Humbo Tebela News

  • Home
  • Humbo Tebela News

Humbo Tebela News Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Humbo Tebela News, Media/News Company, .

"ዘላቂና አስተማማኝ ሠላምን ለማረጋገጥ የኃይማኖት ተቋማት ሚና የጎላ ነው!"  የጠበላ ከተማ አስ/ር ከንቲባ አቶ ዮሐንስ ቡናሮየጠበላ ከተማ አስ/ር የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሠራርና አደረጃ...
18/05/2023

"ዘላቂና አስተማማኝ ሠላምን ለማረጋገጥ የኃይማኖት ተቋማት ሚና የጎላ ነው!" የጠበላ ከተማ አስ/ር ከንቲባ አቶ ዮሐንስ ቡናሮ

የጠበላ ከተማ አስ/ር የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሠራርና አደረጃጀት እና የኃይማኖት ነክ መልካም አስተዳደር ጉዳዮች እንዲሁም የከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ጉዳይ ዙሪያ የጋራ የውይይትና የምክክር መድረክ አካሄዱ።

የጠበላ ከተማ አስ/ር ፀላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ወቅታዊ የፀጥታ ነባራዊ ሁኔታ፣ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሠራርና አደረጃጀት እና የኃይማኖት ነክ መልካም አስተዳደር ጉዳዮችም እና በቀጣይ በቅንጅት መስራት ስለሚገባቸው ስራዎችን በተመለከተ የፀጥታ ስራዎች ማስፈፀሚያ ሰነድ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ዉይይት ተደርጓል።

የሀይማኖት ተቋማት ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ፣ የመቻቻል እና የአብሮነት እሴቶች እንዲጎለብቱ በማድረግ የአከባቢያችን ሰላምና ልማትን ለማረጋገጥ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን የጠበላ ከተማ አስ/ር ከንቲባ አቶ ዮሐንስ ቡናሮ ገልፀዋል።

አያይዘውም ሀይማኖቶች የተመሰረቱበት ዋና ዓላማ ሰላም በመሆኑ ለሰላም መረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የማድረግ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባልም ብለዋል፡፡

አቶ ዮሐንስ ቡናሮ አክለው ከተማውን ማልማት እና ማሳደግ ለከተማ አስተዳደር ብቻ የሚተው አይደለም ቤተ-እምነቶች በሰብዓዊ ድጋፍን ጨምሮ በአረንጓዴ አሻራ እና በሌሎች የልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተውጾ ማበርከት አለባቸው።

ከተማ አስተዳደሩ የጀመራቸው የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች በአስተዳደሩ ጥረት ብቻ ማሳካት ስለማይቻል የኃይማኖት ተቋማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ከንቲባው ጥሪ አቅርበዋል።

የጠበላ ከተማ አስ/ር ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ሻ/ም ለማ ቂልታ በበኩላቸው የከተማችንን ሰላም መጠበቅ ወሳኝ እንደሆነ በመገንዘብ ይህንን ሰላም በማስቀጠል ሁሉም ሃይማኖቶች በጋራ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ሻ/ም ለማ ቂልታ አክለው የከተማችንን ሰላም በዘላቂነት ከማስጠበቅ አንጻር ሁሉም የራሱን ድርሻ ሊወጣ ይገባል በማለት ሃይማኖትን ሽፋን ያደረጉ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ሠላምን በመሰበክና ስነምግባርን በማስተማር ሁሉም ሚናውን በተገቢው መወጣት ይገባል ብለዋል።

ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት በሚደረገው ርብርብ የሃይማኖት ተቋማት ሚና የጎላ በመሆኑ ይህ የሰላምና የጋራ የውይይት መድረክ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል በማለት የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ፎረም ሰብሳቢ አቶ አክሊሉ ሳሙኤል ገልፀዋል ፡፡

አቶ አክሊሉ ሳሙኤል አክለው የሃይማኖት ተቋማት ትውልዱን ከማነፅ ባለፈ ማህበረሰባዊ ትስስራችንንና ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን ለማጠናከር ስነምግባርንና ግብረ ገብነትን በማስተማር ረገድ ሰፊ ስራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

የኃይማኖት ተቋማት በቀጣይም ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩና ትውልድን በስነ-ምግባር በሚያንፁ ስራዎች ላይ አተኩረው እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

በመድረኩ ከየሃይማኖት ተቋማት የመጡ የእምነት አባቶች፣ ከዞን ሃይማኖት ተቋመት ተወክለው የመጡ የሃይማኖት አባቶች፣ ከዞን ሠላሞና ፀጥታ መምሪያ የተወከሉ አካላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

“ሰኔ 12/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ምርጫ በነቂስ ወጥተን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል”፡- መላው የወላይታ ህዝብሰኔ 12/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ምርጫ መላው የወላይታ ህዝብ በነቂስ ...
18/05/2023

“ሰኔ 12/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ምርጫ በነቂስ ወጥተን ለመምረጥ ተዘጋጅተናል”፡- መላው የወላይታ ህዝብ

ሰኔ 12/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ምርጫ መላው የወላይታ ህዝብ በነቂስ ወጥተው ለመምረጥ ከወዲሁ ዝግጁነታቸውን እየገለጹ ናቸው፡፡

ፀሐይና ብርድ ሳይበግረው ታሪክ ሰሪው ኩሪ መላው የወላይታ ህዝብ ሰኔ 12/2015 ዓ.ም የሚካሄደው ምርጫ በነቂስ ወጥቶ ለመምረጥ ተዘጋጅቷል፡፡

ቆሞ ቀሪዎችና ጨለምተኞች ከቤት አይወጡም! ፀሐይና ብርድ ሳይበግረው ታሪክ ሰሪው ኩሪ መላው የወላይታ ህዝብ ሰኔ 12/2015 ዓ.ም በነቂስ ወጥቶ ለመምረጥ ፍላጎታቸውን በስፋት እየገለጸ ይገኛል፡፡

በዚህም ምርጫ መላው የወላይታ ህዝብ የሴራኞችና የጽንፈኞች እኩይ ዓላማቸውን ለመከሸፍ ታጥቆ ተነስቷል፡፡ ከአሁን በኃላ በወላይታ ህዝብ ስም ነግደው ለመበላት የተዘጋጁ ባንዳዎች ለአንደና ለመጨረሻ በዚህ ምርጫ ይከትማል፣ ያበቃል፣ ይዘጋል፡፡

የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎበኙየህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎብኝተዋል።...
11/03/2023

የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎበኙ

የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት በወላይታ ዞን እየተሰራ ያለውን የተለያዩ ፕሮጀክቶች ጎብኝተዋል።

በክቡር አቶ መለሰ መና የተመራው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በወላይታ ዞን በበሌ ሀዋሳ ከተማ የሚገኘውን ኦሞ ሰው ሰራሽ ሀይቅ፣ በኦሞ ሰውሰራሽ ሀይቅ ላይ የሚገነባውን የሮማንና ሀይለማርያም ፋውንዴሽን እና የኢሊኮፕተር ማረፊያና በጉኑኖ ከተማ የሚገነባውን የከተማ ውስጥ ለውስጥ አስፓልት መንገድ ግንባታ ሂደትን ተዟዙረው ተመልክተዋል።

በጉብኝቱ የኢፌዴሪ ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታን ጨምሮ ከተለያዩ የወላይታ ዞን በህዝብ ተመርጠው በፌደራልና በክልል የህዝብ ተወካይ የምክር ቤት አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

ምርጫ ቦርድ የወላይታ ህዝብን ድምጽ ባላከበረ ሁኔታ የወሰነውን ውሳኔን ተከትሎ በከፍተኛ ፍርድቤት ቢከሰስ ህዝቡ እንደሚያሸንፍ ተገለጸየወላይታ ህዝብ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ፣ የድምጽ አ...
07/03/2023

ምርጫ ቦርድ የወላይታ ህዝብን ድምጽ ባላከበረ ሁኔታ የወሰነውን ውሳኔን ተከትሎ በከፍተኛ ፍርድቤት ቢከሰስ ህዝቡ እንደሚያሸንፍ ተገለጸ

የወላይታ ህዝብ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ፣ የድምጽ አሰጣጥና ውጤት በተመለከተ የወሰነው ውሳኔን ተከትሎ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ሰበር ችሎት ቢከሰስ እንደሚያሸንፍ የህግ ምሁራኖች ገለጹ።

ህዝበ ውሳኔው ጋር ተያይዞ ምርጫ ቦርድ የወጣው መግለጫ መራጩን መላው የወላይታ ህዝብንና የዞኑን መንግስትን እንደማይወክልና እንደማይመለከትም ጭምር አስታውቋል። ምክንያቱም የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥና ውጤት በተመለከተ ተዘርዝረው የተቀመጡ ነጥቦች በአጠቃላይ የምርጫ አስፈጻሚዎች ጉድለትና ጥሰት መሆኑ ያሳያልም ብሏል።

ከእነዚህም መካከል ለአብነቱ #የውጤት መግለጫ ቅጾችና የመራጮች መዝገብ ላይ ምርጫ አስፈጻሚዎች ፊርማቸውን በሠነዶቹ ላይ አለማሥፈራቸው" የሚለውን ብቻ ካየን በቂ ነው።

ይህ የወላይታ ህዝብን ለማሸማቀቅ የተቀናጀና የተቀነባበረ ሴራ መሆኑን ገልጿል። ለዚህም መላው የወላይታ ህዝብ ተስፋ ሳይቆርጥ የአይበገሬነት ወኔን በመላበስ ዳግሚ የሚካሄደው ምርጫ ታርክ መስራት ያስፈልጋል።

በቁጫ ህዝብ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ፥ ምርጫ ቦርድ ሆን ብሎ የምርጫ ውጤት እንዲሰረዝና እንዲካሄድ ህገወጥ ውሳኔን ተከትሎ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ሰበር ችሎት ተከስሶ የቁጫ ህዝብ ሰሞኑ ማሸነፉን በመጠቀስ ይህም የምርጫ ቦርዱ ገለልተኝነት አደጋ ላይ መውደቁን ተናግረዋል።

የወላይታ ህዝብ ከወንድም ህዝቦች ጋር በአንድ ክልል ለመደራጀት የወሰነውን ውሳኔን ለመቀልበስና የፖለቲካ ትርፍ ለመግኘት እየሰሩ ያሉ አጭበርባሪዎች መኖራቸውን ጠቅሷል።

አንድ ሚሊዮን ገደማ የሚጠጋ ህዝቡ ከለሊቱ 9:00 ጀምሮ ተሰልፎ እንዲሁም ብርድና ፀሐይ ሳይበግረው የሰጠው ድምጽ ምርጫ ቦርድ የወሰነው ውሳኔ እጅግ የሚቃረን ነው ብሏል።

የህዝበ ውሳኔ ድምጽ አሰጣጥ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ጥቃቅን ችግሮች ከዚህ በፍትም፣ ወደፊትም የሚካሄዱ ምርጫዎች የህግ ጥስት ሊኖሩ እንደሚችል አንስቷል።

በአጠቃላይ አንድ ምርጫ ልሰራዝ የሚቻለው ሠላማዊ፣ ነጻ፣ ገለልተኛ እና ፍታሃዊ ሆኖ ሳይጠናቀቅ ስቀር እንደሆነም ጠቁመዋል።

በመጨረሻም አንዳንድ ጽንፈኞችና የፀረ-ሠላም ኃይሎች አጀንዳ ለማስፈጸምና የወላይታን ገጽታ ለማበላሸት በማህበራዊ ሚዲያ ሀሰተኛና የተዛቡ መረጃዎችን የሚሰራጩ አካላት ላይ መንግስት የማይዳገም እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ጠይቀዋል።

28/01/2023

በወላይታ ዞን ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል

ወላይታ ሶዶ፤ ጥር 19/2015 በተያዘው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ ከ1 ቢሊዮን 349 ሚሊዮን በላይ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ በተያዘው ዓመት ስድስት ወራት በኢንዱስትሪው ዘርፍ 49 ኢንቨስትመንቶችን ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዶ 34 ኢንቨስትመንቶችን መሳብ ተችሏል።

በዚህም በዞኑ አንድ ቢሊዮን 349 ሚሊዮን በላይ ብር ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡

አቶ አክሊሉ እንደገለፁት፣ በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ሁለት ቢሊዮን የሚጠጋ ካፒታል ያላቸውን ባለሀብቶች ወደ ዞኑ ለመሳብ ሲሠራ የቆየ ሲሆን፤ ከ1 ቢሊዮን 349 ሚሊዮን ብር በላይ ኮፒታል ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ወደ ሥራ መግባት ችለዋል።

ወደ ሥራ ገብተዋል ከተባሉት 34 ኢንቨስትመንቶች 18 ያህሉ በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ መሆናቸውን ያብራሩት አቶ አክሊሉ፤ ሌሎች 11 የአገልግሎት እና 5 የሚሆኑ ደግሞ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፎች ወደ ሥራ ገብተዋል ሲሉ አስረድተዋል።

በገጠሩ አካባቢ 500 ሄክታር መሬት ለኢንቨስተሮች ለማቅረብ ታቅዶ ከአንድ ሺህ 500 በላይ ሄክታር መሬት ማቅረብ መቻሉንና በከተማው አካባቢ በካሬ የነበረውን ወደ ሄክታር በመቀየር አምስት ሄክታር መሬት ለማቅረብ ዕቅድ ተይዞ ከስምንት ሄክታር በላይ መሬት ለኢንቨስተሮች አቅርቦት መዋሉንም አክለው አብራርተዋል፡፡

የኢንቨስትመንት ሌላኛው ዓላማ የሥራ ዕድል መፍጠር ነው ያሉት አቶ አክሊሉ፤ ለ10 ሺህ 51 ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የታቀደ ሲሆን፤ ከስድስት ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል አግኝተዋል ሲሉ አስረድተዋል።

መሬት ከተሰጣቸው በኋላ የተለያዩ ምክንያቶችን በማንሳት በሚፈለገው ፍጥነት ወደ ሥራ የማይገቡ ኢንቨስተሮች እንዳሉ በመግለጽም፤ ወደ ሥራ ገብተው ማልማት ከጀመሩ በኋላ የሚያቋርጡ መኖራቸውን ጠቅሰዋል።

ይህን ድርጊት በሚፈጽሙ ባለሀብቶች ላይ የማስጠንቀቂያና የተቀበሉትን መሬት በመንጠቅ በተገቢ ሁኔታ ለሚያለሙ ባለሀብቶች እየተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል ሲል ኢፕድ ዘግቧል።

28/01/2023
28/01/2023

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህዝበ ዉሳኔ ልዩ ምልክት ነጭ እርግብ ነዉ።

በካዎ ኮይሻ ወረዳ ከ1.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው ንጹህ መጠጥ ውሃ ተመርቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠት ጀመረየካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር ከወላይታ ልማት ማህበር ጋር በመተባበ...
28/01/2023

በካዎ ኮይሻ ወረዳ ከ1.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው ንጹህ መጠጥ ውሃ ተመርቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር ከወላይታ ልማት ማህበር ጋር በመተባበር ለዘመናት የህዝብ መልካም አስተዳዳር ጥያቄ ሆኖ የቆየው የንፁህ የመጠጥ ውኃ ጥያቄ ተመርቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ግንባታው ከ1.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ ሲሆን 1970 ህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ ተገኝቶ መልክት ያስተላለፉት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ እንዳሉት የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር በመቅረፍ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

የወላይታ ልማት ማህበር በዞኑ በ23 መዋቅሮች የተለያዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየቀረፈ የሚገኘ የህዝብ አለኝታ የሆነ ማህበር ነው ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው ለሰው ልጆች ከሚያስፈልጉ መሰረታዊ ጉዳዮች አንዱና ዋነኛው የንፁህ መጠጥ ውሃ መሆኑን አስረድተዋል።

የወረዳው የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በገዥ ፓርቲ እና በመንግሥት አማካኝነት በየደረጃው እንደሚፈታ አስገንዝበዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳንኤል መና በበኩላቸው ለቡዙ ዓመታት የህዝብ ጥያቄ የሆነው ንፁህ መጠጥ ውኃ ጥያቄ ምላሽ ማግኘት መቻሉን ገልጸዋል።

አቶ ዳንኤል አያያዘውም የወላይታ ልማት ማህበሩ ላደረገው አስተዋጽኦ በወረዳው አስተዳደርና በህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

በፕሮግራሙ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ፣ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ፣ የወረዳ አጠቃላይ አመራር፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ የአከባቢው ማህበረሰብና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል።

የወላይታ ህዝብ ጠላትና ባንዳ ነውይህ ከታች በፎቶ የምትመለከቱት   Ferenj ይባላል። በአሜሪካ ሀገር የሚኖር ሲሆን የ  Times ፔጅ ከሶስት አድሚኖች አንዱ እሱ ነው።ይህ ግለሰብ ሰሞኑን...
03/01/2023

የወላይታ ህዝብ ጠላትና ባንዳ ነው

ይህ ከታች በፎቶ የምትመለከቱት Ferenj ይባላል። በአሜሪካ ሀገር የሚኖር ሲሆን የ Times ፔጅ ከሶስት አድሚኖች አንዱ እሱ ነው።

ይህ ግለሰብ ሰሞኑን በትርፍ ሰዓት ወላይታ ታይምስ ፔጅ ላይ Live እየገባ የዳጋቶ ኩምቤን ሹመት በይፋ እየተቃወመና ወላይታ ህዝብን የማይመጥን ቃላት በመጠቀም እየተሳደበ ስናገር ሰምተናል።

የወላይታ ህዝብን የዘረፈውንና ንጹሃን እንዲሞቱ ያደረገው #ለዳጋቶ ኩምቤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምን ሹመት ሰጠ ብሎ እየተቃወመ ይገኛል። ይህ ወሸት ከሆነ Ferenj በሚለው አካውንት ከፍታችሁ Video ማየት ትችላላችሁ።

የ ፔጁ አድሚኖች ለግል ጥቅማቸውን ለማሳከት ሀሰተኛና ጥላቻ ንግግር የሚያሰራጩ በመሆናቸው የወላይታ ህዝብ ጠላት መሆናቸውን በይፋ አስመስክረዋል፤ ህዝቡም ማወቅ ያስፈልጋል።

እነኚህ አካላት በህዝብ ስም የሚነግዱና የህዝቡን ዕድገትና ልማት የሚቃወሙ ናቸው። ወላይታ ህዝብ የማንም መጫወቻና መላገጫ አይደለም። ገንዘብ ለማግኘት ብሎ በህዝቡ ላይ እየማገጡ ይገኛሉ። መጀመሪም ዓለማቸው ይህ ነበረ።

ጀግናው የወላይታ ህዝብ ክፉንና ደጉን ለይቶ የሚያወቅ እስከዛሬ ለጸንፈኛ ሀይሎች አጀንዳ ጆሮ ሳይሰጡ በማንኛውም ጊዜ ከመንግሥት ጎን በመሆን ለሀገራችን ልማት እና ዕድገት እየታገሉ የቆዬ ልማትን ብቻ ትኩረት የሚያደረጉ ኩሩ ህዝቦች ናቸው።

ማንም ቱርናፋ በጮሄበት የሚመጣ አንዳች ነገር የለም፣ አንተ አሜሪካ ቁጭ በለህ ወላይታን የትርምስ ቀጠና ለማድረግ የሚትሞክር አስመሳይ ለማኝ መሆንህን ህዝቡ አውቀዋል።

  ፔጅ አድሚኖች መንግስትን ደግፎ ከመጻፍ በአንዴ ወደ ተቃውሞ ለምን ተቀየሩ?የፔጅ አድሚኖች (Admin) አሁን ሶስት ሲሆኑ ሁለቱ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ፣ አንዱ ደግሞ ከሀገር ውጪ አሜርካ...
02/01/2023

ፔጅ አድሚኖች መንግስትን ደግፎ ከመጻፍ በአንዴ ወደ ተቃውሞ ለምን ተቀየሩ?

የፔጅ አድሚኖች (Admin) አሁን ሶስት ሲሆኑ ሁለቱ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ፣ አንዱ ደግሞ ከሀገር ውጪ አሜርካ ላይ ይገኛል።

ከዚህ በፊት በፔጁ የመንግስት፣ የግለሰቦች፣ የግል ኮሌጆችንና የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ መረጃዎችን Copy Paste እያደረጉ ሲሰራጩ መቆየታቸውን ለማንም ሀቂ ነው።

አሁን በፔጃቸው የተዛቡ፣ ጥላቻ ምንጩ ያልተረጋገጠና ሀሰተኛ መረጃዎችን ማሰራጨት መጀመራቸውን ለህዝቡ ጥቅም ወይስ ለራሳቸው ጥቅም ነው የሚለውን ብዙዎች ማወቅ ያለበት ጉዳይ ነው። ምክንያቱም

1. ባለፉት አራት ዓመታት ከዛም ከዚህም በማጭበርበር ያለአግባብና በግፍ የመንግስትን ንብረት ስዘርፉ ነበር

2. በፔጁ አድሚኖች መካከል አንዱ ናትናኤል ገቾ የሚባለው ግለሰብ በሀሰተኛ ብር ዝውውር እጅ ከፍንጅ ተይዞ ከ11 ቀን በላይ ታስሮ ከተፈታ በኃላ ጥፋቱን እና ወንጀሉን አምኖ ህዝብን እና መንግስት ይቅርታ መጠየቅ ሲገባው ህዝብን እና መንግስትን መወንጀሉ

3. የማህበረሰብ አቀንቃኝ በማለት ከተለያዩ ድርጅቶች ለዚህ የሚመደበውን ገንዘብ ለማገኘት አዲስ የዘየዱት ዕቅድ መሆኑን፤

4. ከዚህ በፊት የህወሓት ደጋፊ ናቸው ብሎ በየአካባቢው ያሉ ወጣቶችን ጥቆማ ሰጥቶ እንዲታሰሩ ትልቅ ሚና የተጫወተ ሲሆን አሁን ያንን መጥፎ ስም ለመኸፈን ታስቦ የሚሰራ ሥራ መሆኑ

5. እንዲሁም ከዚህ በፊት ከህዝቡ ያጣውን ቅቡልነት መልሶ ለማገኘት፤

6. ከፀረ-ሠላም ኃላይሎች ጋር በመተባበር የኢኮኖሚ ፍላጎትን ለሟሟላት እና በማህበረሰቡ ውስጥ አዳዲስ አሉታዊ ክስተቶችን ለመፍጠር

7. በአጠቃላይ አሁን መንግስት የያዘው አቋም ተገንዝቦና ተስፋ ቆርጦ ወላይታን ገጽታ ለማበላሸትና የአፍራሽ ኃይሎች ተልዕኮን በማሰራጨት የሁከትና ብጥብጥ ቀጠና ለማድረግ አቅደው እየሰሩ ስለሆነ ህዝቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

ለግል ፍላጎታቸውን ጥቅም ለማግኘት ታላቁን የወላይታ ህዝብን እና የአከባቢውን ማ/ሰብ የሚያሸብሩ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን በመረዳት ህዝቡ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።

መላው የወላይታ ህዝብና ሌሎችም የኢትዮጵያ ህዝቦች የሚለውን ፔጅ ተከታይ የሆነ ሁሉ ፔጁን block, unlike & unfollow በማድረግ በንቅናቄው እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

የWolaita Times ሚዲያ ባለቤቶች ለወላይታ ህዝብ ጠላት መሆናቸውን በይፋ አውጀዋል።ምክንያቱ እንኳን ባይታወቅም በሀገር ደረጃ ለምን የወላይታ ስም በልማትና በሌሎች ነገሮች ይታወቃል ብለ...
28/12/2022

የWolaita Times ሚዲያ ባለቤቶች ለወላይታ ህዝብ ጠላት መሆናቸውን በይፋ አውጀዋል።

ምክንያቱ እንኳን ባይታወቅም በሀገር ደረጃ ለምን የወላይታ ስም በልማትና በሌሎች ነገሮች ይታወቃል ብለው ስም የማጥፋት ዘመቻ ጀምረዋል። ለዚህ ማሳያ አሁን በገጹ በአጋሩት መረጃ ማወቅ ተችሏል።

እነዚህ አካላት በወላይታ ህዝብ ላይ ጦርነትና ያልተገባ ሁከትን ለመፍጠር ከፀረ-ሠላም ኃይሎች ተልዕኮን ተቀብሎ ሰሞኑን እንቅስቃሴ ጀምረዋል። ከዚህ በፊት 38 ንጹሃን እንዲሞቱ ከፍተኛ ተሳትፎ ያደረጉ መሆናቸው መላው የወላይታ ህዝብ ህያው ምስክር ናቸው።

ለወላይታ ህዝብ ልማት፣ ሠላምና ለውጥ አያስፈልግም፣ ህዝቡ መለወጥ የለበትም እያሉ አሉታዊ ተጽዕኖን ለመፍጠር በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ የጀመሩ ሲሆን እስካሁን አልተሳካላቸውም፣ ወደፊትም አይሳካላቸውም። ለዚህ ደግሞ ጀግናው የወላይታ ህዝብ የፀረ-ሽብርተኝነት ተግባር አይሸከምም።

በወላይታ ዞን ብላቴ አከባቢ ከኢትዮጵያ አልፎ ለዓለም የሚበቃ የፍራፍሬ ምርት እየተመረተ ያለውን እየተቃወሙ ይገኛል።

መላው የወላይታ ህዝብና ሌሎች ኢትዮጵያ ህዝብ የሚለውን ፔጅ ተከታይ የሆነ ሁሉ ፔጁን block, unlike & unfollow በማድረግ በንቅናቄው እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።

ቀሪ ዝርዝር መረጃውን ይዘን እንመለስበታለን!

በወላይታ ዞን "የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መመስረት መሠረታዊ መርሆች" በሚል በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነውበወላይታ ዞን "የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል" መመስረት መሠረታዊ እሳ...
28/11/2022

በወላይታ ዞን "የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መመስረት መሠረታዊ መርሆች" በሚል በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

በወላይታ ዞን "የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል" መመስረት መሠረታዊ እሳቤዎችና የህዝበ ውሳኔ ምልክት ማስተዋወቂያ ዞናዊ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ እንደተናገሩት ህዝበ ውሳኔው ስኬታማ እንዲሆንና በክልል አደረጃጀት የሚኖራቸውን ተሳትፎን ግልጽ ለማድረግ የሚያስችል መድረክ ነው ብለዋል።

የመራጮች ድምጽ ሰጪ የሚመዘገቡበትና ቅስቀሳ ሥራ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው ጊዜ ሰሌዳ መሠረት እንደሚከናወን አስታውቀዋል።

የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ገለጻ እያደረጉ ናቸው።

በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ውይይት ተደርጎ የጋራ መግባባት ላይ ይደረሳል ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩ የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞኑ አጠቃላይ አመራርና የወረዳና ከተማ አስተዳደር አስተባባሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ከወረዳ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረሙየወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ ከወረዳ...
20/10/2022

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ከወረዳ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራረሙ

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ ከወረዳ/ከተማ ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በቀጣይ የሚሰሩ ቁልፍ ተግባራት ላይ የውል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

የግብ ስምምነቱ ዓላማው የፓርቲ እና የመንግስት ተግባራት ላይ የነበሩ ጉድለቶችን በማካካስ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው ሲሉ የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ በየነ ገልጸዋል፡፡

አመራሩ ህዝቡና በማሳተፍ ፓርቲያችን የሰነቀውን ራዕይ እውን ለማድረግ ጊዜ የለኝም በሚል ቅኝት ተግባሩን መመራት እንደሚገባ አመላተክዋል፡፡

ህዝባችንን መካስ የሚንችለው የተሰጠንን ተግበር ቆጥረን መሰራት ስንችል ብቻ ነው ያሉት አቶ ዮሐንስ ለዚህም አመራሩ ተግባራትን ለማሳካትና ለማሳለጥ ቁርጠኛ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡

አመራሩ በቀጣይ ወራት ዉስጥ ትኩረት ሊያደርግባቸው በሚገቡ ተግባራት ላይ በተደራጀና በተቀናጀ ሁኔታ መንቀሳቀስ እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

በሁሉም ተቋማት ጠንካራ ፓርቲን የመትከል ሥራ መስራት እንደሚገባ ያሳሰቡት ኃላፊው ተግባራት በአደረጃጀት መመራት እንዳለባትም አስገንዝበዋል፡፡

በእያንዳንዱ ዘርፍና በሁሉም ሥራ መስኮች ያቀድናቸውን ተግባራት ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት ቁርጠኛ ሆነን ስርተን የብልጽግናችንን ጉዞ እውን ማደረግ ይጠብቅብናል ብለዋል፡፡

በሰነዱ ደረጃ ግብ ተጥለው በተፈራረመነው መሠረት በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በጤናው፤ በትምህርት፤ በግብርናና በሌሎች ሥራ መስኮች አንድ በአንድ ተቆጥረው መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

በተዋረድ የወረዳ/ከተማ ፊት አመራሮች እስከ ቀበሌ ድረስ ለስራዉ አጋዥ ከሚሆኑ ሀይሎች ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረም በተቀመጣው ጊዜ ሠለዳ ውስጥ ተግባራት በጥብቅ ዲስፕሊን መምራት እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው "ጊፋታ" በዓል በድምቀት እንዲከበር የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የሀይማኖት መሪዎች ተናገሩየወላይታ ዞን አስተዳዳሪ የዘንድሮው ጊፋታ በዓልን በድምቀ...
14/09/2022

የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው "ጊፋታ" በዓል በድምቀት እንዲከበር የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ የሀይማኖት መሪዎች ተናገሩ

የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ የዘንድሮው ጊፋታ በዓልን በድምቀት ለማከበርና ህዝባዊ በዓል እንዲሆን ከሁሉም አከባቢዎች የተወጣጡ ሀይማኖት መሪዎች ጋር ተወያይቷል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ ባስተላለፉት መልዕክት ጊፋታ በወላይታ ብሔር ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው በዓል መሆኑን ገልጸዋል።

ጊፋታ በዓል ከሃይማኖታዊ በዓል ጋር የማይገናኝ መሆኑን የሀይማኖት መሪዎች በየእምነታቸው ማስተማርና ማስገንዘብ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የወላይታ ማንነታችን ለማሳወቅ ከያዝናቸው ባህሎች አንዱና ዋነኛው ጊፋታ በዓል እንደሆነ ያስረዱት ዋና አስተዳዳሪው ባህላችንን ለማሳወቅ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች ድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ጊፋታ የህዝባችንን አንድነትና አብሮነትን ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለው ዋና አስተዳዳሪው አስታውቀዋል።

የመስቀል በዓልና የጊፋታ በዓል በአንድ ሰሞን የሚከበር እንደሆነ የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ጊፋታ በየትኛዉም መመዘኛ ኃይማኖታዊ በዓል ሊሆን አይችልም ብለዋል።

በበዓሉ ህዝቡ ፈጣሪን የሚያመሰግንበት እንደሆነ ያስረዱት ዋና አስተዳዳሪው ከሩቅ ቦታ ያሉ ተሰብስቦ አብሮ የሚያከብሩት በዓል ነው ብለዋል።

የማህበረሰቡ የጋራ ሀብት የሆነው የጊፋታ በዓል ባህላዊ እንጂ ኃይማኖታዊ እንዳይደለ በአጽንኦት ገልጸዋል።

የዞኑ ባህልና ቱርዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾመ ሀብቴ በበኩላቸው "ጊፋታ" ለወላይታ ህዝብ የአሮጌ ዓመት ማብቅያና የአዲስ ዓመት መቀበያ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ጊፋታ በዓል የወላይታ ህዝብ ቅርስ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊው ጊፋታን በማይዳሰስ ቅርስ እንዲናስመዘግብ ሁሉም ሰው ድርሻውን ልወጣ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

አንዳንድ ብሔር የራሱ የሆነ የዘመን መለወጫ በዓል እንዳለው ሁሉ ለወላይታ ህዝብ ጊፋታ በዓል የዘመን መለወጫ የማንነት መግለጫ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

ጊፋታ በዓል የሚከበርበት ቀን ከምንም ባዕድ አምልኮ ጋር እንደማይገናኝ ኃላፊው ገልጸዋል።

"ህዝቡና አመራሩ አንድነትን ፈጥረው ከሰሩ የምናልመውን ብልጽግናን በአጭሩ ጊዜ ማረጋገጥ እንችላለን"፦ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ የቆላማ አካባቢ ምርምርና ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር እንድ...
19/08/2022

"ህዝቡና አመራሩ አንድነትን ፈጥረው ከሰሩ የምናልመውን ብልጽግናን በአጭሩ ጊዜ ማረጋገጥ እንችላለን"፦ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ

የቆላማ አካባቢ ምርምርና ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ ይህንን ያሉት በቦሎሶ ቦምቤ ወረዳ በትምህርት ዘርፍ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ግለሰብ የማበረታቻና የዕውቅና አሰጣጥ ሥነ ሥርዓትና በህዝቡ ተሳትፎ የተሰሩ የልማት ስራዎችን በጎበኙበት ወቅት ነው።

በወረዳው በአጭር ጊዜ ውስጥ የታዬ ለውጦች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ዶ/ር እንድሪያስ አሳስበዋል።

በእውቀትና በስነምግባር የታነፀ ዜጋን ለማፍራት ትምህርት ዘርፍ ላይ በልዩ ሁኔታ መስራት ያስፈልጋል ያሉት ዶ/ር እንድሪያስ ለዚህም የትምህርቱ ዘርፍ አመራሮች ሚና የላቀ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

የወረዳው ህዝብ ከአመራሩ ጋር በመተባበርና በመቀናጀት አመርቂ ውጤቶች ማየት ችለናል ያሉት ዶ/ር እንዲሪያስ ለሌሎች አከባቢዎችም ምርጥ ተሞክሮ የሚሆኑ ስራዎች መኖራቸውን ተመለክተናልም ብለዋል።

የዞኑ ም/አስተዳደርና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ዳዊት በንግግራቸው ለዕድገትና ለብልጽግናም መሠረቱ ትምህርት ነው ብለዋል።

አመራሩና ህዝቡ ተግባብቶና ተቀናጅተው እንዲሁም አንድነቱ ፈጥረው ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማምጣት መረባረብ እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

በወረዳው በህዝቡ ተሳትፎና በአመራሩ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት ተስፋ ሰጪ ለውጦች መመዝገቡ የሚደነቅና የሚበረታታ ነው ብለዋል።

የወላይታ ህዝብ ለትምህርት የሚሰጠው ቦታ ልዩ ነው ያሉት መስፍን በትምህርት ለሀገር ለህዝብ የሚጠቀም ዜጋን ለማፍራት በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አስታውቀዋል።

የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደሴ ኩማ በበኩላቸው በዞኑ በትምህርት ተደራሽነት ላይ አመርቂ ውጤቶች መመዝገብ መቻሉንም ተናግረዋል።

በትምህርት ተቋማት የላቀ አፈጻጸም የፈጸሙና ያስፈጸሙ አካላት የማበረታቻ ሰርተፊኬት የሚስጠት ተሞክሮ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደሴ ዘካሪያስ እንዳሉት ትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚቻለው የሁሉም ባለድርሻ አካላት ብርቱ ጥረት የሚፈልግ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል።

የወረዳው ህዝብ በልማቱና በሁሉም ዘርፎች እያደረገ ላለው ድጋፍና ትብብር በወረዳው አስተዳደር ስም አመስግነዋል።

የብልጽግና ፓርቲ  ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ስብሰባ አጠናቀቀ። ማዕከላዊ ኮሚቴው በሀገራዊ የሰላምና ደህንነት፣ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዳዮች ላይ በጥልቀ...
26/06/2022

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ስብሰባ አጠናቀቀ።

ማዕከላዊ ኮሚቴው በሀገራዊ የሰላምና ደህንነት፣ የልማትና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በሗላ የተለያዩ አቅጣጫዎችን በማሳለፍ ውይይቱን አጠናቋል።

26/05/2022
01/03/2022
21/02/2022

ከጦርነት አሰተሳሰብ ውስጥ እንውጣ - የቀድሞው ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ያስተላለፉት መልዕክት

18/02/2022

ኢትዮጵያ የምትበለጽገው እኛ አገራችንን ለመለወጥ በፈለግንበት መጠንና የጋራ ራዕይ በሰነቅንበት ልክ ብቻ ነው፡፡ኢትዮጵያ ካዘመመችበት ቀና የምትልበት ጊዜው አሁን ነው፤ይህን ለማሳካት የዛሬ ህያው ኢትዮጵያዊያን ታላቅ አደራ ተጥሎብናል፡፡ይህንን አደራ ጠብቀን የዘመናት በጎ ድምር ውጤቶችን አጎልብተን ኢትዮጵያ የተባለችውን መርከብ ሞተሯን አድሰን ማዕበል ወጀቡ ፈፅሞ እንዳያናውጣት እና እንድትጓዝ ማድረግ ደግሞ የየትውልዱ የኢትዮጵያ ልጆች አደራ ይሆናል፡፡

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Humbo Tebela News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share