በጂንካ ከተማ መንግሥት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት/Jinka Town Government Communication Office

  • Home
  • በጂንካ ከተማ መንግሥት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት/Jinka Town Government Communication Office

በጂንካ ከተማ መንግሥት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት/Jinka Town Government Communication Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በጂንካ ከተማ መንግሥት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት/Jinka Town Government Communication Office, Digital creator, .

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በነገው ዕለት በጂንካ ሁለገብ ስታድየም ውድድሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን አሳወቀ። ጥር 24/2017 ዓ,ም      ጂንካ ዞናዊ የልዩ ልዩ ሻምፒዮና...
01/02/2025

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በነገው ዕለት በጂንካ ሁለገብ ስታድየም ውድድሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን አሳወቀ።

ጥር 24/2017 ዓ,ም
ጂንካ

ዞናዊ የልዩ ልዩ ሻምፒዮና ውድድር ለመሳተፍ በአምስቱም ቀበሌ የተወጣጡ ወጣቶች ውድድር እያደረጉ እንዳሉ የጂንካ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ዘርሁን አሳውቀዋል ።
አክለውም በውድድሩ ጂንካ ከተማን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለመመልመል ቴክኒክ ኮሚቴ ተደራጅቶ እየሰራ መሆኑንም አሳውቀዋል ።

ውድድሩም ነገ ከቀኑ 7 ሰዓት 01 ቀበሌ ከ 02 ቀበሌ
9 ሰአት ኩሬ ቀበሌ ከ ባይጽማል ቀበሌ የሚያደርጉት
የቀበሌያት ጫወታ በጉጉት የሚጠበቅ መሆኑን ጠቁመዋል ።

ሁሉም የከተማችን ወጣቶች በነቂስ በመውጣት በጂንካ ሁለገብ ስታድየም ያለምንም ክፍያ መተው እየተዝናኑ የስፖርት ቤተሰብ ይሁኑ ስል መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራር ወቅታዊ የስምሪት አጀንዳዎችን አፈጻጸም ግብረመልስ ገመገመ።     ጥር 23/2017 ዓ/ም   የጂንካ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራር ወቅታዊየስም...
31/01/2025

የጂንካ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራር ወቅታዊ የስምሪት አጀንዳዎችን አፈጻጸም ግብረመልስ ገመገመ።

ጥር 23/2017 ዓ/ም

የጂንካ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራር ወቅታዊ
የስምሪት አጀንዳዎችን አፈጻጸም ግብረመልስ
ገምግመዋል ።

በአፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ በወቅታዊ መልክ በመንግስትና ፓርቲ ስምሪት የተሰጡ አጀንዳዎች የግብርና ስራዎች ፣ የጤና መድህን እና የቦንድ ግዥ ሌሎችም የስምሪት አጀንዳዎችን ላይ ስምሪት የተሰጠ ስሆን፣

አመራሮቹ ወደታችኛዉ መዋቅር ወርደዉ በቀበሌ ደረጃ ፈጽመዉ የተመለሱትን የተልዕኮ አፈጻጸም ተገምግሟል።

የጂንካ ከተማ አጠቃላይ አመራር 176,000 የቦንድ ግዥ በሁለት ዙር ለመክፈል በገባው ቃል መሠረት የመጀመሪያ ዙር 88,000 መሰብሰቡና ከባለሙያዎች ፣ከነዋሪዎች ፣በአጠቃላይ ከየማህበራዊ መሠረቱ የቦንድ ግዥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገምግሟል ።

በተገመገመዉ መሠረትም የተለያዩ መረጃዎች በስምርቱ መሠረት ተሰርቶ የቀረበበትን አፈጻጸም ስገመገም በጠንካራና እና በደካማ ጎን ለይተዉ የገመገሙና በድክመት ላስገመገሙ አመራሮች ማስተካከያ እንድያደርጉ ጥብቅ አስተያየት እና አቅጣጫዎች ተቀምጧል።

በመጨረሻም ለአመራሮች በተሰጠው አስተያየት መሠረት ሥራዎችን ወርደዉ ሰርተዉ እንዲመለሱ ወደ ቀበሌ ተልከዋል ።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት የውስጥ ገቢ ለመሰብሰብ ከቀበሌና ከመንደር ተጠሪዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።ጥር 23/2017 ዓ,ም    ጂንካመድረኩ ማዘጋጃ ቤቱ ገቢን አሟጦ በ...
31/01/2025

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት የውስጥ ገቢ ለመሰብሰብ ከቀበሌና ከመንደር ተጠሪዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

ጥር 23/2017 ዓ,ም
ጂንካ

መድረኩ ማዘጋጃ ቤቱ ገቢን አሟጦ በመጠቀም የከተማዋን ዕድገት ለማፍጠን የተዘጋጀ መሆኑን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሲሳይ ጋልሽ ተናግረዋል ።

አክለውም የገጠር መሬት ግብር አከፋፈልና ማዘጋጃ ቤቱ ከቀበሌና ከቀጠና አመራር ጋር በጋራ በመሆን የመንግስት ተቋማት ሳይቀር ግብር እንዲከፍልና በሁሉም የገቢ አርዕስት እንዲሰበሰቡ የግንዛቤ መድረክ መሆኑ ተገልጿል ።

በዚህ መድረክ የመጣችሁ በቀበሌ ደረጃ ከማህበረሰቡ ጋር የግንዛቤ መድረክ ተፈጥሮ ከሰኞ ጀምሮ የቦታ ግብር እንደሚከፈል ተገልጿል ።

የገጠር መሬት በጥማድ ይለካል እሱን ደሞ በአጭር ጊዜ መለካት እንዳለበት ተጠቁሟል ።

መምሪያዉ የንግድ ስርዓቱን ለማዘመን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀጂንካ፤ጥር 22/2017 ዓ.ም የኣሪ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ባሳለፍነዉ መንፈቅ ዓመት የንግድ ስርዓቱን ለ...
31/01/2025

መምሪያዉ የንግድ ስርዓቱን ለማዘመን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

ጂንካ፤ጥር 22/2017 ዓ.ም

የኣሪ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ባሳለፍነዉ መንፈቅ ዓመት የንግድ ስርዓቱን ለማዘመን ባከናወናቸዉ ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡን የመምሪያዉ ኃላፊ አቶ ደርበዉ ጠቃቦ ገልፀዋል።

ኃላፊዉ በ2017 ዓ.ም ግማሽ ዓመት መምሪያዉ ባከናወናቸዉን ተግባራትና ወቅታዊ የቤንዝል እጥረትን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

መምሪያ የንግድ ስራን ከማዘመን በተጨማሪ የዉስጥና የዉጭ ኢኒስፔክሽን ስራዎችን በማከናወን የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቡን አቶ ደርበዉ ጠቁመዋል።

በግማሽ ዓመቱ ህገ-ወጥ የንግድ ስርዓትን ለመቆጣጠጠር በተደረገ የኢኒስፔክሽን ስራ 1130 የንግድ ድርጅቶች ላይ የነበሩ ችግሮችን በመለየትና እርምጃ በመዉሰድ ህጋዊ እንደሆኑ መደረጉን አመላክተዋል።

ተቋሙ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪን ለመቆጣጠርና የኑሮ ዉድነቱን ለማረጋጋት ግብረ-ሃይል አቋቅሞ ቁጥጥር ስያደርግ እንደነበር አብራርተዋል።

ቁጥጥርና ክትትል ከማድረግም ባሻገር በየቦታዉ የሰንበት ገበያዎችን በማቋቋም የኑሮ ዉድነቱን ለማረጋጋት ትኩረት ተሰጥቶ መሰራቱን አስገንዝበዋል።

ህገ-ወጥ የቤንዝል ንግድን ለመቆጣጠር የቁጥጥርና ክትትል ስራዎች መሰራታቸዉን ገልፀዉ ህግን ባልተከተለ መልኩ ቤንዝል ስሸጡ የነበሩ ነጋዴዎች ላይ አርምጃ መወሰዱን ጠቁመዋል።

ቤንዝል በህጋዊ መንገድ እንድሸጥና በፍትሐዊነት እንድከፋፈል ለማድረግ መምሪያዉ ለአሽከርካሪዎች የጊዜ ሰለዳ አዘጋጅቶ እንድገዙ ማድረጉን ገልፀዋል።

ኃላፊዉ ወቅታዊ የቤንዚል አጥረትን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ እንደ ሀገር ከዝህ ቀደም ስገባ ከነበረዉ የቤንዝል አቅሪቦት 80 በመቶ መቀነሱንና አሁን እየቀረበ ያለዉ 20 በመቶ የምሆን ብቻ መሆኑን ገልፀዉ ይህም የሆነበት ምክንያት በሱዳንና በደቡብ ሱዳን መካከል በተፈጠረዉ ጦሪነት ምክንያት መሆኑን አብራርተዋል።

በዝህም ምክንያት በማደያዎች በየወሩ ይቀርብ የነበረዉ የቤንዝል አቅርቦት አሁን ተጨማሪ ወራቶችን ልፈጅ እንደሚችል ጠቁመዉ በአሁን ወቅት በዞኑ ያሉ አራት መደያዎች ሙሉ ክፍያ ፈፅመዉ በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ አመላክተዋል።

ችግሩን መፍታት ባይቻልም ለማስታገስ ከሚመለከታቸዉ አካላትና ከአጎራባች ዞኖች ጋር መምሪያዉ እየተናበበ እንደሚገኝና ቤንዝል የሚገኝበትን መንገድ ለማመቻቸት ያላቸዉን አማራጭና አቅም በሙሉ ተጠቅመዉ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ምንጭ ኣዞመኮ

ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል፦ አደም ፋራህብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ መክፈ...
31/01/2025

ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል፦ አደም ፋራህ

ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል፡፡

ምክትል ፕሬዚዳንቱ ብልፅግና ሚዛናዊነትን፣ አስተሳሳሪ ትርክትን እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልፅግናን መሰረት አድርጎ የተቋቋመ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ለማድረግም ፤ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ያለ ልዩነት በማቀፍ እየሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡

እውነተኛ የኅብረ ብሔራዊ ፓርቲ ሥርዓትን በመተግበርም የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በፍትሃዊነት እና በዘላቂነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄድ ነው።

የብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት መካሄድ ጀምሯል የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛውን ጉባዔ የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱን...
31/01/2025

የብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት መካሄድ ጀምሯል

የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛውን ጉባዔ የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱን ማካሄድ ጀምሯል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም ምክትል ፕሬዝዳንቶች በተማሪዎች የቀረበ የስዕል አውደ ርዕይንም ጎብኝተዋል።

በዚህ ጉባዔ ላይ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ እህት ፓርቲዎችም ይሳተፋሉ።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከል ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቦንድ ግዥ አደረገ።ጥር 23/2017 ዓ/ም      ጂንካየጂንካ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ስብዕና ...
31/01/2025

የጂንካ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከል ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቦንድ ግዥ አደረገ።

ጥር 23/2017 ዓ/ም
ጂንካ

የጂንካ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከል የመጀመሪያ ዙር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 20,000 (የሃያ ሺ ብር )ቦንድ ግዥ ማድረጋቸውን የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከል የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ዘርሁን አሳውቀዋል ።

አክለውም ይህ የቦንድ ግዥ እንደተቋም መገዛቱን ገልጽዉ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች የወጣበት አደረጃጀቶች በስፋት በማስተባበር የሀብት አሰባሰብ መርሃ ግብር በተጠናከረ መልኩ እንደምሄድ አሳውቀዋል ።

የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከል ስራአስኪያጅ አቶ ፈለቀ ፍቃዱ እንደተናገሩት የአባይ ግድብ በርካታ መሰናክሎችን አልፎ አሁን ላይ የደረሰበት ደረጃ አኩሪ ነው ብለዋል።

አክለውም ታላቁ ግድባችንን ሙሉ በሙሉ እውን ለማድረግ ማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሰን ዐሻራችን ሲናሳሪፍ ታላቅ ደስታ ይሰማናል ብለዋል።

የጂንካ ከተማ አስ/ር በእጩ ዶክተር ደረሰ ጌታቸው ሞት የተሰማቸውን ሃዘን  ገለፁ።              ጥር 22/2017 ዓ,ም                       ጂ ን ካ በቀብር ስነ ስረዓ...
30/01/2025

የጂንካ ከተማ አስ/ር በእጩ ዶክተር ደረሰ ጌታቸው ሞት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ።

ጥር 22/2017 ዓ,ም
ጂ ን ካ
በቀብር ስነ ስረዓት ላይ የጂንካ ከተማ አስተዳደርን በመወከል የከተማው ረዳት የመንግስት ተጠሪ እና የፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማንጎ ከበደ በመገኜት ለቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ተመኝተዋል ።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የውስጥ የቀበሌዎች ውድድር።
30/01/2025

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የውስጥ የቀበሌዎች ውድድር።

በኣሪ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ችሎት  ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።     22/05/2017/ ዓ/ም             ጅነካ በጂንካ ከተማ አስተዳደር  በከንቲባ የምታደመዉ ችሎት በ...
30/01/2025

በኣሪ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ችሎት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

22/05/2017/ ዓ/ም
ጅነካ

በጂንካ ከተማ አስተዳደር በከንቲባ የምታደመዉ ችሎት በዛሬዉ ቀን ተካሂዷል ።

በችሎቱም ዉሳኔ ያገኙና በቀጣይ ችሎት ቀጠሮ የተሰጣቸዉ ቅረታ አቅራብዎች እዳሉ ችሎቱ ገልጿል ።

በዛሬው ችሎት ሶስት ጉዳዮች የታዩ ስሆን አንዱ ወሳኔ እንዳገኘና ሁለቱ መረጃ አሟልተው እንዲመጡ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል ።

በችሎቱ የአንድ መምህር አሻግሬ በማዘጋጃ ቤት በኩል ክስ በተመለከቴ ማዘጋጃዉ መንገድ ነዉ በተባለዉ ይዞታ ላይ ያሉ በርካታ ንብረቶች እንድነሣ ደብዳቤ በመፃፊ ገልፀዋል ።

በፕላኑ መሠረት መንገድ በመሆኑ በዝህ ቦታ ያለ ንብረቶች/ ዛፎች/ እሰከ ቀን 29/05/2017/ዓ/ም ድረስ መነሳት እዳለበትና መሬቱ ለመንገድ አገልግሎት እድዉል ለማዘጋጃ ቤት እዲንድያስረክቡ ዉሳኔ ተላልፏል ።

ሁለቱ የተቀሩ ጉዳዮች ለቀጣይ ችሎት ተላልፏል ።

በአጠቃላይ ከችሎቱም ታዳሚዎች አንዳንድ ሃሳቦች በመነሣት በሳምንት አንድ ቀን የምደረገዉ ችሎት ቀጣይነት ያለዉና ዉጤታማ መሆኑን ሃሣብ አስተያዬታቸዉን ስተዋል ።

የኣሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ለመምህር ታምራት ካማይና ለባለቤቱ ተስፋነሽ ተጫነ ደማቅ የአቀባበል ስነ-ስርዓት አካህዷል።ጂንካ፤ጥር 22/2017 ዓ.ም የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ በአድ...
30/01/2025

የኣሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ለመምህር ታምራት ካማይና ለባለቤቱ ተስፋነሽ ተጫነ ደማቅ የአቀባበል ስነ-ስርዓት አካህዷል።

ጂንካ፤ጥር 22/2017 ዓ.ም
የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ በአድስ አበባ በተካሄደዉ የ2017 ዓ.ም የሺ ጋብቻ ካርኒቫል ላይ ዞኑን ወክለዉ ለተጋቡ ጥንዶች መምህር ታምራት ካማይና ባሌቤቱ ተስፋነሽ ተጫነ ጂንካ ከተማ ስገቡ ደማቅ አቀባበል አድርገዉላቸዋል።

የኣሪ ዞን አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጋናቡሌ ቡልሚና የባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ቃሾ በተገኙበት ነዉ የአቀባበል ስነ-ስርዓቱ የተካሄደዉ።

መምሪያ ለዞኑ በተሰጠዉ ኮታ መሰረት ጥንዶቹን መልምሎ ፈስቲቫሉ ላይ ተሳትፈዉ ጋብቻቸዉን እንድፈፅሙ ሁኔታዎችን ያመቻቸ ስሆን ጋብቻዉ በሰላም ተጠናቆ ወደቤታቸዉ ስመለሱም ተቀብሎ መርቆ ሸኝቷቸዋል።

ሺ ጥንዶች በተጋቡበት ትልቅ ፈስቲቫል ላይ ተሳትፈዉ ባህላችንን በማሳየት ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግኗቸዋል።

ምንጭ ኣዞመኮ

በኣሪ ዞን በጂንካ ከተማ አስተዳደር የህብረት ስራ ጽህፈት ቤት የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበር አባላት ለመመዝገብ እና ለማደራጀት በወጣው መመሪያ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማካሄዱን ...
30/01/2025

በኣሪ ዞን በጂንካ ከተማ አስተዳደር የህብረት ስራ ጽህፈት ቤት የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበር አባላት ለመመዝገብ እና ለማደራጀት በወጣው መመሪያ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማካሄዱን አስታወቀ።

ጥር 22/2017 ዓ/ም
ጂንካ

በመመሪያ ቁጥር 25/2016 ዓ/ም በወጣው መመሪያ መሠረት ለነባር አባላትና አድስ የተደራጁ አባላት የተገኙ ስሆን በህብረት ስራ ጽ/ቤት ሰነድ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት መደረግ ተችሏል።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ስሳይ ጋልሺ ፣ የጂንካ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ሴቶችና ህፃናት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አንለይ እርገጤ መድረኩ ተመሪቷል።

በጽህፈት ቤቱ በኩል ሰነድ የቀረበ ስሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት መደረግ ተችሏል ።

ከማህበሩ ነባር አባላትና አዳድስ አባላት በኩል በቀረቡ ጥያቄዎች ሀሳብ ላይ ምላሽ የተሰጠ ስሆን መሬት የወሰዱ ነባር አባላት በተያዘለት ጊዜ ግንባታ ማድረግ እንደምገባቸው ተገልጿል።

አዳድስ የማህበሩ አባላት የሚጠበቅባቸውን መስፈረት አሟልተው ከተገኙ ተፈፃሚ ይሆናል ስሉ ተደሚጠዋል።

በመድረኩ የኣሪ ዞን ከተማ ልማት ፣ የጂንካ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና ለሎች የባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

30/01/2025
የኣሪ ዞን በጂንካ ከተማ አስተዳደር የጂንካ ከተማ አስተዳደር  አጠቃላይ አመራር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ ተወያዩ ።ጥር 21/2017       ጂንካበግብርና ዘርፍ የተፋሰስ ስራዎች ፣የሌማት ቱ...
29/01/2025

የኣሪ ዞን በጂንካ ከተማ አስተዳደር የጂንካ ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ ተወያዩ ።

ጥር 21/2017
ጂንካ

በግብርና ዘርፍ የተፋሰስ ስራዎች ፣የሌማት ቱርፋት፣በጤናው ዘርፍ የጤና መድህን ፣ በትምህርት ዘርፍ የትምህርት ጥራት ልዩ ትኩረት በማድረግ እንደሚሰራ ተገልጿል ።

በጂንካ ከተማ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ
ሃብት አሰባሰብ ዙርያ ሰፍ ውይይት ተደረጓል ።

መድረኩን የኣሪ ዞን ፕላን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ አቦነና የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሲሳይ ጋልሽ መርተውታል ።

በስተመጨረሻም ለሁሉም ከተማ አመራር ስምሪት ተሰቷቸው የእለቱ ውይይት ተጠቃሏል ።

በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ የከተማ ዉስጥ ታክሲ አገልግሎት አሠጣጥ ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ ።               ጥር 20/2017 ዓ/ም                            ጂንካ የዞኑ ...
28/01/2025

በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ የከተማ ዉስጥ ታክሲ አገልግሎት አሠጣጥ ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ ።

ጥር 20/2017 ዓ/ም
ጂንካ

የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ከመንገድና ትራንስፖሪት መምሪያ ጋር በጋራ በመሆን በጂንካ ከተማ ዉስጥ የህዝብ ትራንስፖሪት ታክሲ አገልግሎት አሠጣጥ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል ።

የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሽብሩ አማሬ እና የዞኑ መንገድና ትራንስፖሪት መምሪያ ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ጨነቄ እንደገለጹት በዞኑ ዉስጥ የነዳጅ ዉድነትና እጥረት ምክንያት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ በከተማዉ ዉስጥ ሚኒባሶች የታክሲ አገልግሎት ከጥር 21/2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደምሆን ገልፀዋል ።

በዝህም መሠረት የአገልግሎት አሠጣጥና ታሪፊን በምመለከት ፦ 1ኛ መነሻ ከአድሱ አደባባይ አስከ ጤናዳምና ቡርካመር ቀበሌ ታሪፊ አሥር (10)ብር
፦ከአድሱ አደባባይ ወደ ፖሊስ ሠፈር ታርፊ አሥር(10)ብር
፦ከአድሱ አደባባይ ወደ የትነበርሽ ቀበሌ ታሪፊ ሃያ (20)ብር

2ኛ ፈርማታ መነሻ ከአንድነት ፋርክ /መስቀል አደባባይ/ወደ አርክሻ ባጃጅ ተራ ታሪፊ አሥር (10)ብር
፦ከአንድነት ፋርክ /መስቀል አደባባይ/ወደ ኬላ ሠፍር ታርፊ አሥር(10)ብር
፦ከአንድነት ፋርክ /መስቀል አደባባይ/ወደ ሠላሳ መትር /ሊዝ መንደር /ታርፊ አሥር(10)ብር
፦ከአንድነት ፋርክ /መስቀል አደባባይ/ወደ ካይሣ ቀበሌ ታሪፊ ሃያ(20)ብር ሆኖ የተወሰነ በመሆኑ የዞናችን ህዝቦች ሁሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አንድሆኑ ሓላፊዎች ጥሪ አቅርበዋል ።

በመጨረሻም አፈፃፀሙን የትራፊክ ፖሊሶች ክትትል እንድያደርጉ ጥብቅ መመሪያ የወረደ መሆኑን የጠቀሱት የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ድቪዥን ኃላፊ ኢንስፔክተር ሐና መስፊን ለሎች የታሪፊ ማጭበርበር ካለ በቅርበት ላሉ የትራፊክ ፖሊስ አባላት እንድያሳዉቁ አሣስበዋል ።

ዘገባዉ የኣሪ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ነዉ ።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት በጤናአዳም ቀበሌ የሴቶች ልማት ህብረት አደረጃጀት የንቅናቄ መድረክ አካሄደ ። ጥር 20/2017 ዓ.ም    ጂንካ ከተማ የጂንካ ከ...
28/01/2025

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት በጤናአዳም ቀበሌ የሴቶች ልማት ህብረት አደረጃጀት የንቅናቄ መድረክ አካሄደ ።

ጥር 20/2017 ዓ.ም
ጂንካ ከተማ

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት በጤናአዳም ቀበሌ የሴቶች አደረጃጀት ሴቶች ማህበር ፣ ሴቶች ሊግ ፣ሴቶች ፌዴሬሽን አመራሮች ምርጫ እንደሚደረግ ተገልጿል ።

በመድረኩም በኢኮኖሚ የበለፀጉ ሴቶችን ለማፍራት የሴቶች አደረጃጀት ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባና ሴቶች ህፃናት ጽ/ኃላፊ ወ/ሮ አንለይ እርገጤ ተናግራለች ።

አክለውም ሴቶች ተደራጅተው ከሰሩ በልማቱ፣ በኢኮኖሚው፣ በጤናው፣ በትምህርቱ፣ በጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች እና ሌሎችንም ትልልቅ ችግሮች በመቅረፍ ትልቅ ውጤት ማስመዝገብ የሚችሉ በመሆኑ አደረጃጀቶችን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑንተናግረዋል።

ሴቶች ከተደራጁ ለሀገር ልማት ሆነ ብልፅግና ትልቅ አቅም ያላቸው በመሆኑ አደረጃጀትቱን በማጠናከር ወደተግባር እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ረገድ ባለድርሻ አካላት ጠንክረው ሊሰሩ ይገባል ስትል የጂንካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ጽ/ኃላፊ ወ/ሮ ምስራች ታደለ ተናግራለች ።

የሴቶች ልማት ህብረት አደረጃጀት ምንነትና ጠቀሜታ እንዲሁም የአደረጃጀት ሂደት አሰራር፣ የህብረት ስራ ልማት እና የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ዙርያ የጂንካ ከተማ አስ/ር በሴ/ህ/ጽ/ቤት የሴቶች ማህበር ሰብሳቢ ወ/ሮ ወጋየዉ አልቅም አብራርተዋል ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት በተካሄደው 1ኛው የታዳጊ ወጣቶች ትምህርት ስልጠና ምዘና ውድድር ላይ ሲሳተፍ የነበረው የኣሪ ዞን ስፖርት ልዑካን በመዲናዋ ጂንካ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባ...
28/01/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አዘጋጅነት በተካሄደው 1ኛው የታዳጊ ወጣቶች ትምህርት ስልጠና ምዘና ውድድር ላይ ሲሳተፍ የነበረው የኣሪ ዞን ስፖርት ልዑካን በመዲናዋ ጂንካ ከተማ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደረገ።

በውድድሩ ብዙ የወርቅ መዳሊያና የብር መዳሊያ ማስመዝገብ መቻሉ ተገልጿል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ባዘጋጀው የመጀመሪያው ዙር   የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የወንዶች እግር ኳስ ፍጻሜ  የኣሪ ዞን  ከአጠቃላይ ዞኖች 2ኛ ደረጃን በመ...
27/01/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ባዘጋጀው የመጀመሪያው ዙር የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የወንዶች እግር ኳስ ፍጻሜ የኣሪ ዞን ከአጠቃላይ ዞኖች 2ኛ ደረጃን በመያዝ የብር መዳሊያ ተሸላሚ ሆነ።

ጥር 19/2017 ዓ.ም ኣዞመኮ-ጂንካ
የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ባዘጋጀዉ የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ዉድድር በወንዶች የእግር ኳስ ፍፃሜ የኣሪ ዞን ከወላይታ አቻቸው ጋር ተጫውተው 0 ለ 1 ተሸንፈው ከአጠቃላይ ዞኖች 2ኛ ደረጃ በመዉጣት የብር መዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።

የኣሪ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ይሄነዉ ተስፋዬ በታዳጊ ወጣቶች ዉድድር ለተገኘዉ ዉጤት የእንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ባዘጋጀው የመጀመሪያው ዙር የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የወንዶች እግር ኳስ ፍጻሜ የኣሪ ዞን ከአጠቃላይ ዞኖች 2ኛ ደረጃን በመያዝ የብር መዳሊያ ተሸላሚ ሆነ።

ጥር 19/2017 ዓ.ም ኣዞመኮ-ጂንካ
የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ባዘጋጀዉ የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ዉድድር በወንዶች የእግር ኳስ ፍፃሜ የኣሪ ዞን ከወላይታ አቻቸው ጋር ተጫውተው 0 ለ 1 ተሸንፈው ከአጠቃላይ ዞኖች 2ኛ ደረጃ በመዉጣት የብር መዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።

የኣሪ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ይሄነዉ ተስፋዬ በታዳጊ ወጣቶች ዉድድር ለተገኘዉ ዉጤት የእንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጂንካ ከተማ መንግሥት ኮሙንኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት/Jinka Town Government Communication Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share