መልዕክቶቹ ተነሳስተው በጎጃምና በጎንደር እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የርሱን ተልዕኮ ፈጻሚና ርዕዮት አራማጅ የሆኑ አካላት መስጅድ እንዲያቃጥሉ፣ ሙስሊሞችን ከቀያቸው እንዲያፈናቅሉ፣ እንዲገድሉ፣ ንብረታቸውን እንዲዘርፉ፣ እንዲደበድቡና ሌሎች ጥቃቶችንም እንዲፈጽሙ ሰበብ ሁኗል።

ስለዚህ በአፋጣኝ ለፍርድ ይቅረብ።
ሃገር እንዲትረጋጋና ሰላሟ እንዲሰፍን ከተፈለገ፤
ዲያቆኑ ይውጣና በህግ ጥላ ሥር ይዋል!
አለበለዚያ ግን ለማንኛውም ለሚፈጠር ሃገራዊ ችግር ሁሉ፤ ብዝሃነትን የማይረዳ አሃዳዊ ዲያቆን አማካሪው ያደረገው ቤተ መንግስት ኃላፊነቱን ይወስዳል።
ይሄው ነው!
||

ግልባጭ፦
=====
Abiy Ahmed Ali
Office of the Prime Minister-Ethiopia
Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር
========
ታህሳስ 13, 2012 E.C copied

24/12/2019

ይህችን አገር ለማቆየት አዋጪው መንገድ የአምልኮ ቦታዎች ሲፈርሱ መልሶ ለመገንባት ከመረባረብ ይልቅ አፍራሽ ግብረ ሃይሉ በአዕምሮው የተሸከመን የነቀዘ አመለካከት አፍርሶ ለመጠገን ኢንቨስት ማድረግ ነው።

(Copied)

24/12/2019

«መንግስት ከቀንድ ከብቶች ጋር በረት ውስጥ ማደር ያለባቸውን መርዘኛ ሰዎች እየለየ ወደ ማደሪያቸው በጊዜ ማስገባት ካልቻለ ጤናማውን ሰው በክለው ከሰውነት ወደ እንስሳት ዓለም እንዳያወርዱት ያሰጋል።»

24/12/2019

ነገሩ ፈጣን እርምጃ ያሻል ኢትዮጵያዊያን አስቡበት
አብን/አዴፓ እጁ የለበትም ልትሉ ነው?
ሞጣ ላይ መስጊድ ከመቃጠሉ በፊት መጀመሪያ ያደረጉት ይሄንን ነበር።
1- ኔትወርክ ተዘግቷል
2- ከ 10:00 ሰአት ጀምሮ መናሃሪያ ዝግ ነበረ ወደ ሞጣ መግባት ወይም
ከሞጣ መዉጣት አይቻልም ነበር።
3- የመናሃሪያዉ ሃላፊ የነበረዉ ሃብቴ ጸጋዬ ከሁለት ሳምንት በፊት ሙስሊም
ስለሆነ እና ያሰቡትን ለመፈጸም ሰለማይመቻቸዉ ቀደም ብለዉ ከስልጣን
አዉርደዉታል
4- አስቴሪዮ ማርያም ላይ መንገዶች በዲንጋይ ስለተዘጉ ልዩ ሃይሎች
በተፈለገዉ ሰዓት መድረስ አልቻሉ
5- የማቀጣጠያ ነዳጅና ጎማ የጫኑ ፒካፖች ከአመጸኞች ጋር ታይተዋል
6- ማርዘነብ ህንጻ ላይ የተከራዩ ክርስቲያኖች ቀድመዉ እቃቸዉን አዉጥተዋል
7-ሙስሊም ቤት ዉስጥ የተከራዩ ክርስቲያን ተማሪዎች የዛን ቀን አላደሩም
ነበር
ከረምናታ!

24/12/2019

የሃይማኖቶችን የመቻቻልና አብሮ
የመኖር ባህል የሚፃረሩ ጽንፈኛ አካሄዶችን እንደሚያወግዙ ጠቅላይ ሚኒስትር
ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ትናንት በአማራ ክልል
በሞጣ ከተማ ቤተክርስቲያንና መስጊዶች መቃጠላቸውን ተከትሎ በፌስቡክ
ገጻቸው ድርጊቱን ያወገዙበተን መግለጫ አወጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው “በብልጽግና ጎዳና ላይ በምትገኘው
ኢትዮጵያ የሀገራችንን የቆየ የሃይማኖቶችን የመቻቻልና አብሮ የመኖር ባህል
የሚፃረሩ ጽንፈኛ አካሄዶች ቦታ የላቸውም፤ እንዲህ ያሉ የፈሪ አካሄዶችን
አጥብቄ አወግዛለሁ” ብለዋል።
መላው ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያንም የመከባበርና አብሮ የመኖር ጥልቅ
እውቀታቸውን እንዲያጋሩም ጥሪ አቅርበዋል።
“ከፋፋይ አጀንዳዎችን መረዳትና መጠየፍ የጋራ ዕድገታችንን ለማረጋገጥ
ያስችላል” ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል።

24/12/2019

እውነት ይህ በቂ ምላሽ ነው
የአማራ ክልል የሃይማኖት
ተቋማት ጉባኤ በሞጣ ከተማ በእስልምና እና ኦርቶዶክስ እምነት ተቋማት ላይ
የደረሰውን ጥቃት በጥብቅ እንደሚያወግዝ አስታውቋል።
የክልሉ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ፥ አርብ
ዕለት በሞጣ ከተማ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንና እና በእስልምና
እምነት ተቋማት ላይ የደረሰው ጥቃት እምነት ያለው ሰው የሚፈፅመው ድርጊት
አለመሆኑን ገልጿል።
የቦርዱ ሰብሳቢ መልአከ ሠላም ኤፍሬም ሙሉዓለም፥ የሞጣ ከተማ ህዝብ
በፍቅር፣ በአንድነት፣በመቻቻል እና በመተባበር ተከባብሮ የሚኖር መሆኑን
አንስተዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች የጋራ ኮሚቴ በማቋቋም ክርስቲያኖች የሙስሊም መስጊድ
የመስራት በተመሳሳይ ሙስሊሞች ደግሞ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እየገነቡ
በመተሳሰብ የሚኖሩ መሆናቸውን አውስተዋል።
ሰሞኑን በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ የተፈፀመው ጥቃት እምነት ካለው
አካል ሊፈጸም የማይችል እኩይ ተግባር መሆኑን የገለጹት መልአከ ሠላም
ኤፍሬም ፥ ድርጊቱ በጥብቅ ሊወገዝ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ቤተ እምነት ሰዎች ችግራቸውንና ደስታቸውን ለፈጣሪያቸው የሚነግሩበት፣
ትምህርት የሚያገኙበት፣ ፍቅር እና ሠላም የሚሰበክበት፣ ሕሙማን
የሚፈወሱበት እና የተለያዩ የአምልኮ ሥርዓቶች የሚከወኑበት መሆኑን
አንስተዋል።
ስለሆነም እነዚህን ተቋማት በእሳት ማቃጠል በምድራዊ እና ሠማያዊ
መንግሥት እንደሚያስጠይቅ አስረድተዋል።
መንግስትም በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትን አጣርቶ አስፈላጊ የሆነ እርምጃ
መውሰድ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተያያዘ ዜና በሞጣ ከተማ በቤተ እምነቶች ላይ ከተፈጸመው ጥቃት ጋር
በተያያዘ 15 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የምሥራቅ ጎጃም ዞን
ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አያልነህ ተስፋዬ ተናግረዋል።
ከተማዋ በዛሬው ዕለት ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ መመለሷም ተመላክቷል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ibnu murad posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ibnu murad:

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share