Ethio 255

Ethio 255 The news industry are forms of mass media that focus on delivering news to the general public.

27/04/2023

የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የፓርቲው የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ ተገደሉ።

እስካሁን ባለው መረጃ ሌሎች 4 ሰዎችም መገደላቸው ተሰምቷል።

በአቶ ግርማ የሺጥላ፣በቤተሰቦቻቸው እና ጠባቂዎቻቸው ላይ ጥቃት የተፈፀመው በዛሬው ዕለት ሚያዝያ 19፣2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ መሆኑን የአማራ ክልላዊ መንግስት ተናግሯል።

አቶ ግርማ የተገደሉት "የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በሰሜን ሸዋ ዞን ሠርተው ከመሀል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሀን ሲመለሱ ልዩ ቦታው መንዝ ጓሳ አካባቢ በታጠቁ ፅንፈኛ ሃይሎች በደረሰባቸው ጥቃት "መሆኑን የክልሉ መንግስት መግለጫ አስረድቷል።

ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በአቶ ግርማ የሺጥላ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፅፈዋል።

"ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት የወንድማችንን የግርማ የሺጥላን ነፍስ ነጥቀዋል"ብለዋል።

"ልዩነትን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ባህል በሆነበት ክፍለ ዘመን፣ በሐሳብ የተለየንን ሁሉ በጠመንጃ ለማሳመን መነሣት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው"ሲሉም አክለዋል።

አቶ ግርማ ተወልዶው ባደገበት አካባቢ መገደላቸውን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገዳዮቹ " ከእኛ የተለየ ሐሳብ ማሰብ አልነበረበትም ብለው የሚያምኑ ነውጠኛ ጽንፈኞች "ናቸው ብለዋል።

ተግባሩንም "አስነዋሪና አሰቃቂ "ሲሉ ገልፀውታል።

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትም የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።

ገዳዮቹን "ፅንፈኛ ሀይሎች" ሲል የገለፃቸው የክልሉ መግለጫ በሀሳብ ትግል ማሽነፍ ያልቻሉትን በኀይል ለማስፈፀም ያደረሱት ጥቃት ዓላማውን ማሳካት የማይችልና ጊዜው ያለፈበት፣ ዘመኑን ያልዋጀ የጥፋት መንገድ ስለሆነ አምርረን የምንታገለው ተግባር ነው" ሲል ተናግሯል።

መንግስት በክልሉ ውስጥ የሚፈጽሙትን ስርዓት አልበኝነትና የሽብር ድርጊት ለመከላከል፤ ለመቆጣጠርና ሕግ ለማስከበር እርምጃ ይወስዳል ብሏል።

የጥቃቱን አድራሾችም ለሕግ ያቀርባል ሲል መግለጫው አስረድቷል፡፡

የክልሉ ሕዝብ የተፈጠረውን የሽብር ድርጊት ከማውገዝ ጀምሮ ወንጀለኞች ለሕግ ቀርበው ፍትህ እንዲረጋገጥ፣ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግና እንዲረጋጋ የክልሉ መግንስት ጥሪ አቅርቧል ።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግላጫ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጸ/ቤት ኃላፊ እና የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ግርማ የሺጥላ" ባደገበት ቀዬ በጽንፈኞች በግፍ ተገድሏል"ብሏል።

ግድያውን "ነውረኛ እና ዘግናኝ ተግባር"ሲል የገለፀው የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ፈፃሚዎቹ የትም ቢገቡ ለሕግ ይቀርባሉ ብሏል።

የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች በአቶ ግርማ የሺጥላ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልፀዋል።

" መንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን እስር እና እንግልት ያቁም " - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበርየኢትዮጵየ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ባወጣው መግለጫ ፤ ኢትዮ...
14/04/2023

" መንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን እስር እና እንግልት ያቁም " - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር

የኢትዮጵየ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ባወጣው መግለጫ ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ባለሙያዎች የሚሰሩበት አውድ እየጠበበ ጋዜጠኞች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ በመንግስት የፀጥታ አካላት #እየተሸማቀቁ እና #እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ መታዘቡን ገልጿል።

ከሰሞኑን ፤ የማህበሩ መስራችና የስራ አስፈፃሚ አባል እንዲሁም የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ፦
👉 ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ ፣
👉 ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ፣
👉 ጋዜጠኛ ጌትነት አሻግሬ ፣
👉 ጋዜጠኛ በየነ ወልዴ፣
👉 ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው በመንግስት ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።

አንዳንዶቹ ያሉበት ቦታ እና ምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ እንኳን ቤተሰቦቻቸውም በቂ መረጃ ሳይኖራቸው በእስር ላይ ይገኛሉ ብሏል።

ማህበሩ ፤ ጋዜጠኞች ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ እየታሰሩ፣ እየታፈኑና ቤታቸውና ቢሯቸው እየተበረበረ መሆኑ ባለሞያዎች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ፤ የፕረስ ምህዳሩ የበለጠ እንዲጠብ እያደረገ ነው ሲል ገልጿል።

ማህበሩ የተቋቋመው እንደዚህ አይነት ሙያውን የሚያቀጭጩ ጫናዎችን ለመታገል መሆኑን በመግለፅ የመንግሥት እርምጃዎችን በፅኑ አውግዟል።

ጋዜጠኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ጉዳያቸውን እስር ቤት ሳይቆዩ መከታተል እንደሚችሉ ከሁለት ዓመት በፊት በወጣው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቢደነገግም ይህ ግን ማህበሩ እንደሚያሳስበው ገልጿል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር መንግስት፦
- የፕረስ ነፃነት እንዲረጋገጥ
- ያጸደቃቸውን ህገ-መንግስታዊና ዓለም አቀፋዊ ህጎች እንዲያከብርና ውስጡን እንዲፈትሽ
- ያለምንም የህግ አግባብ ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ
- ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆም ጠይቋል።

Ethiopia - Cities are being shaken by gunfire, the special forces have entered, the protesting Amhara authorities, the entire Amhara region are about to...

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን የዶክተሬር ዲግሪ ለመሰረዝ በቂ ማስረጃ መኖሩ ተገለጸጥያቄ ሲነሳበት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የዶክተሬት ዲግሪን ሊያሰርዝ የሚችል በቂ የጥ...
13/04/2023

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን የዶክተሬር ዲግሪ ለመሰረዝ በቂ ማስረጃ መኖሩ ተገለጸ

ጥያቄ ሲነሳበት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የዶክተሬት ዲግሪን ሊያሰርዝ የሚችል በቂ የጥናት “ስርቆት” ማስረጃ ማግኘቱን የዓለም ሰላም ፋውንዴሽን አስታወቀ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እ.ኤ.አ. በ2017 የዶክተሬት ዲግሪያቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰላም እና ደህንነት ጥናት ተቋም (IPSS) ከተቀበሉበት ጊዜ አንስቶ፤ በዶክትሬት ዲግሪያቸው ላይ የሕጋዊነት ጥያቄዎች ሲነሱ እንደነበር ተቋሙ አስታውሷል፡፡

ፋውነዴሽኑ ከዚህ በፊት ጥያቄ ሲነሳበት የነበረውን የጠቅላይ ሚኒስትሩን የዶክተሬት ድግሪ ላይ ሰፊ ማጣራት በማድረግ ያገኘው ማስረጃ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥናት እንደገና ሊመረምር የሚችልበት በቂ ማስረጃ ማግኘቱን ጠቁሟል፡፡

ተቋሙ የዶክትሬት ዲግሪውን ለማገድ ወይም ለመሻር በቂ ነው ያለውን ማስረጃ ሲያቀርብ፤ በሌሎች ጥናቶች ላይ የተጠቀሱ ጽሑፎች በቀጥታና በጥቂት ማሻሻያ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥናት ላይ ተደግመው መገኘታቸው በማስረጃ አስደግፎ አብራርቷል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የዶክተሬት መመረቂያ ፅሑፍ ላይ “የሌብነት” ምልክቶች እንዳሉ ባደረገው ማጠራት መታዘቡን ፋውንዴሽኑ ይፋ ባደረገበት ጽሑፍ ላይ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጉዳዩን እንደገና ሊመለከት የሚችልበትን ሁኔታ ጠቁሟል፡፡

በዚህም ዩኒቨርስቲው ፕላጂያሪዝምን ወይም የሰው ጥናት ስርቆትን በሚከለክለው አሰራር እንደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች የዶክትሬት ዲግሪያቸውን መሰረዝ እንደሚል ተጠቁሟል፡፡ በኹለተኛ ደረጃ እንደ አማራጭ የተጠቆመው፤ ጥናቱ እንደገና ተሻሽሎ ድጋሚ እንዲሰራ በማድረግ እሰከዚያው የዶክተሬት ዲግሪ ማገድ ነው፡፡

የመመረቂያ ጥናቱ “Social Capital and its Role in Traditional Conflict Resolution: The Case of Inter-religious Conflict in Jimma Zone of the Oromia Regional State in Ethiopia” በሚል ርዕስ የተሰራ ሲሆን፤ የጥናቱ ትኩርት ማኅበራዊ ካፒታል በባህላዊ የግጭት አፈታት ውስጥ ያለው ሚና ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡

“ፕላጂያሪዝም” የሰውን ጽሑፍ ወይም ሥራ መስረቅ ወይም የራስ አስመስሎ ማቀረብ የሚል ተቀራራቢ ትርጉም የሚሰጠው ሲሆን፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥናትም ይህ አይነቱ ችግር እንደታየበት ፋይንደሽኑ ትናንት ይፋ ባደረገው ጽሑፍ አስታውቋል፡፡

የዓለም ሰላም ፋውንዴሽን በጠቅላይ ሚኒስትሩ የዶክተሬት ዲግሪ ላይ ያቀረባቸውን ማስረጃዎች ለመመልከት 👉 https://t.co/rnnNneqRIl
(በመርሻ ጥሩነህ)

Alex de Waal, Jan Nyssen, Gebrekirstos Gebreselassie, Boud Roukema and Rundassa Eshete Ever since Abiy Ahmed was awarded his PhD degree at the Institute of Peace and Security Studies (IPSS) at Addis Ababa University in 2017, questions have been asked about whether this was a legitimate doctorate. On...

https://www.facebook.com/353996825672757/posts/646758493063254/?app=fbl
12/04/2023

https://www.facebook.com/353996825672757/posts/646758493063254/?app=fbl

"ኢትዮዽያን ማስቀጠል ከሚፈልጉት ጎን በመሆናችን የሚከፋ ከአለ እርሱ መፍረሷን የሚናፍቅ ብቻ ነው!" ጄ/ል ስብሃት ኤፍሬም :- የኤርትራ መከላከያ እና ማዕድን ሚኒስቴር

"የኢትዮዽያ መፍረስ ቀድሞ የሚጎዳት ኤርትራን ነው! እኛም ይህንን በመረዳታችን በኢትዮዽያ መቀጠል የማያወላውል አቋም ያላቸውን ወጣቶች ያለንን ወታደራዊ ክህሎት ለማካፈል ፈቃደኛ በመሆናችን የሚከፋ ከአለ የኢትዮዽያን መፍረስ የሚናፍቅ ብቻ ነው።

ከጥንት ጀምሮ 'በኢትዮዽያ መቀጠል የማያወላውል አቋም አለው' ተብሎ ከሚታመንባቸው ብሔሮች መካከል ግንባር ቀደሙ «የአማራ» ብሔር ነው።

ከነፃነት ኤርትራ በፊት በትጥቅ ትግሉ ወቅት የአማራ ብሄር አባል የሆነ ወይም በእናቱ ወይም በአባቱ የአማራ ዘር ያለበት ኤርትራዊ ሳይቀር የኤርትራን ከኢትዮዽያ መለየት ፈጽሞ የማይቀበለው መሆኑን ስለተገነዘብን ለትግሉ ውጤታማነት ሲባል #በአማራ ህዝብ ላይ ብዙ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ሰርተናል። በወቅቱ ትግሉን ውጤታማ ከደረጉልን ቁልፍ ስልቶች መካከል አንዱ ነበር።

ሆኖም ግን በቅርቡ ሁለቱ ሀገራት በዶ/ር አብይ ምክንያት ዳግም ሲገናኙ በመጀመርያ በአፋጣኝ ኢንዲታረም ያደረግነው ፤ ለትግሉ ስኬታማነት ለሰራነው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በይፋ ይቅርታ መጠየቅና «አማርኛ» ቋንቋ ኤርትራ ውስጥ በሚገኙት ትምህርት ቤቶች በሙሉ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ መወሰን ነበር፤ ተግባራዊ አድርገነዋል።

በመሆኑም አሁን በወያኔ የሽብር ድርጊት በቀጠናው በተከሰተው የሰላም መደፍረስ ምክንያት በተለይም ሱዳን፣ ኢትዮዽያንና ኤርትራን በሚያዋስነው ድንበር አካባቢ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ከኢትዮዽያ ጋር ከሚያዋስነን የአማራ ክልል ህዝብ ጋር በመተጋገዝና በመረዳዳት እየሰራን ነው።

የእኛ እቅድ የቀጠናውን ሰላም በጋራ ለመጠበቅ በአዋሳኝ ከሚገኘው ከአማራ ክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመተጋገዝ በሱዳን ኮሪደር የሚገቡ ማናቸውንም ፀረ-ሰላም የውጭ ኃይሎች መከላከል እንጁ በኢትዮዽያ የውስጥ ጉዳይ ፈጽሞ መግባት አይደለም።

ይህንን ተግባራዊ ስናደርግ በወያኔ ስርአት በሴራ ፖለቲካ ተጠልፎ የተዳከመውን የአማራ የፀጥታ አካላትን ወታደራዊ ክህሎታችንን እና ልምዳችንን በማካፈል በቀጠናው ጠንካራ አቋም ያለው አንድነት መፍጠር ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ፤ ለኢትዮዽያ ቀጣይነት የማያወላውል አቋም ያላቸውን የአማራ ወጣቶች ፈቃደኛ እስከሆኑ ድረስ በአሉበት ስፍራ ወይም ወደ ኤርትራ በመምጣት ወታደራዊ ክህሎት እንዲኖራቸው እናግዛ
ቸዋለን። " Interest

11/04/2023

ሠላም ለኢትዮጵያ !!!!

10/04/2023
እንዳትረሱት !!!
10/04/2023

እንዳትረሱት !!!

10/04/2023

" ባልበላው ጭሬ ልበትነው!! ''
አለች

Washington Post article:"The Amhara people are facing an existential threat," said a third resident naming several conte...
10/04/2023

Washington Post article:

"The Amhara people are facing an existential threat," said a third resident naming several contested areas prone to violent clashes. "Why did they start the disarmament with Amhara/"

Six Amhara journalists have been arrested in the past two weeks, according to the Amhara Association of America and social media posts. The head of the Ethiopian Media Authority did not respond to requests for comment on the journalists' arrest.
https://www.washingtonpost.com/world/2023/04/10/ethiopia-disarm-amhara-tigray/

10/04/2023

ኢትዮጵያየ ክፉሽን አልስማ !!

Send a message to learn more

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio 255 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share