Beder media

Beder media በድር ሚዲያ

19/08/2022

የኢትዬጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች የቱርክ ኤምባሲ የሐይማኖት ጉዳይ ዳይሪክቶሬትን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በኢትዮጵያ የቱርክ ኤምባሲ የሀይማኖት ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ከሆኑት ከጀሚል ኢብራሂም ጋር በፅህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል

በውይይቱ ላይ ከፕሬዝደንቱ በተጨማሪ ምክትል ፕሬዝደንቱ ሼይኽ አብደልአዚዝ አብድል ወሌ እና የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ፀሃፊ ሼይኽ ሐሚድ ሙሳ ተካፍለዋል::

በኢትዮጵያ የቱርክ ኤምባሲ የሀይማኖት ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ሚስተር ጀሚል ኢብራሂም ከጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች ጋር ትውውቅ ያደረጉ ሲሆን በሐይማኖታዊ እና በሌሎች በሁለትዬሽ ጉዳዮች ላይ በስፋት አብረው መስራት እንደሚፈልጉ በውይይታቸው ላይ አንስተዋል::

ሚስተር ጀማል ኢብራሂም በኢትዬጵያ የቅዱስ ቁርዓን የአማርኛ ትርጉምን በስፋት ለህዝቡ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል በበርካታ ኮፒ አሳትመው ለማሰራጨት ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር አብረው መስራት እንደሚፈልጉ የገለፁ ሲሆን በተጨማሪም የቅዱስ ቁርዓንን በኦሮምኛ ቋንቋ ትርጉም በመጅሊሱ በኩል ተዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው እና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በሚፈለገው ብዛት አሳትመው ለህዝቡ ለማድረስ ቢሯቸው ዝግጁ መሆኑን ለጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች ገልፀውላቸዋል::

በጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራር በኩልም ሙስሊሙን የሚጠቅሙ ማንኛውንም ስራዎች በትብብር እና በመተጋገዝ ለመስራት ሁሌም ዝግጁ መሆናቸውን እና በራቸው ክፍት መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከቱርክ ኤምባሲ የሐማኖትን ጉዳይ ዳይሪክቶሬት ጋር በቀጣይም በስፋት በጋራ ጉዳዮች ላይ ለመስራት ከስምምነት በመድረስ ውይይታቸውን አጠናቀዋል::

ሸይኽ ፈትሑ ዲን ሐጂ ዘይኑ ሙቁና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።የም/ቤቱ የቀድሞ ም/ፕሬዝዳንት የነበሩት ሸይኽ ዓሊ ሙሐመድ በቢሯቸው በመ...
03/08/2022

ሸይኽ ፈትሑ ዲን ሐጂ ዘይኑ ሙቁና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።

የም/ቤቱ የቀድሞ ም/ፕሬዝዳንት የነበሩት ሸይኽ ዓሊ ሙሐመድ በቢሯቸው በመገኘት ለሸይኽ ፈትሑ ዲን ሐጂ ዘይኑ ቢሮውን አስረክበዋል።

በዚህም መሰረት፦

1) ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ የም/ቤቱ ዋና ፕሬዝዳንት፣
2) ሸይኽ ፈትሑ ዲን ሐጂ ዘይኑ ሙቀና ም/ፕሬዝዳንት፣
3) ሸይኽ ሑሴን በሺር የም/ቤቱ ዋና ጸሐፊ በመሆን ም/ቤቱን የሚመሩ ይሆናል።

©: የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

27/07/2022

ዉድ የ ዳዕዋ ቲቪ ቤተሰቦች እንደሚታወቀው ዳዕዋ ቲቪ የተለያዩ ቂርዓቶችን እና ዳዕዋዎችን በ ብቁ አሊሞቻችን እያቀረበ ያለና የ ኢልም ክፍተቱን ለመሙላት በ ቲቪ እና በ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በተከታታይ እያቀረበ ይገኝል። ነገር ግን ይህ ትምህርት በ ብዙ ማህበረሰባችን ጋር ተደራሽ ስላልሆነ እና መማር የሚፈልጉ ነገር ግን እንዳለ የማያውቁ ስላሉ ሁላችሁም ቤተሰቦቻችን ላላችሁ ኦዲያንስ እና ቤተሰብ ሼር በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ የ ኢልም ማግኘት ሰበብ እንዲሆኑ በ ትህትና እንጠይቃለን።

★★★★★
📡 የ ዳዕዋ ቲቪ ስርጭትን በ ናይል ሳት
ለመከታተል:– 👇
ፍሪኩዌንሲ:- 12521
ሲምቦልሬት:- 27500
ፖላራይዜሽን:- vertical
★★★★★

Youtube👇
https://www.youtube.com/channel/UCrF8wiLRD4IIE1-5-73zdAg

Facebook👇
https://www.facebook.com/daewatv/

Telegram👇
https://t.me/daewa_tv

የትግራይ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር ለአዲሶቹ የመጅሊስ  አመራሮች ድጋፉን በመግለፅ መግለጫ አወጣ።የትግራይ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር የሙስሊሙን ተቋም ለሁለት ለመክፈል ሴራ ሲሸርቡ የነበሩ ...
26/07/2022

የትግራይ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር ለአዲሶቹ የመጅሊስ አመራሮች ድጋፉን በመግለፅ መግለጫ አወጣ።

የትግራይ ሙስሊሞች አንድነት ማህበር የሙስሊሙን ተቋም ለሁለት ለመክፈል ሴራ ሲሸርቡ የነበሩ ቡድኖች ሴራቸው ከሽፎ አዲስ አመራር በመመረጡ የተሰማውን ደስታ ገልጿል::
አዲሶቹ አመራሮችም ህዝበ ሙስሊሙን የጠንካራ ተቋም ባለቤት ከማድረግ ባሻገር በሃገሩ የልማት ስራዎች ላይም እንዲሳተፍ እንዲያደርጉ አሳስቧል::
ማህበሩ ከአዲሱ የመጅሊስ አመራሮች ጎን በመቆም በሁሉም ነገር ለማገዝ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል:

" የተቀመጠው አድራሻ በአግባቡ ስለማይሰራ ውጤታችንን ማየት አልቻልንም " - ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆችየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘንድሮው የስምንተኛ ከተማ አቀፍ ፈተ...
25/07/2022

" የተቀመጠው አድራሻ በአግባቡ ስለማይሰራ ውጤታችንን ማየት አልቻልንም " - ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘንድሮው የስምንተኛ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን አሳውቋል።

ቢሮው ተማሪዎች ውጤታቸውን https://aaceb.gov.et/%e1%8b%a88%e1%8a%9b-%e1%8a%ad%e1%8d%8d%e1%88%8d-%e1%8b%89%e1%8c%a4%e1%89%b5/ ወይም aaceb.gov.et ላይ በመግባት ማየት እንደሚችሉ ገልጾ ነበር።

ነገር ግን ቢሮው ይፋ ያደረገው ውጤት መመልከቻ አድራሻ በትክክል ስለማይሰራ ውጤት ለማየት እንዳልቻሉ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች አሳውቀዋል።

በመሆኑም ፤ የከተማው ትምህርት ቢሮ አድራሻው ላይ ያለውን ችግር እንዲያርም /እንዲያስተካክል እንዲሁም ለህዝብ ይፋ ከመደረጉ በፊት ተገቢውን ፍተሻ ማለፉን ሊያረጋግጥ ይገባል ብለዋል።

በአዲስ አበባ ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 29 /2014 ዓ/ም በተሰጠው የ8ኛ ክፍል ፈተና ከ71 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።

በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ይፋ በተደረገው መረጃ ለፈተናው ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከል 63.9 ፐርሰንት ተማሪዎች 50 እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል፤ 85.5% ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል ለመዛወር ችለዋል።

[et_pb_section fb_built=”1″ fullwidth=”on” _builder_version=”3.22.2″ global_module=”237511″ saved_tabs=”all”][et_pb_fullwidth_image src=”https://aaceb.gov.et/wp-content/uploads/2021/11/aaceb-web-new-header-ENG-text.png” _builder_version=”3.22.2″][/et_pb_fullwidth_image][e...

25/07/2022

beder media

ህዝበ-ሙስሊሙ አንድነቱን በማጠናከር የሃሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ሊከፋፍሉት የሚሰሩ አካላትን ፍላጎት ማክሸፍ አለበት ሲሉ ሸይኽ ሀጂ ኢብራሒም ቱፋ ጥሪ አቀረቡ

ህዝበ-ሙስሊሙ አንድነቱን በማጠናከር የሃሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ሊከፋፍሉት የሚሰሩ አካላትን ፍላጎት ማክሸፍ እንዳለበት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሒም ቱፋ ጥሪ አቀረቡ፡፡

በአዲስ መልኩ ስራ የጀመሩት የመጅሊሱ አመራሮች የሙስሊሙን አንድነት ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡

ኢዜአ በጽህፈት ቤታቸው ተገኝቶ ያነጋገራቸው የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሒም ቱፋ፤ ህዝበ-ሙስሊሙን አንድ አድርጎ የሚመራ ጠንካራ ተቋም መገንባት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የረዥም ጊዜ ጥያቄ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ከለውጡ በፊት በነበረው ስርዓት ይህ ጥያቄ እንዲመለስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አካላት ከፍተኛ ዋጋ እንደከፈሉም ነው የገለጹት፡፡

ከዚህ አኳያ ለረዥም ጊዜ ህዝበ-ሙስሊሙን አንድ ለማድረግ የተሞከሩ በርካታ ጥረቶች ሊሳኩ አለመቻላቸውን አስታውሰው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የሚመሩት መንግስት የሙስሊሙ የዘመናት ጥያቄ እንዲመለስ የሚጠበቅበትን እገዛ ማድረጉን አብራርተዋል፡፡

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሁሉንም ክልሎች ያሳተፈ ምርጫ በማካሄድ የራሱን አመራሮች በመምረጥ በኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ መክፈት መቻሉን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ እስልምናን ከተቀበሉ ቀደምት አገራት መካከል አንዷ መሆኗን ያስታወሱት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሒም፤ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን በሚመጥን መልኩ ጠንካራ መጅሊስ ለመገንባት ቁርጠኛ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

አንድነት ኃይልና ሰላም መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ በአዲስ መልኩ ስራ የጀመሩት የመጅሊሱ አመራሮች የሙስሊሙን አንድነት ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩም ነው ያረጋገጡት፡፡

ከዚህ ቀደም በርካታ ኡለማዎች ጊዜ ሰጥተው ያዘጋጁት "የአንድነትና ትብብር" ሰነድ ቢኖርም እስካሁን ወደ ተግባር አለመለወጡን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ የሚፈለገው አንድነትና ለውጥ እንዳይመጣ እንቅፋት ፈጥሮ መቆየቱን ተናግረዋል።

"የመጅሊሱ አመራሮች ሰነዱን ወደ ተግባር ለማስገባት ይሰራሉ" ሲሉም አመልክተዋል።

ሆኖም አንዳንድ አካላት የተለያዩ የሃሰት መረጃዎችን በማሰራጨት ህዝበ-ሙስሊሙን ለመከፋፈል እየሰሩ መሆኑን የጠቀሱት ሸህ ሀጂ ኢብራሒም፤ የእነዚህ አካላት ዋነኛ ፍላጎት ሙስሊሙን በመከፋፈል ሀገር ማተራመስ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም ህዝበ-ሙስሊሙ ይህን ተገንዝቦ አንድነቱን ይበልጥ ሊያጠናክር እንደሚገባም ጥሪ አቅርበው፤ በየትኛውም ጊዜ የሚፈጠሩ ችግሮችን ተቀራርቦ በውይይት መፍታት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ኢዜአ

❝ሕዝበ ሙስሊሙ ለሰላም በአንድነት እንዲቆም ጥሪ ቀረበ❞ ‼  የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኸ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ‼ሙስሊሙ ኅብረተሰብ ከአንድነት ውጪ የሚያዋጣ...
23/07/2022

❝ሕዝበ ሙስሊሙ ለሰላም በአንድነት እንዲቆም ጥሪ ቀረበ❞ ‼ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኸ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ‼

ሙስሊሙ ኅብረተሰብ ከአንድነት ውጪ የሚያዋጣው ነገር አለመኖሩን ተረድቶ ሀዲስና ቁርኣንን መሠረት በማድረግ ለሰላም በአንድነት እንዲቆም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ እንደተናገሩት የነብዩ መሐመድን እና የሱሀቦችን ፈለግ በመከተል ሀገሪቱን ወደ ሰላም ማምጣት ተገቢ ነው።

̋ሀገራችን ኢትዮጵያ በኡለማ የበለፀገች ሀገር ነችና ኡለማዎቻችን የሚሉትን በመስማት መተግበር አስፈላጊ ነው ̋ ያሉት ፕሬዚዳንቱ ከምን ጊዜውም በላይ አሁን ለሰላም ቅድሚያ የሚሰጥበት ወቅት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የሌሎች እምነት ተከታዮችም የራሳችሁን እምነት እንደምታከብሩ ሁሉ የሌላውን እምነት ማክበር ተገቢ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡ መጀመሪያ ከራስ እምነት እኩል የሌሎችን ማክበር የሚገባ መሆኑን የጠቀሱት ሀጂ ኢብራሂም፤ የሌላውን እምነት ሳያከብሩ ግን እምነቴን አከብራለሁ ማለት ትክክል አለመሆኑን አስረድተዋል።

ቤተክርስቲያን እየተቃጠለ መስጊድ አይነካም ማለት ዘበት፤ መስጊድ እየተቃጠለ ቤተክርስቲያን አይነካም ማለትም አይቻልም ያሉት ፕሬዚዳንቱ ሁሉም ተከባብሮ ተባብሮ ተቻችሎ መኖር ይገባዋል ብለዋል።

አንድ ሀገር ውስጥ አንዱ ጎጂ አንዱ ተጎጂ ሆኖ አሸናፊ ይኖራል ማለት እንደማይቻል ተናግረው ደም እየፈሰሰ ባለበት ሀገር ሰላም ይኖራል ማለት ስህተት መሆኑን አስረድተዋል።

ሰው የሰው ልጅ በመሆኑ ብቻ ክቡር መሆኑን በእስልምና አስተምህሮት ውስጥ መኖርን ጠቅሰው ሰው በሃይማኖቱ ሳይሆን ሰው በመሆኑ ብቻ ተከብሮ መኖር ይገባዋል ብለዋል። በሃይማኖት መነጣጠል፤ በማንነት ደም መፋሰስ ይበቃል ፤ በሰላም ተከባብረን ተፈቃቅረን እንደተለመደው እንኑር በማለትም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።ኢፕድ

ተራዝሟል
21/07/2022

ተራዝሟል

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ዋናው ጽ/ቤት  ቅጥር ግቢ ውስጥ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላና የጽዳት ዘመቻ መርኀ ግብር ስለሚደረግ በቦታው በመገኘት እንድትሳተፉ እንጋብዛለን...
19/07/2022

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ዋናው ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላና የጽዳት ዘመቻ መርኀ ግብር ስለሚደረግ በቦታው በመገኘት እንድትሳተፉ እንጋብዛለን።

ቀን:- ሐምሌ 16 /17
ቅዳሜ እና እሁድ
ሰዓት:- 2፡00 - 6:00

አዘጋጅ:- የ ኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ርክክቡ ተጠናቋል !!
18/07/2022

ርክክቡ ተጠናቋል !!

18/07/2022

Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.
የህዝበ ሙስሊሙ የዘመናት ጥያቄ የሆነው የጠንካራ ተቋም ባለቤትነት ጥያቄ እልባት እንዲያገኝ የተጀመረው ሂደት ዛሬ በሸራተን አዲስ አዲስ ምዕራፍ እና አዲስ ተስፋ የሚሰጥ ሂደቶችን እያለፈ ይገኛል::
የህዝበ ሙስሊሙ ተቋም ህዝብን የሚያገልግል እንጂ መገልገያ እንዳይሆን በህግ እና በስርዓት እንዲመራ ማድረግ ለተቋሙ የጥንካሬ ምንጭ መሆኑ አያጠያይቅም::
ሁለተኛው አገር አቀፍ የተቋማዊ ለውጥእና የሙስሊሙ አንድነት ጉባኤ በሸራተን አዲስ ተስይሞ ምክክር እያደረገ ሲሆን የዚህ ጉባኤ ውጤት ባለፉት ሶስት አመታት የባከኑ ጉዜያቶችን የሚክስ እና ህዝበ ሙስሊሙን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቋማዊ አንድነቱን የሚያፀናበት እንዲሚሆን ይጠበቃል::
ህዝበ ሙስሊሙ የዘመናት የጠንካራ ተቋም ጥያቄው በግለሰቦች እጅ የሚንጠለጠል እንዳይሆን በቀጣይም በአዲስ መንፈስ እና አንድነት ተቋሙን የሚመሩ አመራሮች የተሰጣቸውን ሃላፊነት በሚገባ እንዲወጡ በቅርበት ሊከታተል ይገባል::
እንደዚህ ቀደሙ ጊዜ እና ምክንያት በመስጠት ተቋም አልባ እንዲሆን ሊፈቅድ አይገባም::
ህዝበ ሙስሊሙ በህግ እና በስርዓት የሚመራ፣ ሁሉንም ሙስሊሞች በአባትነት አቅፎ የሚይዝ ጠንካራ ተቋም የመገንባቱ ሂደት ለስኬት ይበቃ ዘንድ ሁሉም በሚችለው ሊረባረብ እና ዱዓ ሊያደርግ ይገባል::

መግለጫው ተሰቷል በዝርዝር በኋላ እንመለስበታለን ።
18/07/2022

መግለጫው ተሰቷል በዝርዝር በኋላ እንመለስበታለን ።

18/07/2022

አሁን በሰማነው መረጃ መሰረት በዛሬው እለት የተመረጠው አዲሱ መጅሊስ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል ።

18/07/2022

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለቀጣይ 3 ዓመታት የሚመሩ ኃላፊዎች በዛሬው ሐምሌ 11/2014 እየተካሄደ ያለው ጉባኤ መረጠ::
ሸኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ፕሬዝዳንት
ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን ም/ፕሬዝዳንት
ሸኽ አብዱልአዚዝ ም/ፕሬዝዳንት
ሸኽ ሀሚድ ሙሳ ፀሀፊ

18/07/2022

ከ300 ተሳታፊዎች 261 ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የአመራሮች ምርጫ እየተካሄደ ነው።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የአመራሮች ምርጫ እየተካሄደ ነው።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቋማዊ ለውጥና አንድነት 2ኛ ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል።

በጉባኤው ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን መጂሊሱን ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የሚመሩ አመራሮች ምርጫም በመካሄድ ላይ ነው።

በጉባኤው ላይ በድምፅ ይሳተፋሉ ተብለው ከሚጠበቁት 300 ተሳታፊዎች መካከል ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ 261ዱ መገኘታቸው ታውቋል።

ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በተካሄደው ጉባኤ ከተሳተፉት መካከል 39ኙ በሞት፣ በህመም፣ ከሀጂ ጉዞ ባለመመለስና በልዩ ልዩ ምክንያቶች በዛሬው ጉባኤ አለመገኘታቸውም እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቋማዊ ለውጥና አንድነት 1ኛ ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ መካሄዱ ይታወሳል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

18/07/2022

ዛሬ እየተካሄደ የሚገኘው የሸራተኑ ጉባኤን አስመልክቶ
------------
ስብሰባው የሚመለከታቸው ከሁለቱም በኩል ያሉ ዑለማኦችና አስተባባሪዎች እንዲሁም የመንግስት አካላት በሸራተኑ ስብሰባ ታድመዋል።

አካባቢው ልዩ የሆነ ጥበቃ እየተደረገለት በመሆኑ ከፍል ውሀ መስጂድ ጀምሮ በሸራተን ወደ አራት ኪሎ መዞሪያ የሚወስደው መንገድ ለተሽከርካሪም ሆነ ለእግረኛ ዝግ ተደርጓል። በፍል ውሀ ዙሪያም በርካታ የፌዴራል ፖሊሶች ይታያሉ።

ሚዲያን አስመልክቶ የትኛውም ሚዲያ መግባት ተከልክሏል ።

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Beder media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share