Jobiraw .com

Jobiraw .com Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Jobiraw .com, News & Media Website, .

09/10/2022

ሕወሓት ለትግራይ ህዝብ በዕርዳታ የመጣ መድሃኒትን ዘርፏል

አሸባሪው ሕወሓት በመቀሌ የሚገኘውን የዓለም ጤና ድርጅት /WHO/ የመድሃት መጋዘን በመዝረፉ እና መድሃቱን ለተዋጊዎቹ እንዲውል በማድርጉ የመቀሌ ሕዝብ በከፍተኛ የመድሃት ችግር ውስጥ መግባቱን መረጃዎች አለመከቱ፡፡

ከመቀሌ እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ህወሓት መቀሌ የሚገኘውን የዓለም ጤና ድርጅት /WHO/ መጋዘን ሙሉ ለሙሉ ዘረፋ መፈፀሙንና ይህም ድርጊቱ የWHO ሃላፊ ቴድሮስ አድሃኖም ይሁንታ ሳያገኝ እንዳልቀረ ነው የተጠቆመው፡፡

ህወሃት ዘረፋ የፈጸመው በተለየያዩ ግንባሮች ባደረጋቸው ውጊያዎች የቆሰሉ የአሸባሪው ቡድን አባላት ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ እና የቡድኑ አባላት ህክምና ማግኘት ባለመቻላቸው ከተዋጊዎቹ ቅሬታ እንዳይነሳ መልስ ለመስጠት እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ህወሓት ለቁስለኞች ብቻ ሳይሆን ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች በዓለም ጤና ድርጅት የመጠባበቂያነት የተቀመጠውን የደም ግፊት፣የስኳርና ሌሎች መድሃኒቶች መውሰዱ የተገለፀ ሲሆን በመቀሌ በአሁኑ ወቅት በተለይም አዛውንቶችና ሽማግሌዎች የስኳርና የደም ግፊት መድሃኒት በማጣታቸው ለከፍተኛ አደጋ መጋለጣቸውን እየወጡ ያሉ ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡

የትግራይን ህዝብ አፍኖ ለፖለቲካ ጥቅሙ ማዋልን የለመደው ህወሓት ከአሁን ቀደም የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለዕርዳታ ማሰራጫ ያሰቀመጠውን 570 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ በመዝረፉ የዓለም ምግብ ፕሮግራም በትግራይ የሰብአዊ እርዳታ ማከፋፈል እንዳልቻለ መናገሩ የሚታወስ ነው፡፡

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በርግጥ ተቆርቋሪነቱ ለትግራይ ህዝብ ከሆነ ሕወሓት በትግራይ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ እንዲያስቆምና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ንብረት የሆኑ መጋዘኖችን እየዘረፈ ለጦርነት ማዋሉንም በግልጽ ሊያወግዝ ይገባል።

25/07/2022

bezuayehu wendimu

06/01/2022

የገና ሥጦታ ሎተሪ ወጥቷል!

የገና ሥጦታ ሎተሪ ሀሙስ ታህሳስ 28/ 2014 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡

በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል።

1ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1977732
2ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0341880
3ኛ. 2,500,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0929042
4ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1357756
5ኛ. 1,000,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 1288620
6ኛ. 500,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0614488

7ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው 20,000 ብር የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 18052
8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 05609
9ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4599
10ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 6941
11ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 883

12ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 250 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 904
13ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 22
14ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 50 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡

[ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ]

የአማራ ባለሃብቶች ጥምረት ለአገሩ ህልውና ከልጁ ጋር በክብር ለተሰዋው አቶ እሸቴ ሞገስ ቤተሰቦች 2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ።የተደረገውን ድጋፍ የባለሃብቶቹ ጥምረት ተወካይ አቶ ዮናስ መኮ...
12/12/2021

የአማራ ባለሃብቶች ጥምረት ለአገሩ ህልውና ከልጁ ጋር በክብር ለተሰዋው አቶ እሸቴ ሞገስ ቤተሰቦች 2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ።

የተደረገውን ድጋፍ የባለሃብቶቹ ጥምረት ተወካይ አቶ ዮናስ መኮንን ለአቶ እሸቴ ሞገስ ታናሽ ወንድም ዶክተር ይተብቱ ሞገስ ተረክበዋል፡፡

አቶ እሸቴ ሞገስ ከልጃቸው ይታገስ እሸቴ ጋር በመሆን በሸዋሮቢት ሳላይሽ ላይ ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ ብሎ የተነሳውን የአሸባሪው ህወሃት ዘጠኝ ወራሪ ኃይሎችን በጀግንነት በመግደል በክብር መሰዋታቸው ይታወሳል፡፡

_ አካባቢህን ጠብቅ፣
_ ወደ ግንባር ዝመት፣
_ መከላከያን ደግፍ።

በአሜሪካ ሁሉም ግዛቶች የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነውበሰልፉ ላይ በሁሉም የአሜሪካ ግዛቶች የሚኖሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያንና ትው...
11/12/2021

በአሜሪካ ሁሉም ግዛቶች የሚኖሩ ዳያስፖራዎች የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነው

በሰልፉ ላይ በሁሉም የአሜሪካ ግዛቶች የሚኖሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች እየተሳተፉ ነው።

ሰልፈኞቹ የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርገውን ያልተገባ ጫና የሚቃወሙ መልዕክቶችን እያስተላልፉ ነው።

ሰልፈኞቹ አሸባሪው ሕወሓት እየፈጸማቸው ያሉ አሰቃቂ ድርጊቶች እና የምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ዙሪያ የሚያሰራጯቸውን ሐሰተኛ መረጃዎችን በማውገዝ ላይ ይገኛሉ።

ከአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት አንስቶ እስከ ‘ካፒቶል ሂል’ በሚደረገው የአንድ ሰዓት የእግር ጉዞ ለአሜሪካ ዜጎች በኢትዮጵያ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ የተመለከቱ መረጃዎችን የያዙ በራሪ ወረቀቶች እንደሚበተኑም ተገልጿል።

ሰልፉ በአሜሪካ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ አባላት በሰልፉ ላይ በሕልውና ማስከበር ዘመቻው ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት ጎን መቆማቸውን የሚገልጹበት እንድሆነም ተመልክቷል።

በዋሺንግተን ዲሲ የሚካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ “የበቃ” ወይም ‘ ’ ዘመቻ አካል ሲሆን ሰልፉን የሰላምና አንድነት ለኢትዮጵያ ማኅበር ዋሺንግተን ግብርኃይል ከተለያዩ ተቋሞችና አገር ወዳጆች በጋራ እንዳዘጋጁት ተገልጿል።

17/11/2021

በአዲስ አበባ መሬት ተቆፍሮ የተቀበሩ ሽጉጦች፣ ወርቆች እና ገንዘብ በህብረተሰቡ ጥቆማ ተያዙ

መሬት ውስጥ ተቆፍረው የተቀበሩ ሽጉጦች፣ ወርቆች እና ገንዘብ በህብረተሰቡ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ብርበራ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የህወሓት እና ሸኔ የሽብር ቡድኖች ከውስጥ እና ከውጪ ድጋፍ በሚሰጧቸው ፀረ ሠላም ኃይሎች እና ተላላኪዎቻቸው አማካይነት ከተማዋን ለማተራመስ የሚያደርጉትን ስውር እንቅስቃሴ ለመግታት እና ድብቅ ሴራቸውን ለማክሸፍ ከሌሎች የፀጥታ አካላት እና ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጿል፡፡

ፖሊስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረት በማድረግ የህወሓት የሽብር ቡድንን በመደገፍ በተጠረጠሩ ግለሰቦች መኖሪያ ቤት እያደረገው ያለው ብርበራ እና ፍተሻ ሲጠናከር የተለያዩ ፈንጂዎች እኛ ሌሎች የጦር መሳሪያዎች በተለያዩ ቦታዎች ተጥለው እና መሬት ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸው ተጠቅሷል፡፡

17/11/2021

ዩጋንዳ ላይ ጥቃት ደረሰ
ዛሬ በኡጋንዳ በደረሱ 2 የሽብር አደጋዎች 3 ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆሰሉ፡፡

ካምፓላ ሁለት ቦታዎች በደረሱ የአጥፍቶ ጠፊዎች የሽብር ጥቃት ይ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ፖሊስ አስታቋል፡፡

በአደጋው ከቆሰሉት 33 ሰዎች ውስጥ አምስቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል፡፡ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል፡፡

በካምፓላ ሁለት የገበያ ማዕከላት ላይ ደረሰ የተባለው ይህ የዛሬ ረፋድ የሽብር ጥቃት በአገሪቱ ፓርላማ መግቢያ አካባቢ ነው የተፈጸመው፡፡

የአገሪቱ ፖሊስ በበኩሉ አደጋው በሁለት የአገር ውስጥ የሽብር ቡድን አባላት አማካኝነት በተመሳሳይ ሰዓት በተለያዩ ቦታዎች ፍንዳታው መድረሱን ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት አስታውቋል፡፡

ይሁንና እስካሁን በሽብር ድርጊቱ ዙሪያ ሃላፊነት የወሰደ አካል እንደሌለ የተገለጸ ሲሆን የአገሪቱ ፖሊስ ድርጊቱን እየመረመርኩ ነው ብሏል፡፡

ከ1 ወር በፊት በካምፓላ ከተማ ባለ አንድ ሬስቶራንት ውስጥ በደረሰ ተመሳሳይ የሽብር አደጋ ሁለት ሰዎች የሞቱ ሲሆን ሀላፊነቱን አይኤስ አይ ኤስ ለድርጊቱ ሃላፊነት ወስዶ ነበር፡፡

በዚሁ ዓመት መስከረም ወር መጨረሻ ቀናት ላይ አንድ አጥፍቶ ጠፊ የሽብር ቡድን በፈጸመው ጥቃት እራሱን ገድሎ በርካቶችን ማቁሰሉ አይነጋም

Credit : Al AIN

16/11/2021

በዩጋንዳ ካምፓላ ሊካሄድ የነበረው ጉባኤ ተላለፈ።

የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በየነ መንግስታት (IGAD) አባል ሀገራት መሪዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረገዉ ጦርነት በሰላም ስለሚያበቃበት መንገድ ለመነጋገር ለዛሬ ይዘዉት የነበረዉ ቀጠሮ ተሰረዘ።

በሰሜን ኢትዮጵያ ስላለው ጦርነት የኢጋድ አባል ሐገራት መሪዎች ዛሬ ካምፓላ-ዩጋንዳ ዉስጥ ተገናኝተዉ እንዲነጋገሩ የጠሩት የዩጋንዳዉ ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴ ቬኒ ነበሩ።

ነገር ግን የዛሬው ጉባኤ ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ሮይተርስን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ አስነብቧል። ጉባኤዉ የተላለፈበትን ምክንያትም ሆነ የሚደረግበት ቀን አልተጠቀሰም።

16/11/2021

በዓለም የሃያላኑ የኢኮኖሚ ፉክክር ቻይና ቀዳሚ ሆነች

በዓለም የሃያላኑ የኢኮኖሚ ፉክክር ቻይና አሜሪካን በመበለጥ ቀዳሚ ሃገር መሆኗ ተገለፀ።

እንደ ዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ ተንታኝና አማካሪ ተቋም ማክ ኪንሴይ ሪፖርት፥ ቻይና በዓለም ከፍተኛ ሃብት በማካበት አሜሪካን በመብለጥ ቀዳሚ ሃገር ሆናለች።

እንደ ብሉምበርግ የቢዝነስ ሪፖር ገለፃ የቻይና ሀብት ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን በፈረንጆቹ 2000 ሰባት ትሪሊየን ዶላር የነበረው አጠቃላይ ሃብቷ በ17 እጥፍ አድጎ በ2020 ወደ 120 ትሪሊየን ዶላር ማደጉ ተገልጿል፡፡

አሜሪካ ሀብቷን በተመሳሳይ ጊዜ በእጥፍ ያሳደገች ቢሆንም በፈረንጆቹ 2020 ያላት ሀብት 90 ትሪሊየን ዶላር ብቻ መሆኑ ነው የተገለፀው፡፡

ቻይና ዓለም አቀፉን የንግድ ድርጅት መቀላቀሏ ለኢኮኖሚዋ ማደግና መጨመር እገዛ ማድረጉ ይነገራል።

አሁን ዓለም ላይ ካለው ሃብት ውስጥ 68% የሚሆነው በሪል እስቴት ዘርፍ ውስጥ የተከማቸ መሆኑን አር ቲ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

©FBC

16/11/2021

"ማነህ፥ ከየት ነህ? " ካሉህ....

ታምሩ ዓለሙ እንደፃፈው

ስማኝማ "ማነህ፥ ከየት ነህ? ካሉህ...እንዲህ በላቸው

ከአፍሪካ ብቸኛዋ ቅኝ ካልተገዛች፥ ሀያላኑን ድል ከነሳች የነፃነት ቀንዲል ምድር የተገኘሁ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ነኝ በላቸው፤ የሚኒልክን ጀግንነት የጣይቱን ብልጠት አስታውሳቸው

እናንተ የነፃነት ቀን ስትዘክሩ እኛ ግን የድል ቀን እናከብራለን በልና ስለ አድዋ ገድል ኮራ ብለህ አስተምራቸው

በሁለቱም ፆታዎች በኦሊምፒክ ወርቅ ያጠለቁ የመጀመሪያ አፍሪካዊያን አትሌቶች ከበቀሉባት የጀግኖች አምባ የተገኘሁ የኢትዮጵያ ልጅ ነኝ በላቸው፤ የአበበ ቢቂላን የባዶ እግር አሻራ ፥ የደራርቱ ቱሉን የሳቅና የእምባ ድል ታሪክ ጥቀስላቸው

ከአፍሪካ ሀገራት ሁሉ ብቸኛዋ የራሷ ፊደል ካላት ባለ ሆሄ ምድር ሀ...ሁ...ብዬ አፌን የፈታሁ ሀበሻ እኮ ነኝ በልና ንገራቸው

ከብዙዎቹ ቀድማ ክርስትናንና እስልምናን ከተቀበለች፥ እኔም ከአባቶቼ እምነቴን የተረከብኩ አቢሲንያዊ ነኝ በላቸው፤ በመፅሀፍ ቅዱስና በቅዱስ ቁርአን ስሟ ተደጋግሞ የተጠቀሰ ሀገር እንዳለችህ ጠቁማቸው

አዎ "ማነህ፥ ከየት ነህ?" ካሉህ እንዲህ በላቸው...

የላሊበላ፣ የፋሲልና የአክሱም የጥበብ አሻራዎችን፥ የተፈጥሮ ስጦታዎችን እያነሳህ የግዮን ውሀን የተጎነጨሁ እድለኛ ፍጡር ነኝ ብለህ ማንነትህን አሳያቸው

ስለ ዋርካው ምስለኔ ፍትህ፥ ስለ የኔታ ፊደል፥ ስለ ገዳ ስርዓት፣ ስለ ዙምራ ስልጣኔ እየዘከርክ የባህልና የትውፊት ሀብታም ከሆነች ሀገር ስምህ መታተሙን አረጋግጥላቸው

አረንጓዴ ቢጫና ቀይ ቀለሟን አፍሪካዊያን የተጋሯት፥ የሰንደቅ ቀለሟን ብዙዎች የተቀባበሏት የነፃነት አውራ የቀስተደመና ምልክት መጠሪያ እንዳለችህ ንገራቸው።

16/11/2021

በአርሲ ነጌሌ ከተማ 52 የአሸባሪው ህወሓት ቡድን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምዕራብ አርሲ ዞን፣ አርሲ ነጌሌ ከተማ 52 የአሸባሪው ሕወሃት ቡድን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የአርሲ ነጌሌ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጣቢያ ምክትል ኃላፊ ሳጂን ኦላና ገመቹ እንደገለጹት፣ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ሊውሉ የቻሉት በጸጥታ ኃይሎች በተደረገ ፍተሻ ነው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የቀድሞ የመከላከያ ሰራዊት አልባሳት፣ ኤስ ኬ ኤስ የጦር መሳሪያ፣ የተለያዩ ፓስፖርቶች፣ የባንክ ደብተሮች፣ የባንክ ቼክ፣ የተለያዩ ሞባይሎችና ላፕቶፖች፣ የተለያዩ መታወቂያ ወረቀቶች መንጃ ፍቃዶችና ከተለያዩ የጽሑፍ መረጃዎች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ከአርሲ ነጌሌ ከተማ ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
©EBC

16/11/2021

ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ችግር በውጪ አገራት ጣልቃ ገብነት ሊፈታ እንደማይችል እና መፍትሄው ከውስጥ መምጣት እንዳለበት የአሜሪካ የቀድሞ አምባሳደሮች አምባሳደር ቲቦር ናዥ እና አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ ተናግረዋል

አምባሳደሮቹ የዘር መከፋፈል ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ችግር እንደዳረጋት ገልፀው፤ “ኢትዮጵያውያኖች ልዩነታቸውን አቻችለው በአንድነትና በሰላም መኖር የሚችሉበትን መንገድ መፈለግ አለባቸው” ብለዋል።

በኢትዮጵያና በጊኒ የአሜሪካ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉትና በትራምፕ አስተዳደር ረዳት የውጭ ጉዳይ የነበሩት ቲቦር ናዥ እንዲሁም በኢትዮጵያ፣ ላይቤሪያ እና ዛምቢያ አምባሳደር የነበሩት ዶናልድ ቡዝ ኢትዮጵያውያን ለውጪ ሀይል ግፊት የማይንበረከኩ መሆናቸውን ማስተዋላቸውን ጠቁመዋል።

አያይዘውም የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሚና ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው እንዲፈቱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

ሁለቱም ዲፕሎማቶች ከአሜሪካ ድምፅ ዘጋቢ ካሮል ካስቲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ ሲተገበር የኖረው ዘርን መሰረት ያደረገ የፌደራሊዝም ስርዓት ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ችግር መሰረት እንደሆነም ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የሚታየው ችግር የተባባሰው የፖለቲካ አመራሮች ከህዝቡ ድጋፍ ለማግኘት ዘርን መጠቀማቸው ነው ያሉት አምባሳደር ቡዝ፥ በኢትዮጵያ የተሞከረው ዘርን መሰረት ያደረገ የፌደራሊዝም ስርዓት የታሰበውን ውጤት አለማምጣት ለዚህ ልዩነት መስፋፋት አስተዋፅኦ እንዳደረገ አስምረውበታል።
©FBC

16/11/2021

በኦሮሚያ ክልል መንግስት የሰዓት እላፊ ጨምሮ ሌሎች ውሳኔዎች ተላልፏል።

የክልሉ መንግስት ውሳኔውን ያሳለፈው በአገሪቱ ካለው ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሕገወጥ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር በማለም ነው።

በዚህም መሰረት ፦

• በክልሉ የሰዎችና የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ገደብ ተጥሏል። ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ለሊት 11፡30 ድረስ እንቅስቃሴ ማድረግ ተከልክሏል።

• ሰዎች መንቀሳቀስ የሚችሉት ከለሊት 11፡30 እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ሲሆን ተሸከርካሪዎች ግን መንቀሳቀስ የሚችሉት እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ብቻ ነው።

• በመንገድ ላይ ፍተሻዎች ይኖራሉ። ድንገተኛ ፍተሻ ይካሄዳል፤ በኬላዎችም ላይ ፍተሻ ይደረጋል። በመንግሥት መስሪያ ቤቶችና ሕዝብ በሚሰበሰብባቸው ቦታዎችም ፍተሻዎች ይካሄዳሉ። አብዛኛዎቹ ፍተሻዎች ምሽት ላይ የሚካሄዱ መሆናቸው ተጠቁሟል።

• በክልሉ የሚገኙ አከራዮች የተከራዮቻቸውን መታወቂያ በመያዝ በቀበሌና በአቅራቢያቸው በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች እየሄዱ ማስመዝገብ አለባቸው።

• አከራዮች አዲስ ተከራይ፤ ያለመታወቂያ ቤት ማከራየት የሌለባቸው ሲሆን መታወቂያ የሌላቸው ተከራዮች ካሉ መታወቂያ እንዲያወጡ ጊዜያዊ አሰራር ተዘርግቷል።

ተጨማሪ ፦ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ መሳሪያ ያላቸው ነዋሪዎች በ10 ቀናት ውስጥ እንዲያስመዘግቡ ታዟል።

መረጃው የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ግዛቸው ገቢሳ ለቢቢ እንዲሁም የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አዱኛ አሕመድ ለፋና ብሮድካስቲንግ ከሰጡት ቃል የተወሰደ ነው።

የእነዚህ ሰዎች ጭካኔ ድንበር የለውም(በጣም እንጠንቀቅ ለመከላከያው ለፈኖየሚደርሰውን እየተጠነቀቅን ።)በአዲስ አበባ ከተማ  ንፋስልክ ላፍቶ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ  የምትኖር   ባለትዳርና ...
16/11/2021

የእነዚህ ሰዎች ጭካኔ ድንበር የለውም

(በጣም እንጠንቀቅ ለመከላከያው ለፈኖ
የሚደርሰውን እየተጠነቀቅን ።)

በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስልክ ላፍቶ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ የምትኖር ባለትዳርና የ4 ልጆች እናት ፣
የትግራይ ተወላጅ የሆነች በትላንትናው እለት ማለትም ኅዳር 5/03/214

ይች የትግሬ ተወላጅ የሆነች ሴት 1 ኩንታል የእንጀራ ድርቆሽ ።በርካታ የታሸገ በሶ እና ሽሮ በርበሬ በወያላ አሸክማ ወደ ታክሲ በምትሄድበት ወቅት ከአካባቢው ማህበረሰብ በደረሰ ጥቆማ ፖሊስ ሴትየዋና ከእነ ጫነችው ቁሳቁስ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኃላ፣

ፖሊስ ወዴት እየሄድሽ ነው ይላታል ። ተጠርጣሪዋም ወደ ደብረ ብርሃን ድርቆሽና በሶ ለወሎ ተፈናቃዮች ልለግስ ነው ብላ መለሰች ።
ፖሊስ ጥርጣሬ ውስጥ በመግባቱ እዚሁ ማደር አለብሽ ይላታል ። በበነገው የያዘችው ድርቆሽና በሶ በመርዝ የተበከለ መሆኑን በላቦራቶሪ ታውቋል ።

ሴትየዋም ጥብቅ ምርመራ እየተካሄደባት ነው ብሏል

ኮማንደር ገመቹ ካቻ በቀለ
የንፋስ ላፍ ክ ፖሊስ ሃላፊ
በ ታላቁ አምደ ጽዮን እንደ ፃፈው

ያሬድ አላዩ

16/11/2021



በአሁን ግዜ ቤት የሚገዙ፣ የሚሸጡ ሁሉ ስራቸው ህገወጥ ስለሆነ ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ አገልግሎት አሳስቧል።
.
የቋሚ ንብረት ሽያጭ የቆመ ቢሆንም በአዲስ አበባ ከተማ አገልግሎቱ ሳይጀመር ሽያጭ እና ማስተላልፈ በመንደር ውል እና በውክል እየተሰራ መሆኑ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።

የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን አማረ ፤ በውክልናም ሆነ በመንደር ውል የቤት ሽያጭ ማከናወን ህጉ እንደማይፈቅድ ገልፀዋል።
አገልግሎቱ የሚጀምርበትን ጊዜ እናሳውቃለን ብለዋል።

" ቤት ሽያጭ ውል ሰነድ የማረጋገጥ አገልግሎት ነው " ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ " ይህ ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጧል። ተቋሙ በተለይ ከአ/አ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ህገወጥ ይዞታዎችን የማረጋገጥ ስራ እየሰረ ስለሆነ ከዛ ጋር ተያይዞ ላልተገባ ሰዎች ያልተገባ ውል ውስጥ እንዳይገቡ ያን የማረጋገጥ ስራ እስኪጠናቀቅ በጊዜያዊነት አገልግሎቱን መስጥ ቆሟል " ሲሉ አስረድተዋል።

ይሄ ህገወጥ ይዞታዎችን የማጣራት ስራ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሙሉቀን ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ላልተወሰ ጊዜ የማይንቀሳቀስ ንብረት ወይም መኖሪያ ቤት ሽያጭ / በስጦታ የማስተላለፍ ውሉ አሁንም ለጊዜው እንደተቋረጠ ይቀጥላል ሲሉ አሳውቀዋል።

ተቋሙ የተቋረጠውን አገልግሎት በሚጀምርበት ሰዓት በግልፅ በተለያየ ሚዲያ መረጃውን የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል።

በተለይ የተጠራቀመ አገልግሎት ካለ ተገልጋዮች በሰልፍ ብዙ ሳንይገላቱ ለመስራት አሰራር ተዘርግቶ ይኬዳል ሲሉ ጠቁመዋል።

ህብረተሰቡ ላልተገባ የመንደር ውል ሆነ ባልተገባ መረጀ ላይ ተመስርቶ ከሚደረጉ ውሎች እንዲቆጠብ የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ አገልግሎት ለሸገር ራድዮ በሰጠው ቃል አሳስቧል።

(sheger Fm)

16/11/2021

❝የህልውና ትግላችን ጠላትን ማሸነፍ እና ከወረራቸው አካባቢዎች ማስወጣት ብቻ ሳይሆን ዳግም ለአማራ ስጋት በማይሆንበት ደረጃ እስከ መቅበር ድረስ ነው❞ የፋኖ ብርጌድ መሪ ሻለቃ ሰፈር መለሰ

የፋኖ ብርጌድ መሪ ሻለቃ ሰፈር መለሰ ፋኖ ከወትሮው በተለዬ በመንግሥት ድጋፍ በሻለቃና በብርጌድ ተደራጅቷል፤ በዚህ መንገድ መደራጀቱም የአማራን ሕዝባዊ ኃይል ያጠናክራል ነው ያሉት።

በሻለቃና በብርጌድ የተደራጀው የፋኖ ኃይል ከመከላከያ ሠራዊቱ፣ ከአማራ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ጋር በመቀናጀት ጠላትን እየተፋለመ እንደሚገኝም አዛዡ ገልጸዋል።

በግንባሩ የሚገኘው አጠቃላይ ሠራዊት እርስ በርሱ ተቀናጅቶና ተናቦ ጠላትን ለመቅበር እየታገለ ይገኛል ብለዋል።

ፋኖ በግንባር የጠላትን ምሽግ እየደረማመሰ በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ እንዲሁም የሞራል ኪሳራ እያደረሰ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ጠላት የተለያዩ ጠንካራ ምሽጎችን በመሥራት በተደጋጋሚ ጥቃት ለመሰንዘር ጥረት እያደረገ ቢገኝም የፋኖ ኃይል ፀረ ማጥቃት በማድረግ ሁለት የጠላት ምሽጎችን በመስበር ጀብዱ ፈፅሟል፤ በርካታ የጠላትን ኃይልን በመደምሰስ ትጥቆችን ማርኮ መታጠቁን አመላክተዋል።

በሁሉም ግንባር የአሸባሪው ኃይል መስፋፋት በቅርቡ ይገታል ያሉት ሻለቃ ሰፈር ሕዝባዊ ሠራዊቱ የጠላትን አሰላለፍና አቅም በውል ተረድቷል፤ ስለሆነም የጠላትን መስፋፋት በመግታት እና መልሶ በማጥቃት ጠላት ሰርጎ የገባባቸውን አካባቢዎች በሙሉ ነፃ እናወጣለን ነው ያሉት።

❝የህልውና ትግላችን ጠላትን ማሸነፍ እና ከወረራቸው አካባቢዎች ማስወጣት ብቻ ሳይሆን አሸባሪው ኃይል ዳግም ለአማራ ስጋት በማይሆንበት ደረጃ እስከ መቅበር ድረስ ነው❞ ብለዋል።

©አሚኮ

16/11/2021

የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል በሰሜኑ ግጭት ጣልቃ እንዲገባም ሆነ ሃይል ሊያሰፍር አይገባም

“ለአሜሪካ መንግስት ግልፅ መልእክት ማስተላለፍ የምንፈልገው የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል በሰሜኑ ግጭት ጣልቃ እንዲገባም ሆነ ሃይል ሊያሰፍር አይገባም “ ሲል የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት አስገነዘበ።

ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ ለአሜሪካን ኮንግረስ፣ ለአሜሪካ ውጪጉዳይ እና ለአሜሪካን መከላከያ አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ወታደራዊ እርምጃ ልትወስድ እንደማይገባ አስገንዝቧል።

በአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሁለት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የመከላከያ መሪዎች በኢትዮጵያ ባለው የሰሜኑ ግጭት አሜሪካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነትን ልታካሂድ ትችላለች ማለታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ሊቀ መንበርና ተባባሪ መስራች ዲያቆን ዮሴፍ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

“ለአሜሪካ መንግስት ግልፅ መልእክት ማስተላለፍ የምንፈልገው የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል በሰሜኑ ግጭት ጣልቃ እንዲገባም ሆነ ሃይል ሊያሰፍር አይገባም “ ብለዋል በመግለጫቸው።

በትግራይ ያለው ግጭት የውስጥ ጉዳይ ሆኖ በኢትዮጵያውያን እና በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጠው መንግስታቸው ብቻ ሊያዝ እንደሚገባም አመላክተዋል።

“ኢትዮጵያ አሜሪካውያንን ወክለን እንደምንናገረው የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ከማባባስ እንዲቆጠብ እንጠይቃለን” ያለው መግለጫው የአሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ መግባት ሃላፊነት የጎደለውና የተሳሳተ ውሳኔ ነው፡፡

ይህም አሜሪካ ለ20 አመታት በአፍጋኒስታን በነበራት ቆይታ በመጨረሻዎቹ አመታት ተፈጥሮ የነበረውን ቀውስ ማንም የሚያስታውሰው ነው አብዛኞቹ አሜሪካውያንም ይህን ድርጊት ተቃውመውታል፡፡

©ኢዜአ

16/11/2021

1) ጊዜያዊ መታወቂያ የጠፋበት፣ የተበላሸበት ወይም በሌላ ምክንያት ጉዳት የደረሰበት ወይም በማናቸውም ምክንያት ከእጁ የወጣበት ማንኛውም ሰው ለፖሊስ በ24 ሰዓት ውስጥ ሪፖርት የማድረግ ሀላፊነት አለበት፣
2) በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 1 የተመለከተው ሁኔታ ሪፖርት ፖሊስ ተቋም በሚሰጠው ማረጋገጫ መሰረት ጊዜያዊ መታወቂያ የመስጠት ስልጣን የተሰጠው አካል፣ ምትክ ጊዜያዊ መታወቂያ ይሰጣል::

13. የተከለከሉ ተግባራት

የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም በአዋጁ እና ሌሎች ህጎች መሰረት የወንጀል ኃላፊነት ያስከትላል፡-
1) ጊዜያዊ መታወቂያ ለመውሰድ ሀሰተኛ መረጃ መስጠት ፣
2) መስፈርቱን ለማያሟላ ሰው ጊዜያዊ መታወቂያ መስጠት፤
3) መስፈርቱን የማያሟላ ሰው ጊዘያዊ መታወቂያ እንዲሰጠው በማሰብ ማረጋገጫ ደብዳቤ መፃፍ ወይም ምስክር መሆን፣
4) ከአንድ በላይ ጊዜያዊ መታወቂያ ይዞ መገኘት፡፡

ክፍል አራት

ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች

14. ተፈፃሚነት የሌላቸው መመሪያዎች ወይም ልማዳዊ አሰራሮች

ከዚህ መመሪያ ጋር የሚቃረን ማንኛዉም መመሪያ ወይም የአሰራር ልምድ በዚህ መመሪያ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ይህ መመረያ ጸንቶ በሚቆይበት ጊዜ ተፈፃሚነት አይኖረዉም፡፡

15. መመሪያዉ የሚፀናበት ግዜ

ይህ መመሪያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡

አዲስ አበባ ጥቅምት 6 ቀን 2014 ዓ.ም

(የአስቸካይ ጊዜ አዋጅ መመሪያ እዝ)

16/11/2021

የሳምሪ አባል የሆኑና በማይካድራው የግፍ ወንጀል ላይ የተሳተፉ ሶስት ግለሰቦች በአዲስ አበባ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ግለሰቦቹ በሱዳን አድርገው ወደየመን ከሄዱ በኃላ ከየመን በስደተኛ ስም መግባታቸው ተገልጿል።

ሶስቱ ተጠርጣሪዎች ተልእኮአቸውን በሚስጢር ለማከናወን ሲንቀሳቀስ በህዝብ ጥቆማ ትብብር መያዛቸውን የኢሳት የመረጃ ምንጮች ተናግረዋል።

ግለሰቦቹ በዛሬው ዕለት በስሚት የኮንዶሚኒየም ግንባታ ሳይት በጥበቃ ድርጅት ውስጥ ተደብቀው መያዛቸውም ታውቋል።

እነዚህ ተጠርጣሪዎች የሳውዲ ፖስፖርት ያላቸው እንዲሁም የአዲስ እበባ የነዋሪነት መታወቂያ የሀሰት በማሰራት ሲንቀሳቀሱ ነበር ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ የአሽባሪውን ህወሀት ተልዕኮ ሊፈፅሙ ሲንቀሳቀሱ በህብረተሰቡና በዙሪያው ባሉ ሰራተኞች የነቃ ተሳትፎ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

አካባቢያችን ነቅተን እንጠብቅ !!

16/11/2021

የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል የሕግ ታራሚዎችን በአሽከርካሪነት ሙያ ማሰልጠን ሊጀምር ነው

የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል የሕግ ታራሚዎችን በሕዝብ አንድ አሽከርካሪነት ሙያ ለማስልጠን የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ የአሽከርካሪነት ሙያ ሰልጣኝ ታራሚዎች ስለመኪና አነዳድ በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸው የተከናወነውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ የሚበረታታ እንደሆነ ተመልክቷል፡፡

ስልጠናውን ለማስጀመር በኮሚሽኑ በኩል መሟላት የሚገባቸው ነገሮች በሙሉ እንዲሟሉ እየተደረገ ሲሆን ፣ ማዕከሉ ማረሚያ ቤቱ ያለበትን የልምምድ ተሸከርካሪ እጥረት በአጭር ቀናት ውስጥ እንደሚቀረፍ የዝዋይ ማረሚያ ቤት ማዕከል ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ፍቅሬ አብዩ በተለይ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የማቋቋሚያ አዋጅ መሠረት ለሕግ ታራሚዎችና ተሸከርካሪ መንዳት የሚያስችላቸውን ስልጠና በማረሚያ ቤት እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡

ስልጠናው በአንድ ማዕከል ማረሚያ ቤት ብቻ ሳይወሰን በሌሎች ማረሚያ ቤቶች ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት ኢንስፔክተር ፍቅሬ ፣ በዝዋይ ማረሚያ ቤት ማዕከል ስልጠናውን ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡

ከኦሮሚያ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተሰርቷል፡፡ ዝግጅቱን ወደ ተግባር ለማሸጋገር የሚያስችል የተግባር ማስተማርያ ወርክ ሾፕ የተዘጋጀ ሲሆን ፣ የንድፈ ሃሳብ ትምህርትና የመስክ ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል ሥራም ተከናውኗል፡፡

የዝዋይ ማረሚያ ቤት ከባቱ ከተማ ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ማዕከላዊ ጋራዥ አሰልጠኞችን በትብብር በማስመጣት የአሽከርካሪነት ሙያ ለመጀመር በሚያስችል ደረጃ ወርክ ሾፕ በአግባቡ በማደራጀት በሕዝብ አንድ ስልጠና ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን የዝዋይ ማረሚያ ቤት ማዕከል ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ፍቅሬ አብዩ ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል፡፡

09/11/2021

የአፍሪካ ህብረት የጸጥታው ምክር ቤት በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በህብረቱ ልዩ መልዕክተኛ ኦባሳንጆ ገለጻ እንደተደረገለት አል ዐይን በድረገፁ አስነብቧል።

ህብረቱ ዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ/ም አስቸኳይ ዝግ ስብሰባ አካሂዷል፡፡ ስብሰባው በበይነ መረብ የተካሄደ እንደነበር ተገልጿል።

በስብሰባው ላይ ፦

• የህብረቱ የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዲዎዬ፣

• የህብረቱ የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴገን ኦባሳንጆ፣

• በአፍሪካ ህብረት የግብጽ ቋሚ ተወካይ መሃመድ ጋድ እና በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ ተሳትፈዋል፡፡

ስብሰባው የተካሄደው በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ለመምክርና የአፍሪካ ህብረት የምስራቅ አፍሪካ ተወካይ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴገን ኦባሳንጆን ገለጻ ለማድመጥ ነበር፡፡

በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ በተሳተፉበት በዚህ ስብሰባ ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ከመከረና የኦባሳንጆን ገለጻ ካደመጠ በኋላ ያለው ወይም ያስቀመጠው ቀጣይ አቅጣጫ እንዳለ የታወቀ ነገር የለም፡፡

ነገር ግን ም/ ቤቱ የተሰበሰበበትን ጉዳይ የተመለከተ መግለጫን እንደሚያወጣ መረጃ እንዳለው አል ዓይን ዘግቧል።

09/11/2021

"ህይወታችንን ገብረን ኢትዮጵያን እናቆያታለን!" - ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዘጋጅነት መከላከያን ለመደገፍ እና አሸባሪው ቡድን በከፈተው ጦርነት የተፈናቀሉ ዜጎችን ለማቋቋም በተካሄደው ገቢ ማሰባሰባ መርሐግብር ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የዛሬ መቶ አመት አካባቢ ኢትዮጵያዊያን ወራሪ ሲመጣባቸው እንዴትሆነው ነጻ እንዳወጡ ሳስብ ይገርመኛል ፤ከቅርብና ከሩቅ ሲያጠቋም አንገዛም ብለው ኢትዮጵያንዉያን በህብረት ቆመዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያን ትላንትም ነጻ ነበርን፣ ዛሬም ነጻ ነን፣ ነገም ነጻ እንሆናለን ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ ኢትዮጵያ የተፈተነችው በአቅሟ ልክ ነው ፤ሌላው ቢሆን በዚህ ልክ አይፈተንም ብለዋል።

ጠላቶቿ በኢትዮጵያ በተባበረ ክንድ ይሸነፋሉ ፤
ኢትዮጵያ ለምልሟ ባንድራዋ ከፍ ብሎ የምናይበት ጊዜ ይመጣል በመሆን ህይወታችንን ገብረን ኢትዮጵያን እናቆያታለን ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ።

እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊም ሀገሩን የሚወድ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፤እውቀት ያለው በእውቀቱ ፤ጉልበት ያለው በጉልበቱ በተባበረ ክንድ በጋራ እንድንቆም ጠያቂ ብቻ ሳይሆን መላሽም እንድትሆኑ አደራ እላለሁ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወዴት አለ ብለው ለሚጠይቁ ሁሉ ጀልባዋ ላይ ነው ያለው በሏቸው ፤ህዝቡን ወታደሩን አስተባብሮ ነጻ የተረከባትን ሀገር ነጻ ያስረክባል ሲሉ ተናግረዋል ።

ኢትዮጵያ አትፈርስም አትበተንም ጠላቶቿን አሸንፋ የአፍሪካ ፈርጥና ምሳሌ ትሆናለች ብለዋል ።

09/11/2021

«የጦር መሳርያ የመቀማት ዓላማ የለንም » ፖሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ የጦር መሳርያ የማስመዝገቡ ሂደት የከተማዋን ደህንነት ለማስጠበቅ እንጂ የጦር መሳርያ የመቀማት ዓላማ እንደሌለው የከተማዋ ፖሊስ ገለጸ። በትግራይ ተወላጆች ላይ በጅምላ እስራት እየተፈጸመ ነው የሚለውን ክስ እንደማይቀበሉ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ ተናግረዋል። «ከፖሊስ ጋር ተባብረው የሚሰሩ እና ለፖሊስ መረጃ የሚሰጡ የትግራይ ተወላጆች አሉ» ያሉት ኮማንደር ፋሲካ የከተማዋን ደህንነት የማስጠበቁ ስራ በደሴ እና የኮምቦልቻ ከተሞች የተፈጠረውን አይነት ተመሳሳይ ችግር አዲስ አበባ ውስጥ እንዲከሰት ስለማንፈልግ ቁጥጥራችንን ጠበቅ አድርገናል ብለዋል ።
(የጀርመን ድምጽ)

09/11/2021

'' ፈተናውም በማንም፤ በምንም፤ በየትም አልተሰረቀም '' - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ መሰጠት የተጀመረው የ2013 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ቀንን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ በመግለጫቸው ከሞላ ጎደል ፈተናው በሰላማዊ መንገድ መከናወኑን ገልጸዋል። ''ፈተናውም በማንም በምንም በየትም አልተሰረቀም'' ሲሉ ገልጸዋል።

በዛሬው ዕለት 2 ተማሪዎች በኦሮሚያ ክልል 2 ተማሪዎች በደቡብ ክልል በስልካቸው ፎቶ አንስተው ''ኤሌክትሮኒክ ኩረጃ'' ሊፈጽሙ ሲሉ መያዛቸውን ጠቅሰዋል።

ተማሪዎቹ ፈተና ክፍል ከገቡ በኋላ ፈተናውን በፎቶ አንስተው ሲላላኩ መያዛቸው ነው የተጠቀሰው። ይህም ተማሪዎች ለፈተና ከገቡ በኋላ የተለቀቀ በመሆኑ ፈተናው ተሰርቋል ሊባል አይችልም ተብሏል።

ፈተናው በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄድ ከፌደራል ጀምሮ እስከታች ባሉ የኮማንድ ፖስቱ አባላት ያደረጉት አስተዋጽኦ የተሻለ መሆኑን ጠቅሰዋል። በሚቀጥሉት ሦስት ቀናትም ትብብሩ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

ዛሬ በተሰጠው መግለጫ ተማሪዎች የሞባይል፣ የስማርት ሰዓትም ሆነ ሌሎች ዲጂታል ኤሌክትሪክ መሳሪያዎችን ይዞ መገኘት እንደማይፈቀድ አጽንኦት ተሰጥቶ ተገልጿል።

ሕዝብ ተናገረ!ሰሞኑን በተለያዩ ክልሎች ከ30 ሚልዮን በላይ ሕዝብ ዐደባባይ ወጥቶ ስለሀገሩ ተናግሯል። ኢትዮጵያን ለማዳን እስከ ሕይወት መሥዋዕትነት እንደሚከፍል፣ ለጸጥታ ኃይሉ አስፈላጊውን ...
07/11/2021

ሕዝብ ተናገረ!

ሰሞኑን በተለያዩ ክልሎች ከ30 ሚልዮን በላይ ሕዝብ ዐደባባይ ወጥቶ ስለሀገሩ ተናግሯል። ኢትዮጵያን ለማዳን እስከ ሕይወት መሥዋዕትነት እንደሚከፍል፣ ለጸጥታ ኃይሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ፣ ማንኛውንም የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማይቀበል፣ የሕወሐትንና አጋር ጽንፈኛ ኃይሎችን ሀገር የማፍረስ የሽብር ተግባራት አጥብቆ እንደሚያወግዝ በግልጽ ተናግሯል።

እንዲሁም አንዳንድ የውጭ ሚዲያዎች፣ ዲፕሎማቶችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ስለ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፉትን የተዛባ መረጃ ሕዝቡ ኮንኗል። የሚያስተዳድረውን መንግሥት ነጻ፣ ገለልተኛና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መምረጡንና ይህንን ውሳኔውንም ዓለም እንዲያከብርለት ሕዝቡ አጥብቆ ጠይቋል።

ሕዝቡ ሀገሩን ለማዳን ማንኛውንም መሥዋዕትነት እንደሚከፍል በተግባር አሳይቷል።

ሕዝቡ በወራሪው በተያዙ አካባቢዎችም በከፍተኛ ግለት እየተነሣ ነው። በተወረሩ አካባቢዎች የሚገኘው ሕዝብ ጽንፈኛውን ሕወሐት ምቾት ተሰምቶት እንዳይቀመጥ እያደረገው ይገኛል። ይህ የሕዝብ ንቅናቄ አሸባሪውን በሁሉም ቦታዎች እግር በእግር እየተከታተለ ርምጃ በመውሰድ አከባቢዎችን ተገድዶ እንዲለቅ እያደረገው ይገኛል።

አሁን የተጀመረውን ለኢትዮጽያ ህልውና ሕዝብን የማዝመት ንቅናቄ በብዛትና በስፋት በማከናወን፣ አሸባሪውን ሕወሐትን ድል ማድረግ እንዳለበት ሕዝቡ በአንድ ቋንቋ ተናግሯል። ግንባር ቀደም ሆኖ እንደሚዘምትም አረጋግጧል። ወሳኙ ጉዳይ የውስጥ ዐቅማችንን መጠቀም መሆኑን ሕዝቡ በዐደባባይ አሳይቷል።

ሕዝብ ተናግሯልና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሊያዳምጥ ይገባል።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

@ኢዜአ

07/11/2021



አሜሪካን ጨምሮ 16 የዓለማችን ሀገራት በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የተካሄደውን ጥምር ምርመራ ሪፖርት እንደሚቀበሉት በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።

የጣምራ ሪፖርቱን እንደሚቀበሉ ያሳወቁት፦
• አሜሪካ
• አውስትራሊያ
• ቤልጂየም
• ካናዳ
• ዴንማርክ
• ፊንላንድ
• ፈረንሳይ
• ጀርመን
• አይስላንድ
• አየርላንድ
• ሉግዘንበርግ
• ኔዘርላንድ
• ኒውዝላንድ
• ኖርዌይ
• ስዊድን እና እንግሊዝ ናቸው።

ሀገራቱ በመግለጫቸው ሁለቱ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ተቋማት በትግራይ ክልል ባለው ጦርነት ዙሪያ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ያወጡት ሪፖርት ገለልተኛ እና ተጠያቂነትን ሊያሰፍን የሚችል መሆኑን አስታውቀዋል።

በሪፖርቱ መሰረት በሰብዓዊ መብት ጥሰት ሁሉም አካላት መሳተፋቸው በመረጋገጡ ሁሉም ተሳታፊዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ሀገራቱ አሳስበዋል።

በተጨማሪ በሰብዓዊ መብት ጥሰቶቹ ላይ የተሳተፉ ሁሉም አካላት በሪፖርቱ ግኝቶች መሰረት ወደ መፍትሄ እንዲመጡም ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል 16ቱ አገራት የኢትዮጵያ መንግስት በጦርነቱ ለተጎዱ አካላት እያደረገ ያለው ድጋፍ፣ ወንጀል ፈፅመዋል በሚል በተጠረጠሩ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ምርመራ መጀመሩ ና እያደረጋቸው ላለው ሌሎች ጥረቶች እውቅና እንሰጣለን ብለዋል።

መንግስት የጀመረውን ጥረት እንዲቀጥልበት የጠየቁ ሲሆን በተለይ ለተጎጂዎች ተጨማሪ የሰብዓዊ መብት ድጋፎች እንዲደርሱ፣ በወንጀል ፈጻሚዎች ላይ ተጨማሪ ምርመራዎች እንዲካሄዱና ጦርነቱን በዘላቂነት ለማስቆም ብሄራዊ ውይይት እንዲያካሂድ ጠይቀዋል።

ሀገራቱ ኢትዮጵያ ወደ ቀድሞ ሰላሟና መረጋጋቷ እንድትመለስ ድጋፍ እንደሚያደርጉና የግዛት አንድነቷን እንደሚያከብሩም አሳውቀዋል።
አልዓይንይ

መስቀል አደባባይበአሁን ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ህወሓትን እና ሸኔን የሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ነው።በሰልፉ ላይ የውጭ ...
07/11/2021

መስቀል አደባባይ

በአሁን ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ህወሓትን እና ሸኔን የሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ነው።

በሰልፉ ላይ የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትንና የውጭ ሀገር መገነኛ ብዙሃንን አጥብቀው የሚተቹ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ የተፃፉ የተለያዩ መፈክሮች በሰልፈኞች ተይዘዋል።

ሰልፈኞች ካያዟቸው መፈክሮች መካከል ፦

- የአሜሪካ እና የእንግሊዝ ኤምባሲዎች ከኢትዮጵያ ይውጡና ቦታው ለልማት ይዋል።

- CNN ፣ BBC በኢትዮጵያ ጉዳይ ሀሰተኛ ዜናዎቻችሁን አቁሙ።

- የአውሮፓ መንግስታት መሰሪነታችሁን አቁሙ ፤ በግልፅ ግቡኑና ህወሓትን በጦር ሜዳ አግዙት።

- ኢትዮጵያ በውክልና ጦርነት አትንበረከክም።

- SHAME ON YOU USA !

- You are liar you can't repeat in Ethiopia again.

- Americans don't come back we are better off without you.

- የሚሉት ይገኙበታል።

በተጨማሪም ሰልፈኞቹ ከያዟቸው ሌሎች መፈክሮች መካከል ፦

- ይህ ትውልድ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ያስከብራል።

- የቀኝ ገዢዎች ሀሳብ ይመክናል ፤ ኢትዮጵያ ታሸንፋለች።

- ክብር ለመከላከያ ሰራዊት

- ኢትዮጵያን ማሸነፍ አይቻልም።

- እኔ የሀገሬ ጠባቂ ነኝ።

- ከኢትዮጵያዬ 🇪🇹 የሚበልጥብኝ የለም።

- እኛ እያለን ኢትዮጵያ ሀገራችን በፍፁም አትፈርስም፤ የሚሉት ይጠቀሳሉ።

07/11/2021

አዲስ አበባ ፓሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረት በማድረግ ለከተማው ፀጥታ ስጋት ናቸው
ያላቸውን የግለሰቦች መኖሪያ ቤቶች፣ ንግድ ቤቶች እና ድርጅቶች ብርበራ ማድረጉን አሳውቋል።

ፖሊስ አደረኩት ባለው ብርበራ ልዩ ልዩ የጦር መሳሪያዎችና ወታደራዊ ቁሳቁሶችን በኤግዚቢትነት መያዙን ገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ከህዝብ የደረሰኝን መረጃ በመቀበልና በመተንተን በ11ዱ ክ/ከተሞች የህወሃት ደጋፊና ናፋቂ በሆኑ እና በተጠረጠሩ ግለሰቦች እንዲሁም በመኖሪያ ቤቶች ፣ ንግድ ቤቶችና ድርጅች ላይ ከጥቅምት 23 - 25 ቀን 2014 ዓ/ም ባሉት 3 ቀናት ውስጥ ብርበራ ና ፍተሻ አድርጊያለሁኝ ብሏል።

በዚህም፦
- የተለዩ የጦር መሳሪያዎች
- ክላሽ- ኮቭ ጠብመንጃ
- በተሽከርካሪ በድብቅ ተጭነው የገቡ መትረየስ ጠብመንጃዎች
- የብሬን ጥይቶች
- ቦንብ
- SKS ጠብ-መንጃ
- በርካታ የተለያዩ የጦር መሳሪያ ጥይቶች
- የጦር ሜዳ መነፅሮችን
- የተለያዩ የፀጥታ አካላት መገልገያ ቁሳቁሶች
- የመገናኛ ሬዲዮ ቻርጀር
- ወታደራዊ አርማዎችና ወታደራዊ ኮምፓስ ይዣለሁኝ ብሏል።

ከእነዚህ የጦር መሳሪያዎችና የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳት በተጨማሪ የአዲስ አበባ ፖሊስ ከህወሃት ደጋፊዎችና ናፋቂዎች እጅ በህግ ከሚፈቀደው መጠን በላይ የተከማቸ የአሜሪካ ዶላር ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችና የዝሆን ጥርስም በብርበራ ወቅት ይዣለሁ ሲል ገልጿል።

በተለያዩ ተቋማት ስም የተዘጋጁ ሀሰተኛ ሰነዶች ከእነ ማዘጋጃ መሳሪያዎቹ መያዙን የገለፀው ፖሊስ በግለሰቦች እጅ መገኘት የማይገባቸው የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ሰነዶችን ጨምሮ በርካታ ፓስፖርቶች እንዲሁም የተለያዩ ሃሰተኛ ሰነዶች በቁጥጥር ስር አውያለሁ ብሏል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሰረት በማድረግ ለከተማው ፀጥታ ስጋት ናቸው ባላቸው የግለሰቦች መኖሪያ ቤቶች፣ ንግድ ቤቶች እና ድርጅቶች ብርበራ ማድረጉን አሳውቋል። ፖ....

07/11/2021

" የፖለቲካ መሰረት የሌለው ደካማ ስብስብ ነው " - ሚኒስትር ዲኤታ ከበደ ዴሲሳ

ሀገሪቱን እየመራ ያለውን የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ትላንትና በአሜሪካ ሀገር የኢትዮጵያ ፌደራሊስት እና ኮንፌደራሊስት ኃይሎች ጥምረት በሚል ዘጠኝ የፖለቲካ ቡድኖች አንድ ጥምረት መመስረተዋል።

ጥረቱን ከመሰሩቱት መካከል የህ/ተ/ም/ቤት አሸባሪ ሲል የፈረጃቸው የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (ህወሓት) እና መንግስት "ሸኔ" ሲል የሚጠራው እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሚለው ቡድን ዋነኞቹ ናቸው።

ይህ አሜሪካ ዋሽንግቶን ዲሲ ውስጥ የተመሰረተው ጥምረት በኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት የመመሥረት፤ የኢትዮጵያን መንግሥትን በኃይል አልያም በድርድር ለማስወገድ እቅድ እናላቸው አሳውቀዋል።

ይህንን ጉዳይ በተመለኩተ ቃላቸውን ለቢቢሲ ኒውስ ሃውር የሰጡት የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ከበደ ዴሲሳ፣ "ደካማ የፖለቲካ ኃይል ነው" በማለት ገልጸውታል።

በተጨማሪም በዚህ ጥምረት መመስረት "አለመደነቃቸውን" አመልከተዋል፤ ጥምረቱ በአገሪቱ ውስጥ ይህ ነው የሚባል ድጋፍ የሌለው ነው ብለዋል። "እነዚህ አማጺያን ቡድኖች መሠረት የላቸውም። ምንም አይነት ማኅበራዊ መሠረት የላቸውም፤ ምንም ለውጥ ሳያመጡ ላለፉት 40 ዓመታት እዚያው የቆዩ ናቸው።" ሲሉም ተናግረዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ከበደ ፥ "በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ መረጋጋት በሚያስፈልግበት ጊዜ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች መንግሥት ተዳክሟል፣ ሥልጣን ላይ መቆየት አይችልም ብለው ሲያስቡ ተሰባስበው ትብብር ይፈጥራሉ" በማለት ሁኔታው የተለመደ መሆኑንም ለቢቢሲ ተናግረዋል።

07/11/2021

ከፌደራል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ መምሪያ የሚተላለፉ መመሪያወች እንደተጠበቁ ሆነው÷ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት በክልሉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ የክልከላ መመሪያዎች አውጥቷል

ክልከላዎቹም ፦

1. በክልሉ ውስጥ ባሉ አካባቢወች ማንኛውም ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ከቀኑ 12፡00 ሰዓት በኋላ እንቅስቃሴ ማድረግ የተከለከለ ነው።

2. ማንኛውም የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ባለ ሶስት እግርን ጨምሮ ከምሽቱ 2፡00 በኃላ ማንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

3. የምርት ዕንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል የጭነት መኪኖች በየኬላው ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገባቸው እንዲንቀሳቀሱ የፈቀድላቸው ሆኖ ከረዳቱና ካሽከርካሪው ውጪ መጫን የተከለከለ ነው።

4. ከፀጥታ አካላት ውጪ ማንኛውም እግረኛ በክልሉ ውስጥ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው።

5. ከጤና ተቋማት፣ከነዳጅ ማደያዎች፤ከፖሊስ ጣብያ ውጪ ማንኛውም አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከምሽቱ 3፡00 በኋላ አገልግሎት መስጠት አይችሉም።

6. ማንኛውም ባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ እና አሽከርካሪ የመንግስትን ጨምሮ ከቀን 29/2/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 3/3/2014 ዓ.ም ድረስ በአቅራብያቸው ባለው የፖሊስ ተቋም ቀርበው መመዝገብ አለባቸው።

07/11/2021

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊና የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ የሆኑት ማርቲን ግሪፊትስ እና በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ ዛሬ የትግራይ ክልል መዲና መቐለ መግባታቸውን ሮይተርስ ከአንድ የሰብዓዊ ድጋፍ አድራጊ ምንጭ እና ጉዳዩን ከሚያውቅ አንድ ሰው መስማቱን ዘግቧል።

በኢትዮጵያ የሚገኘው የUN የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ቃል አቀባይ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ አልሰጠም።

በኒውዮርክ የሚገኙ የUN ባለስልጣናት ስለጉዳዩ መረጃ እንዲሰጡ ወዲያውኑ ማግኘት እንዳልተቻለ እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት ቃል አቀባይ ኢባ ካሎንዶ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አለመስጠታቸውን የዜና ወኪሉ ዘግቧል።

የህወሓት ቡድን ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ለዜና ወኪሉ ፥ "ሁለቱም ባለስልጣናት መቐለ እንደሚገኙ አረጋግጣለሁ ውይይትም እያደረግን ነው" የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ቃል አቀባይ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ በባለስልጣናቱ ጉብኝት ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አለመስጠታቸውን ዜና ወኪሉ ዘግቧል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊና የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ የሆኑት ማርቲን ግሪፊትስ ከቀናት በፊት አዲስ አበባ መግባታቸው እና ከኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት እና የአሁኑ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጎ ኦባሳንጆ የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ቆሞ ሰላም እንዲወርድ የተለያዩ ስራዎችን እየሰሩ መሆናቸው ይታወቃል።

07/11/2021

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ከሰሞኑ የተወሰኑ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች፦
- የተዛቡ፣
- ትክክለኛ የጋዜጠኝነት መርህን ያልተከተሉ፣
- የአገር ሉዓላዊነትና የህዝቦችን አንድነት አደጋ ውስጥ የሚጥሉ ብሎም የፖለቲካዊ ውግንና ያላቸውን ዘገባዎች ማሰራጨታቸውን አጥብቆ ኮነነ።

ማህበሩ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ የሰሩትን ዘገባ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህ መግለጫው ሰሞኑን አዲስ አበባን እና ዙሪያዋን በተመለከተ የተሰራጩ ዘገባዎችን ትክክለኛነትና ሚዛናዊነት ለማጣራት ጥረት ማድረጉን ገልጿል።

ለዘገባ ከተንቀሳቀሱና በየአካባቢው ከሚኖሩ አባሎቹ ብሎም ከነዋሪዎች ባገኘነው መረጃ መሰረት እስካሁን ድረስ አዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙት አካባቢዎች ሁሉ በተለመደው እንቅስቃሴያቸው ላይ ይገኛሉ ብሏል።

ማህበሩ ከሰሞኑ ዓለምአቀፍ ሚዲያዎች የተዛቡ እና ፖለቲካዊ ውግንና ያላቸውን ዘገባዎች ማሰራጨታቸውን አጥብቆ የኮነነ ሲሆን በእንደዚህ ያሉ ሙያዊ መርሆን ባልተከተሉ ዘገባዎች እየተሳተፉ ያሉ ጋዜጠኞች ጋዜጠኝነታቸውን በሙያዊ አስተምህሮው መሰረት እንዲፈፅሙ ጠይቋል።

በተጨማሪ መቀመጫቸውን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለም ያደረጉና ስለኢትዮጵያ የሚዘግቡ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ባለሙያዎች ከእንደዚህ አይነት አዘጋገብ እንዲወጡ አጥብቆ አሳስቧል።

የኢትዮጵያ መንግስትና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትም የየትኛውም መገናኛ ብዙኃን ዘጋቢዎች ተገቢውን መረጃ እንዲያገኙና በተለያዩ አካባቢዎች ተዘዋውረው እውነተኛ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ እንዲችሉ አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንደሚገባቸው አሳስቧል።

የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃንም ፈጣን፣ ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ሚዛናዊ መረጃዎችን እንዲያቀርቡ መክሯል።

01/11/2021

ኮምቦልቻ ጽናቱን ይስጥሽ!

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ማብራሪያ መስጠታቸውን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ማምሻውን ዘግቧል።በሽብርተኛ ድርጅትነት የ...
01/11/2021

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ማብራሪያ መስጠታቸውን ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ማምሻውን ዘግቧል።

በሽብርተኛ ድርጅትነት የተፈረጀው የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) የከፈተውን ጦርነት እና ጦርነቱን እየመራበት ያለው ህዝባዊ አካሄድ አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የገለፀው ቴሌቪዥን ጣቢያው ህዝብ ለመከላከያ ሠራዊቱ ያሳየው ድጋፍ የሚበረታታ እንደነበር አስታውሰዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ በቅስቀሳ የመጣውን የህዝብ ኃይል ለማስተናገድ በመንግስት በኩል በቂ ዝግጅት እንዳልነበር በዛሬው መድረክ የተናገሩ ሲሆን አሁን ላይ ከዛ ሁኔታ እርምት ተወስዶ ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ እየተሰራበት እንደሆነ መግለፃቸውን የቴሌቪዥን ጣቢያው ዘገባ ያስረዳል። #ተጨማሪ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በወሎ ግንባር በነበረ ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ተሳትፈዋል አሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው።

" በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ከአሸባሪው ቡድን ጋር ተሳትፈዋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጦርነቱ የተሳተፉት እንነዚህ አካላት ኢትዮጵያውያን ያልሆኑና የኢትዮጵያውያን ዝርያ የሌላቸው #ነጮች እና #ጥቁሮች ናቸው ብለዋል ፤ በጦርነቱ ላይ ተሳትፈውም መስዋትነት መክፈላቸውን ገልፀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የገጠመችው ጦርነት ከአንድ ወገን ጋር ብቻ እንዳልሆነ በመረዳት ህዝቡ ዋጋ ለመክፈል ያለውን ፍቅር በተግባር ሊገልጽ እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

አሜሪካን ጠላታችን ናት!!!          ብዙአየሁ ወንድሙከማንም እና ከምንም በላይ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ጠላት የአሜሪካን መንግስት ነው።~ከአሸባሪው ወያኔ ጀርባ ሆና በእርዳታ ስም ለጦ...
01/11/2021

አሜሪካን ጠላታችን ናት!!!
ብዙአየሁ ወንድሙ

ከማንም እና ከምንም በላይ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ጠላት የአሜሪካን መንግስት ነው።
~ከአሸባሪው ወያኔ ጀርባ ሆና በእርዳታ ስም ለጦርነቱ የሎጀስቲክ ድጋፍ ታደርጋለች።
~ህንድ ውቅያኖስ ላይ ሆኖ አፍሪካ ቀንድን በሚቆጣጠረው ወታደራዊ ዕዟ አማካኝነት የኢትዮጵያን ወታደራዊ እንቅስቃሴ በሳተላይት እየተከታተለ ለጠላት ያቀብላል።በክፍተቱ ጥቃቱ እንዲፈጸም ያግዛል።
~ባለው አቅሙ ሁሉ በሚገኙ ዓለም አቀፍ መድረኮች ኢትዮጵያን ለማውገዝ፣ለማግለል፣ማዕቀብ ለማስጣል ተግቶ ይሰራል።
~ሉአላዊ አገርን ከአሸባሪ ቡድን ጋር እኩል በአንድ ሚዛን ላይ በማስቀመጥ ተደራደሩ ይላል።
የመፍትሔ ጥቆማ ከተጠየኩ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እጇን ከኢትዮጵያ እንድትሰበስብና አፏን ዘግታ እንድትቀመጥ ማድረግ።ይህ ካልሆነ ሌሎችን የእሷ ተባባሪ አገሮችን ጨምሮ ኢንባሲያቸውን ዘግተው ከአገር እንዲወጡ እንጩህ።

አሜሪካ TPLF ከአማራ እና አፋር ክልሎች እንዲወጣ በድጋሚ አሳሰበች።ዛሬ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) ከአማራ እና አፋር...
30/10/2021

አሜሪካ TPLF ከአማራ እና አፋር ክልሎች እንዲወጣ በድጋሚ አሳሰበች።

ዛሬ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) ከአማራ እና አፋር ክልል እንዲወጣ፤ ወደ ደሴ እና ኮምቦልቻ ከተማ የሚያደርገውን ግስጋሴ እንዲገታ አሳስቧል።

ሚኒስቴሩ TPLF በከተሞች ላይ ከባድ መሳሪያዎችን ከመተኮስ እንዲቆጠብ ያሳሰበ ሲሆን ሁሉም ወገኖች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ተኩስ አቁም እንዲያደርጉ እና ድርድር እንዲጀምሩ ጥሪ አድርጓል።

መንግስት በመቐለ እና በሌሎች የትግራይ አካባቢዎች የፈፀማቸውን የአየር ድብደባዎች የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያወገዘ ሲሆን አሜሪካ በትግራይ፣ በአማራ፣ በአፋር ሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኗንም አሳውቋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የሚደርሰው የሰብዓዊ ድጋፎች እንዳይቆራረጡ፤ የሲቪሎች ደህንነት እንዲጠበቅና መብቶች እንዲከበሩና አጥፊዎች እንዲጠየቁም ጠይቋል።

* የሚኒስቴሩ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

30/10/2021



" እስካሁን ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል "- የአዲስ ከተማ ፖሊስ መምሪያ

መሳለሚያ እህል በረንዳ አካባቢ በአማኑኤል ህንፃ ላይ በተከሰተው የእሳት አደጋ እስካሁን 8 ሚሊዮን 370 ሺ 280 ብር የሚገመት ንብረት እንደወደመ የአዲስ ከተማ ፓሊስ መምሪያ አሳውቋል።

የእሳት አደጋውን መንስኤ እና ተያያዥ ጉዳዮች በተመለከተ በቀጣይ ምርመራ ተደርጎ ይገለጻል ተብሏል።

 #ደሴን መቆጣጠር ማለት፦(በ ዶ/ር ምስጋናው ታደሰ /ወሎ ዩኒቨርስቲ)ሆን ተብሎ እና ተፈልጎ እስኪመስል ድረስ ወሎ የጦርነት ቀጠና ከሆነ ዉሎ አድሯል፡፡ አሁን ደግሞ የጠላት ጦር የወሎ መዲና...
25/10/2021

#ደሴን መቆጣጠር ማለት፦
(በ ዶ/ር ምስጋናው ታደሰ /ወሎ ዩኒቨርስቲ)

ሆን ተብሎ እና ተፈልጎ እስኪመስል ድረስ ወሎ የጦርነት ቀጠና ከሆነ ዉሎ አድሯል፡፡ አሁን ደግሞ የጠላት ጦር የወሎ መዲና የሆነችዉን ደሴን እና የበርካታ ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች ማዕከል የሆነችዉን ኮምቦልቻን ለመቆጣጠር ያለ የሌለ ኃይሉን አሰልፎ አሰፍስፏል፡፡

ደሴን እና ኮምቦልቻን መንግሥት እንዲታደግ ስንጠይቅ መንደርተኝነት ተጠናዉቶን ወይ ደግሞ እጅግ ጠበን ስለ ሁለት ከተሞች ብቻ እያሰብን (እየተናገርን) አይደለም፡፡ እርግጥ ነዉ ደሴ የወሎ የባህልና የታሪክ ማህደር ናት፡፡ ለሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያም የአይን ብሌን ናት፡፡

ነገር ግን ደሴ እና ኮምቦልቻን ታደጉ ስንል የሀገሪቱን መዲና፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩንም ቤተ መንግሥት ታደጉ እያልን ነዉ፡፡ ደሴ በሰሜን በኩል ለሚመጣ ወራሪ የመጨረሻዋ ምሽግ ናት፡፡ ደሴን አልፎ የሄደ ጠላት አዲስ አበባን ከመቆጣጠር የሚያግደዉ ነገር የለም፡፡ የአካባቢዉ ታሪካዊ ዳራም ይህንኑ እዉነት ነዉ የሚያረጋግጥልን፡፡ ሁለቱን ታሪካዊ አጋጣሚዎች እዚህ ላይ ማስወታስ ያስልጋል፡፡

በ1928ቱ የጣልያን ወረራ ወቅት በሰሜን በኩል የመጣዉ በማርሻል ባዶግሊዮ የተመራዉ ወራሪ ኃይል ሰኞ በሚያዝያ 12 ቀን 1928 ዓ.ም ደሴን ተቆጣጠረ፡፡ ከ12 ቀናት በኋላ ሚዝያ 24 ቀን 1928 ዓ.ም ንጉሠ ነገሥቱ በጅቡቲ በኩል አድርገዉ ወደ ለንደን ተሰደዱ፡፡ ከሃምሳ አምስት ዓመታት በኋላ በተመሳሳይ ሁኔታ ታሪክ ራሱን ደገመ፡፡ ቅዳሜ ግንቦት 10 ቀን 1983 ዓ.ም ኢህአዴግ ደሴን ተቆጣጠረ፡፡ ከሦስት ቀናት በኋላ ግንቦት 13 ቀን መንግስቱ ሃይለማርያም በቦሌ በኩል ወደ ሐራሬ ሄዱ፡፡ እንግዲህ ደሴን መቆጣጠር ማለት . . . ያልኩት ከዚህ የተነሳ ነዉ፡፡

አሁንም ደሴን መቆጣጠር ማለት አዲስ አበባን መቆጣጠር እንደማለት ነዉ፡፡ የጁንታዉ ጦር ደሴን መቆጣጠር ከቻለ በቀናት ዉስጥ ወደ መዲናዋ መዳረሱ አይቀሬ ነዉ፡፡ በዚህ ጊዜ ዶ/ር አቢይ አህመድ በጂቡቲ በኩል አድርገዉ ወደ ለንደን ወይንም በቦሌ በኩል ወደ ሃራሬ ወይንም ወደሌላ መዳረሻ ይሄዳሉ ብየ አላስብም፡፡ አሁን ጊዜዉና ሁኔታዉ ሌላ ስለሆነ፡፡ ነገር ግን ጁንታዉ ደሴን አልፎ እዚህ ደረጃ ላይ ከደረሰ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ድርድ ሊመጡ ይችሉ ይሆናል የሚል ስጋት ጭምጭምታም አለ፡፡

ይህ ሁሉ ዜጋ ካለቀ በኋላ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሕይወታቸዉን ካጡ፣ ሚሊዮች ከተፈናቀሉ፣ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ንብረት ከወደመ በኋላ ለመደራደር ማሰቡ በራሱ ከሀገር ክህደት ወንጀል የሚበልጥ ወንጀል ነዉ፡፡

ከዚህ ሁሉ ዘርፈ ብዙ የፖለቲካ ቀዉስ ለመዉጣት መንግስትም ሆነ የአካባቢዉ ማህበረሰብ ተባብሮ ወረራዉን መቀልበስ ብሎም ወራሪዉን ጠራርጎ ወደመጣበት መመለስ፤ እንዲሁም ይህንን በዚህ ዘመን የበቀለ ክፉ አረም ነቅሎ እና አቃጥሎ ኢትዮጵያ እንድታርፍ ማድረግ አማራጭ የሌለዉ ለነገም ቀጠሮ የማይያዝለት መፍትሄ ነዉ፡፡

የአካባቢዉ ማህበረሰብ የሚችለዉን እያደረገ ነዉ፡፡ ከዚህ በላይም መደራጀት እና መደገፍ ይኖርበታል፡፡ የመንግሥት ቁርጠኝነት ደግሞ የነገሩ ሁሉ ማሰሪያ ነዉና ወደመጨረሻዉ እርምጃ እዲገባ፣ የተለያዩ አደረጃጀቶችን እንዲያግዝ፣ በዜጎቹ ላይ እየደረሰ ያለዉን ስቃይ እንዲያስቆም እንጠይቃለን፡፡

23/10/2021

ፕሬዘዳንት ኤርዶሃን የአሜሪካንን ጨምሮ የ10 አገራት አምባሳደሮች ቱርክን ለቀው እንዲወጡ አዘዙ

ቱርክ የአሜሪካንን ጨምሮ የ10 አገራት አምባሳደሮች አገሯን ለቀው እንዲወጡ አዘዘች።እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ የቱርክ ፕሬዘዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ባስተላለፉት ውሳኔ የአሜሪካንን ጨምሮ የ10 የአውሮፓ አገራት አምባሳደሮች አንካራን ለቀው እንዲወጡ ተወስኗል።አምባሳደሮቹ እንዲባረሩ የተወሰነው በፈረንጆቹ 2016 ዓመት ከተካሄደው እና ከከሸፈው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጀርባ እጁ አለበት በሚል ተጠርጥሮ ጉዳዩ በፍርድ ሂደት ላይ ያለ አንድ ግለሰብ ከእስር እንዲፈታ መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው።

ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫትናንት የኢፌዲሪ አየር ሃይል በመቀሌ የአሸባሪው ህወሃት ቡድን የወታደራዊ ማሰልጠኛና ማዘዣ ማእከል የሆነውና  የቀድሞ የመከላከያ ሰራዊት ማሰል...
23/10/2021

ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ

ትናንት የኢፌዲሪ አየር ሃይል በመቀሌ የአሸባሪው ህወሃት ቡድን የወታደራዊ ማሰልጠኛና ማዘዣ ማእከል የሆነውና የቀድሞ የመከላከያ ሰራዊት ማሰልጠኛ የነበረውን ቦታ በአየር መደብደቡ ይታወቃል።

በዚሁ እለት ከኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በኩል ፈቃድ የተሰጣቸው ሁለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ አውሮፕላኖች በመቀሌ እንዲያርፉ በስፍራው ካሉ የበረራ ተቆጣጣሪዎች ፍቃድ በመከልከላቸው ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውም የሚታወቅ ነው።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፈን ዱጃሪክ አውሮፕላኖቹ ከፌደራል መንግስት ፈቃድ የተሰጣቸው እንደሆኑና ወደ አዲስ አበባ የተመለሱትም በኤርፖርቱ የበረራ ተቆጣጣሪዎች ፍቃድ በመከልከላቸው ብቻ መሆኑንም አሳውቀዋል።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ አንዳንድ የውጭ መገናኛ ብዙሃን የእርዳታ አውሮፕላኖቹ የተመለሱት በየአየር ጥቃቱ ሳቢያ እንደሆነ በማስመሰል የተሳሳተ ዘገባን አውጥተዋል።

የአየር ጥቃቶቹ በከፍተኛ ጥንቃቄ የተወሰዱና የሽብር ቡድኑ ለእኩይ አላማ የሚጠቀምባቸውን የመገናኛና የወታደራዊ ማሰልጠኛዎችን ብቻ ኢላማ ያደረጉ ናቸው።

የሽብር ቡድኑ ይህንን መሰል የተሳሳቱ መረጃዎችን በማውጣት ህብረተሰቡን በሃሰተኛ ምስሎች ለማወናበድ የሚወስዳቸውን እርምጃዎች ተገንዝቦ ጥንቃቄን መውሰድ እንዳለበት መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

13/02/ 2014 ዓ.ም

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jobiraw .com posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Jobiraw .com:

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share