12/03/2022
የዚች ልጅ ቤተሰቦች እዲገኙ ወይም ለሚያውቃት ሰው እዲደርስ ሸር ሸር እድታደርጉት በፈጣሪ ስም እለምናቹሀለሁ !!!
እህታችን በድገተኛ ህመም ሂወቷ ካለፈ ዛሬ አራትኛ ቀኗ ነው እስካሁን ድረስ የቤተሰቦቿን አድራሻ ማወቅ አልተቻለም።
አከራዋን ስጠይቃቸው 2 ልጅ እዳላትና (የራያ ) ልጅ ነኝ እዳለቻት ነግራኛለች አብረዋት ለሚኖሩት ደግሞ ለአዳንዶቹ (የወልዲያ) ልጅ ነኝ፣ ለሌላወቹ ደግሞ ( የጎንደር ) ልጅ ነኝ ትላቸው ስለነበር የቤተሰቦቿን አድራሻ ማወቅ አልተቻለም።
ይች ልጅ ቤተሰቦቿን ለመርዳትና ሰርታ ሂወቷን ለመቀየር ወደ አረብ አገር ዱባይተሰደደች። ዱባይ በኩትራት ቤት እየሰራች እያለ የሚጥል በሽታ ስለነበረባት አሰሪዋ እደዚህ እየሆንሽ እኔጋ አላሰራሽም ደስ አለሽ ቦታ በውጭ ስሪ ብላ ስታሰናብታት እህታችንም እደማንኛውም ሰው በውጭ ለመስራት ታክሲዋን ይዛ አበሻ አለበት ሰፈር አድርሰኝ ትለዋለች ባለታክሲውም ወደ አጅማን ያመጣና አበሻ አለበት ቦታ ይጥላታል፣ ታክሲው ካደረሳት ቦታ ተቀምጣ አበሻ ስትጠብቅ አበሻ ታገኝና አዲስ እደሆነችና የጃዛ ቤት እደምትፈልግ ስትነግራቸው ልጆቹም ነይ ከኛጋ ብለው ይወስዷትና የጃዛ ቤት ከልጆቹ ጋር እየኖረች እያለ ስራ ታገኝና እመዳም ቤት እየሰራች እያለ march 7/20014 በፊት ያሰቃያት የነበረው በሽታዋ ይነሳባትና ያማታል ። ሁኔታዋን ያዩ አሰሪዎቿም ወደ እጃዛ ቤቷ አድርሰዋት ይመለሳሉ አከራዋም ደጋግፋ ወደቤት ታስገባትና ታስተኛታለች ጠዋት ላይ ሲነሱ መናገር አትችልም አከራዋ ለሰኮሪቲ በመናገር አምቡላንስ ተደውሎ መተው አጅማን sheikh khalifa hospital ቢወስዷትም ልጅቱ መትረፍ አልቻለችም።
እስካሁን ድረስ አስከሬኗ ወደ አገር እዲገባ በቅርበት የሚከታተል ሰው ባለመኖሩ የኢትዮጲያ ኢምባሲም ሆነ
ኮሚኒቲ መረጃው ደርሷቸው እያለ ዝምታን መርጠዋል።
Ⓒ//ማርቆስ የጊዮን ልጅ🙏