04/07/2022
| ሰበር ዜና
"ከንቲባው ቃላቸውን ሰተዋል"
============================
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን በህዝብ አመኔታ እንዲያጣ አድርገሀል" በሚል ምክንያት በእስር ላይ የሚገኘው አቶ በቃል ምስጋናው ለሶስትኛ ጊዜ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀረበ። በቃል ምስጋነው ከጠበቃው አቶ እንድሪያስ ተካልኝ ጋር ችሎት የቀረበ ሲሆን ችሎቱም ከአሁን ቀደሙ በተለየ በፖሊስ እና በጠበቃው መካከል ክርክር የተደረገ ሲሆን ክቡር ፍርድ ቤቱም የሁለቱንም ሀሳብ ተከታትሏል።
ፖሊስ ተለዋጭ ቀጠሮ የጠየቀ ሲሆን ምክንያት ብሎ ያቀረበውም "የባለስልጣናትን ቃል መቀበል ፣ የባንኮች መልስ እንዲሁም የፎረንሲክ ምርመራ ሪፖርቶች ውጤት ስላልደረሰኝ ተጨማሪ ቀጠሮ ይሰጥልኝ" ሲል ለችሎቱ አቅርቧል። ፖሊስ ከዚህ ጋር አያይዞ ቃላቸውን የተቀበላቸው የተወሰኑ የመስተዳደሩ ባለስልጣኖች እንዳሉ ጠቅሶ ከእነሱም ውስጥ የመስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር አንዱ መሆናቸውን አሳውቋል።
ከንቲባ አቶ ከድር ከአሁን ቀደም በመስተዳደሩ የስብሰባ አዳራሽ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የበቃል ምስጋናው እስር ከእሳቸው ውጪ እንደሆነ ቢናገሩም ከፍርድ ቤቱ ሂደት መረዳት እንደተቻለው ጉዳዩ በቀጥታ ከእሳቸው እና ከተለያዩ የከተማ አስተዳደሩ ባለስልጣናት ጋር እንደሚገናኝ ለመረዳት መቻላቸውን በስፍራው የተገኙ የአቶ በቃል ምስጋናው ቤተሰቦች እና ወዳጆች የገለፁ ሲሆን አክለውም ይህ ጉዳይ ግለሰባዊ እንዳይሆን ከፍተኛ ጥርጣሬና ስጋት እንዳደረባቸው ዘጋቢያችን ከስፍራው ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል። ፍርድ ቤቱም ለሐምሌ7 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።
------ DMN ------
Like our page ➣
DMN
Subscribe to our YouTube Channel ➣
https://youtube.com/channel/UC346TY8iLQi5vjjDnqu5ryg
Join our Telegram Channel ➣
https://t.me/diremedianetwork።