Ahimed kadir

Ahimed kadir Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ahimed kadir, Digital creator, .

06/01/2024

የብሔራዊነት ወርቃማ ትርክት ምሳሌ የሆነችው የሁላችንም ከተማ!!

ከተማችን በአዲስ መንፈስ ታድሳ፣ ብሩህ ተስፋ ሰንቃ የአፍሪካ መዲና የሆነች ሁሉ ሚናፍቃት የብዝሀነት ማዕከል ናት። እንደ ስሟ እያበበች ያለችው አዲስ አበባ የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ አጠናክራ በመቀጠል የኗሪዎችን ሁለንተናዊ ችግሮቿን ፈታ ውጥን ትልሞቿን አሳክታ ያቀደችዉን ብልፅግና አሳክታ በፈጣን እድገት ላይ የምትገኝ ውብ ከተማ ናት።

ፓርቲያችን ሊገነባው ለሚፈልገው የብሔራዊነት ትርክት ቀደምት ምሳሌ የሆነች የብሔር የሀይማኖት፣ የሀሳብ ብዝሀነትን በውስጧ አቅፋ በፍቅር በሰላም እና በአንድነት የምታኖር መሰባሰቢያ አውዳችን ናት!!

በከተማችን በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት የተለያዩ ሰው ተኮር ተግባራትን እየተገበረ ፣ የተለያዩ የገበያ ማእከላት፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የመመገቢያ ማእከሎች፣ የወጣቶችን ጥያቄ ለመመለስ የተለያዩ የወጣቶች ማእከሎች እና የተለያዩ ስታዲየሞች እየገነባ ይገኛል።

የከተማችን አስተዳደር የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የክ/ከተሞች የእሁድ ገበያን በማቋቋም ህብረተሰቡ በቀላል ዋጋ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን እንዲሸምቱ እየተደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው።

ይህ ተግባር ፓርቲያችን በምርጫ ወቅት ለዜጎች ቃል የገባውን ሁሉንም አንድ በአንድ እየመለሰ መሆኑን የሚሳይ ነው።

የለውጡ አመራር በከተማችን ባስመዘገበው ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአለም መድረክ የተለያዩ እውቅናዎችን እና ሽልማቶችን እየተቸሩን ይገኛሉ።

ከተማችን ሁለንተናዊ ብልፅግናን አረጋግጣ ለሁሉም ነዋሪዎቿ ምቹ እና ሁሉም ዜጎች በእኩልነት የሚኖሩባት ህብረ-ብሔራዊ አንድነት የሰፈነባት ከተማ ሆኗ ትቀጥላለች።

06/01/2024
06/01/2024

የተጀመረውን የሰው ተኮር ተግባራትን አጠናክረን በማስቀጠል የህዝባችንን የመረዳዳት እሴት እናሳልጣለን!

የተቸገሩትን መርዳት፣ የደከሙትን መደገፍ የታመሙትን መጠየቅ፣ የተራቡትን ማጉረስ የህዝባችን ነባር እሴት ነው።

የፓርቲያችን እና የመንግስታችን ሰው ተኮር ፕሮግራሞችም ከህዝባችን ነባር እሴት ጋር የተጣጣሙ ናቸው።

የመረዳዳት ባህሎቻችን ወቅት ጠብቀው የሚደረጉ ሳይሆኑ ዓመቱን ሙሉ እንዲዘልቁ በተለይም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህላችን እንዲሆን ጥረቶች እየተደረጉ ነው።

ሀይማኖታዊ በዓላትንም በወንድማማችነት በእህትማማችነት እና በአብሮነት ማክበር ለኢትዮጵያዊያን እንግዳ ነገር አይደለም።

በተለይም የአደባባይ በዓላትን የማክበሪያ ቦታዎች የሁሉም የሀይማኖት አባቶች እና ተከታዮቻቸው በጋራ ከማፅዳት ጀምሮ "እንኳን አደረሳችሁ" እየተባባሉ መጠያየቅ ዋነኛው የበዓል ቀን ድምቀት ነው።

ለአብነትም ከነገ በስቲያ በዕለተ እሁድ በህዝበ ክርስቲያኑ የሚከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል (ገና) የህዝባችን የመረዳዳትና የመጠያየቅ እሴት ጎልቶ የሚወጣበት ዕለት ነው።

ያለው ለሌለው እያካፈለ፣ ተካፍሎ በመብላት ሁሉም ደስ ብሎት በዓሉን እንዲያሳልፍ የሚደረጉ ጥረቶች ዕለቱን ሁሉም በተስፋና በደስታ እንዲጠብቀው የሚያደርጉ የበዓሉ ተጨማሪ ድምቀት ናቸው።

ለአገራችን እና ለህዝባችን በጉልበታቸው፣ በእውቀታቸው እንዲሁም በገንዘባቸው ሲተጉ ቆይተው በእርጅና ዘመናቸው ጧሪ ያጡ አባት እናቶቻችንን እንዲሁም በተለያየ የህይወት አጋጣሚ የእኛን እርዳታ ለሚፈልጉ ወገኖቻችን ለመድረስ ዛሬ ነገ ልንል አይገባም።

የመኖር ጣዕሙ ሚስጥሩ ያለው በመስጠት እንጅ በመቀበል ላይ አይደለምና አለኝታነታችንን በማሳየት በምንም የማናገኘውን የመንፈስ እርካታ ልንጎናፀፍ ይገባል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን ህይወት በማሻሻል ፍትሀዊ ልማትን ለማረጋገጥ በሰው ተኮር የልማት ፕሮግራሞች ከሚያከናውናቸው ተግባራት በተጨማሪ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዋጋ ንረት እንዳይባባስ በተለይም በሸማቾች በኩል ምርቶችን በከፍተኛ ድጎማ እያቀረበ ሲሆን በየአካባቢው የሚፈጠሩ ባዛር እና ኤግዚቢሽኖችም መልካም አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ይታመናል።

ጊዜ በማይሰጥ አንገብጋቢ ችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎች ቢያንስ በቀን አንዴ መመገብ የሚያስችላቸውን ተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከል ከባለሀብቶች ጋር በመተባበር የማስፋፋት ስራ እየተከናወነ ሲሆን ማዕድ ማጋራትም ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የአገራችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ሲረጋገጥ የህዝባችን የኑሮ ደረጃ ከፍ እንደሚል ፓርቲያችን ያምናል። የአገራችን ብልፅግና እውን የሚሆነው የህዝባችንን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጥን አንገብጋቢ ችግሮችን ደግሞ በሰው ተኮር ፕሮግራሞቻችን እያቃለልን ስንጓዝ ነው።

የመረዳዳት ባህላችን እንዲዳብር መልዕክታችንን እያስተላለፍን ከወዲሁ መልካም የገና በዓል ለማለት እንወዳለን!

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

01/01/2024

ብልጽግና ፓርቲ ሀገር በቀል፣ ገቢር ነበብ ፣ አካታች፣ ተደራሽ አና በኢትዮጵያ ተጨባጭ አቅሞች ላይ በተመሠረተ የፖለቲካ እሳቤ የሚመራ ፓርቲ ነዉ።

ብልፅግና የኢትዮጵያን አቅሞች በመደመር እሳቤ በማሰባሰብ ፣ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል፣ ሰህተቶችን በማረም፣ የተዛቡ ትርክቶችን በማረቅ በጋራ የመልማትን፣ በትብብር የማደግን አቅጣጫ ይከተላል።

ይህ አዲስ ፖለቲካዊ እይታ ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ደረጃ ማሸጋገሪያ ሀዲድ ፤ የተጀመረዉን ለዉጥ ለማፅናትም አቅም ነዉ።

መልካም ዕለተ ሰንበት
Addis Ababa Prosperity Party

01/01/2024

መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ላደረጉ ኤምባሲዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንዲሁም አዲሱን ዓመት ለሚያከብሩ የኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንላቸው እመኛለሁ።

Hawaasa diippilomaatotaa fi Embaasiiwwan teessoo isaanii Finfinnee godhatan akkasumas bara haaraa kan kabajan firoottan Itoophiyaa hundaaf bara haaraa gaarii akka ta'uufin hawwa.

I wish a happy and prosperous new year (2024GC) to all the diplomatic community based in Addis Ababa and international friends and families living abroad.

30/12/2023

የወል ትርክት ለወል ሀገር!

ብልፅግና ፓርቲ ነጠላ ትርክቶች በመሀላቸው ያለውን የሀሳብ ክፍተት ከመሙላት ይልቅ የበለጠ የሀሳብ ልዩነት እንዲፈጠር ሰበብ አስባብ የሚፈልጉ እንደመሆናቸው መጠን ለወል ሀገር ግንባታ መሰናክል ናቸው ብሎ ያምናል። በመሆኑም ብሄራዊነት የተሰኘ አሰባሳቢ ሀገራዊ ትርክት ይዞ የተነሳ ፓርቲ ነው።

ይህ ታላቁ ትርክት መከፋፈልና መገፋፋትን በመሻገር ትብብርና መሰባሰብን ማዕከል አድርጎ የሚንቀሳቀስ በመሆኑ ከፖለቲካ ፓርቲ የተሻገረ ሀገራዊ ጠቀሜታ አለው።

ኢትዮጵያ ከአንድ ፖለቲካ አመለካከት በላይ የሆነች የተከበረች ሀገራችን ነች። የፖለቲካ አመለካከት የፖሊሲ አማራጭ ጉዳይ ስለሆነ በፖለቲካ ፓርቲ የተደራጁ ሀይሎች በሚያራምዱት የፖሊሲ አማራጭ የተለያዩ ቢሆኑም በሀገር ሉአላዊነትና ብሄራዊ ጥቅም በትብብር መስራት እንዳለባቸው ብልፅግና ፓርቲ በፅኑ ያምናል።

ከዚህ የፀና እምነቱ የተነሳ ነው ብልፅግና ፓርቲ ሙሉ በሙሉ የመንግሥት ስልጣን መቆጣጠር የሚያስችል የህዝብ ይሁንታ አግኝተው ሲያበቃ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደረጃ የተለያዩ የተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግስት ውስጥ ገብተው ሀገራቸውን ማገልገል እንዲችሉ ዕድል የሰጣቸው።

የሀገራችን ሰላም፣ አንድነትና ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ ብሄራዊነት የተሰኘ አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንስራ።

30/12/2023

የሰላም ጥሪውን በማይቀበሉ ሃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! መንግስት

የሕዝብን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞች በመጻረርና ሃብትና ንብረትን በማውደም የትኛውንም አይነት ጥያቄ መመለስ አይቻልም ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በወቅታዊ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸውም ከውጪ እና ከውስጥ ተቀናጅተው በሃይል እና በጉልበት በብጥብጥ እና በአመጽ እኩይ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎቶችን በሌሎች ላይ ለመጫን ብሎም ኢትዮጵያ ለማፍረስ የተቃጣውን ጥቃት የሀገራችን ሕዝቦች በማስተባበር በመመከት መቀልበሰ ተችሏል ብለዋል፡፡

አሁን ላይም በሀገሪቱ አንጻራዊ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ መቻሉን ነው የገለጹት፡፡

የሕዝብን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞች እና መብቶች በመጻረር ሃብትና ንብረትን በማውደም የትኛውንም አይነት ጥያቄ መመለስ አይቻልም ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡

የተለያዩ ጥያቄ እና ፍላጎት ያላቸው ሃይሎች ጥያቄዎቻቸውን በሰለጠነ መንገድ እንዲያራምዱና እንዲታገሉ የፖለቲካ ምህዳሩ ለዚህ ያመቸ እንዲሆን መንግስት ጥረት እያደረገ ነው ብለዋል፡፡

ሰላምን ዘላቂ ለማድረግና ቂምን ለመሻር ከሒሳብ ማወረራድና የጥላቻ መንገድ መውጣት የሚያስችሉ በርካታ እርምጃዎች መወሰዳቸውንም አብራርተዋል፡፡

ካንዱ የታሪክ ምዕራፍ ወደ አንዱ ስንሸጋገር በይደር ያደሩ እና ያልተቋጩ ዛሬም አጨቃጫቂ የሆኑ ጉዳዮች ችግሩን ይበልጥ እያወሳሰቡት እንደሚገኙ አንስተዋል፡፡

በየአካባቢው ነፍጥ አንግበው ከተነሱ ሃይሎች ጋር የሀገሪቱ ሕገ-መንግስት በሚፈቅደውና የሀገር አንድነትን እና ሉዓላዊነትን ባከበረ መልኩ የሰላም ውይይቶችን በማድረግ ወደ ሰላማዊ ሁኔታ እንዲመጡ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡

በአንጻሩ መንግስት በተደጋጋሚ የሚያቀርበውን የሠላም ጥሪ በመግፋት ግጭትና ሁከት የሚፈጥሩ የጥፋት ሃይሎች ዛሬም መኖራቸውን አንስተዋል፡፡

እነዚህ ሃይሎች መሰረታዊ የሕዝብ ጥያቄዎችን የሚመልስ የፖለቲካ ሥልት እና አካሄድ የማይከተሉ እንዲሁም በሕዝብ ጥያቄ ሽፋን የሕዝብ መገልገያዎችን ማወደም የዕለት ተዕለት ተግባራቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ይህ አውዳሚ እና እኩይ ድርጊታቸው የጸጥታ ሃይሎች ከሕብረተሰቡ ጋር ተቀናጅተው ከሚወስዱት እርማጃ ጋር ተዳምሮ ከሕዝቡ እንዲነጠሉ አድርጓቸዋል ብለዋል ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፡፡

በቀጣይም መላው ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምን ለመጠበቅ እና ለማጽናት የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከአሸባሪው ሸኔ ጋር መንግሥት የሠላም ንግግር ለማድረግ ያደረገው ጥረት አለመሳካቱን ጠቁመው÷ሠላምን ለማስጠበቅ ሲባል በሸኔ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን አረጋግጠዋል፡፡

በዚህም በርካታ የሸኔ አባላት ተደምስሰዋል ወይም እጅ ሰጥተዋል አሊያም የሎጂስቲክስ እና የሰብዓዊ ቀውስ እንዲደርስባቸው ተደርጓል ነው ያሉት፡፡

በአማራ ክልል የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ መንግስት በወሰደው አፋጣኝ እርምጃ ክልሉን ከመፍረስ አደጋ ከመታደግ ባለፈ የክልሉ የፖለቲካና አስተዳደር መዋቅር እንደ አዲስ እንዲደራጅ አድርጓል ብለዋል፡፡

በክልሉ ከሰላም ማስከበር ጎን ለጎንም የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎም በርካታ ታጣቂዎች ወደ ተዘጋጀላቸው የተዋድሶ ማዕከላት እየገቡ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

አሁንም የሰላም ጥሪው ክፍት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ጥሪውን በማይቀበሉት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በኢኮኖሚ ዘርፍም መንግስት የተለያዩ የኢኮኖሚ ፖሊስ መሻሻያዎችን በማድረግ ኢኮኖሚውን የማነቃቃት ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡

የተፈጠረውን የኑሮ ውድነት ችግር ለመቅረፍም የትኩረት መስኮች ተለይተው ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ነው ያብራሩት፡፡

በአሁኑ ወቅት የመኸር አዝመራ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ተሰብስቦ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡

30/12/2023
28/12/2023

ብልጽግና ፓርቲ በጽንፎች መሐል ሚዛን ጠብቆ የሚጓዝ ፓርቲ ነው!

ብሔራዊነት ከዋልታ ረገጥነት የወጣ ነው ፤ ብሔራዊነት ፍፁማዊ አንድነት እና ፍፁማዊ ልዩነት አይደለም፡፡ ብሔራዊነት ሀገራዊ አንድነት ሳይከፋፍል፤ ብዝኃ ማንነትንም ሳይደፈጥጥ ሁሉንም በልኩ እውቅና የሚሰጥ አሰባሳቢ እሳቤ ነው፡፡

የብሔራዊነት መንገዱ መደመር ነው፡፡ መዳረሻው ሁለንተናዊ ብልጽግና ነው፡፡ ብሔራዊነት አካታችነት መለያው ነው፡፡ ዋልታ ረገጥነት የብሔራዊነት ተቃራኒ ነው፡፡ ብልጽግና ፓርቲ በጽንፎች መሐል ሚዛን ጠብቆ የሚጓዝ ፓርቲ ነው፡፡ የመሐል ፖለቲካ፤ ፈተናዎች እንደሚበዙበት እሙን ነው፡፡

ከምሥረታው ጀምሮ በፈተናዎች እየጠነከረ የመጣው ፓርቲያችን ዕሳቤውን በብቃት ዳር ማድረስ እንጂ ለፈተናዎች እጅ መስጠት መለያው አይደለም፡፡ የመሐል ፓለቲካውን በማስጠበቅ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በመደመር መንገድ ይጓዛል፡፡

በወንድማማችነት/እህትማማችነት/ ገመድ የተራራቁ ጽንፎችን ያቀራርባል፡፡ ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ለማንነቶች ተገቢውን ዕውቅና ይሰጣል፡፡

የፍጽማዊ አንድነት እና የፍፁማዊ ልዩነት ጽንፎችን በማዳከም ብሔራዊነትን በገዥ ትርክትነት ማጽናት ወቅቱ የሚጠይቀው ቁልፍ የፖለቲካ ሥራችን ይሆናል፡፡

24/12/2023

ፓርቲያችን ብልፅግና ብሔራዊነት ገዢ ትርክት እንዲሆን የፈለገበት የመጀመሪያው ምክንያት ትርክቱ "አማካይ በመሆኑ" የተነሳ ነው!!

ኅብረ ብሔራዊነትን፣አካታችነትን ፍትሀዊነትን እና እኩልነትን ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚያረጋግጥ አሰባሳቢ ትርክት ሀገራችን ያስፈልጋታል ብሎ ብልፅግና ፓርቲ ያምናል።

አብሮነትን ክዶ ልዩነት ላይ ብቻ የሚያተኩር ትርክት፣ብዝኃነትንም ደፍጥጦ ፍፁማዊ አንድነት ላይ የሚያተኩር ትርክት ለምናስበው ሀገራዊ ብልፅግና አይጠቅመንም።

ኢትዮጵያ ሀገራችን ትናንት ሀገራዊ አንድነትን ለማስጠበቅ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ዋጋ የከፈሉላት፣ህዝቦቿ ብዙ የተድላ እና የፈተና ጊዜያትን በጋራ ወጥተው የወረዱባት፣በአንድነትም በልዩነትም ትርክት የተነሳ ግጭት እና ፈተናዎችን ያሳለፈች ሀገር ናት።

የብልፅግና ብሔራዊነት ትርክት ትናንትን አምርሮ የሚረግም ወይም አግንኖ የሚያወድስ አይደለም። ከትናንት ጠቃሚ የሆኑ ወረቶችን ለማስቀጠል የሚሰራ፣ጥፋቶችን የሚያርም ነው።ዛሬን ግን ለስራ እንጂ ለቁዘማ አይጠቀምበትም።

21/12/2023

የብሔራዊነት ወርቃማ ትርክት ምሳሌ የሆነቸው የሁላችንም ከተማ!!

ከተማችን በአዲስ መንፈስ ታድሳ፣ ብሩህ ተስፋ ሰንቃ የአፍሪካ መዲና የሆነች ሁሉ ሚናፍቃት የብዝሀነት ማዕከል ናት። እንደ ስሟ እያበበች ያለችው አዲስ አበባ የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ አጠናክራ በመቀጠል የኗሪዎችን ሁለንተናዊ ችግሮቿን ፈታ ውጥን ትልሞቿን አሳክታ ያቀደችዉን ብልፅግና አሳክታ በፈጣን እድገት ላይ የምትገች ውብ ከተማ ናት።

ፓርቲያችን ሊገነባው ለሚፈልገው የብሔራዊነት ትርክት ቀደምት ምሳሌ የሆነች የብሔር የሀይማኖት፣ የሀሳብ ብዝሀነትን በውስጧ አቅፋ በፍቅር በሰላም እና በአንድነት የምታኖር መሰባሰቢያ አውዳችን ናት!!

በከተማችን በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት የተለያዩ ሰው ተኮር ተግባራትን እየተገበረ ፣ የተለያዩ የገበያ ማእከላት፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የመመገቢያ ማእከሎች፣ የወጣቶችን ጥያቄ ለመመለስ የተለያዩ የወጣቶች ማእከሎች እና የተለያዩ ስታዲየሞች እየገነባ ይገኛል።

የከተማችን አስተዳደር የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የክ/ከተሞች የእሁድ ገበያን በማቋቋም ህብረተሰቡ በቀላል ዋጋ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን እንዲሸምቱ እየተደረገ ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው።

ይህ ተግባር ፓርቲያችን በምርጫ ወቅት ለዜጎች ቃል የገባውን ሁሉንም አንድ በአንድ እየመለሰ መሆኑን የሚሳይ ነው።

የለውጡ አመራር በከተማችን ባስመዘገበው ዘርፈ ብዙ ተግባራት በአለም መድረክ የተለያዩ እውቅናዎችን እና ሽልማቶችን እየተቸሩን ይገኛሉ።

ከተማችን ሁለንተናዊ ብልፅግናን አረጋግጣ ለሁሉም ነዋሪዎቿ ምቹ እና ሁሉም ዜጎች በእኩልነት የሚኖሩባት ህብረብሔራዊ አንድነት የሰፈነባት ከተማ ሆኗ ትቀጥላለች።

21/12/2023

ብሔራዊነት የሕዝቦችን የጋራ ጉዳይ ማጉላት ነው፡፡

ብሔራዊነት የሕዝቦችን የጋራ ጉዳይ ማጉላት ነው፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ የኖርን፣ ለአንድ ሀገር እኩል ዋጋ የከፈልን ነን ብሎ ያስባል፡፡ በዚህች ሀገር የመጡ ዕድሎችንና መከራዎችን እኩል ተጋርተናል ብሎ ያምናል፤ እኩል የሀገር ባለቤቶች ነን ብሎ ይቀበላል።

ቢጻፍም ባይጻፍም፤ ቢነገርም ባይነገርም ለኢትዮጵያ ታሪክ የየራሳችንን አስተዋጽኦ ያደረግን፤ የባህል፤ የእምነት፤ የቋንቋ፤ የአስተሳሰብ ልዩነቶችን የምናከብር ነን ብሎ ይቀበላል፡፡

ልዩነቶቻችን ግን አንድነታችንን ወደ መከፋፈል የማይወስዱብን፤ አንድነታችንም ማንነታችንን የማያጠፋብን፤ ዛሬን አጥብቀን የምንሠራ፤ ነገን በርትተን የምንገነባ ሕዝቦች ነን ብሎ ያስባል፡፡

ብሔራዊነት በሀገራችን ለሚገኙ ሁሉም ብሔር፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ዕውቅና የሚሰጥ ካላቸው የትሪክ ትሥሥር፤ የጋራ ጥቅምና የጋራ ተስፋ በመነሳት፤ በፈቃደኝት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ህብረትና ትብብር ሊኖሪቸው ይገባል የሚል አስተሳሰብ ነው፡፡

ብሔራዊነት ብዝኃነትን ሳይክድና ሳይደፈጥጥ የህብረትን አስፈላጊነትና ጥቅም አጽንኦት የሚሰጥ፤ የቋንቋና የባህል ልዩነቶችንም የሚያከብር አካሄድ ነው፡፡ ብሔራዊነት ለጋራ ዓላማና ግብ አብረን መቆም፤ አብረን መሥራት እንዳለብን፤ እጣ ፈነታችን እጅጉን የተቆራኘ በመሆኑ መደጋገፍ፤ መተጋገዝ እንደሚገባን የሚያስገነዝብ ትርክት ነው፡፡

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ahimed kadir posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share