Agew Media Network

  • Home
  • Agew Media Network

Agew Media Network Media Company /news

የአገዎች ስልጣኔ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።........................////የአገው ነግስታት በስልጣናቸው ዘመን በአክሱማውያን እግር ተተክተዉ ለኢትዮጵያ...
26/04/2022

የአገዎች ስልጣኔ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።........................////

የአገው ነግስታት በስልጣናቸው ዘመን በአክሱማውያን እግር ተተክተዉ ለኢትዮጵያ በሀውርታዊ መንግሥትና ሕብረተሰብ ዕድገት መስፋፋት ጠንካራ መሠረት አበጅ።
በዚህ ረገድና ታሪካዊ የሽግግር ዘመን የአገው ነግሥታት 1ኛ፤ በጎሳ ፣በቋንቋና በባህል በተለየዩ በኢትዮጵያ ኩሻዊ፣ሴማዊና ናይሎቲካዊ ማህበረሰቦች መካከል ለዘላቂ ብሔራዊ አንድነትና ዉህደት ታሪካዊ የሥርዓት አንድነት አጠነከሩ ። የሮማውያንና የፋርሳውያን የአፄ መንግሥታት በአረቦችና በቱርኮች እጅ ተንኮታኩተው እንደወደቁ የአክሱማዉያን መንግስታዊ ሥርዓት እንዳይጠፋ አደረጉ ።
2ኛ፤ የአገሪቱን የአዋማዝም ፣የጁዳይዝም፣የክርስትና የእስልምና የሃይማኖችን በሚከተሉ በጎሳና በቋንቋ በተለያዩ ብዙ ማህበረሰቦች መካከል የሕግና የሃይል ተፅዕኖ ሳይደርግ በአንድ ማዕከላዊ የአፄ መንግስት ሥልጣንና ሥርዓት ስር ለአንድ የኢትዮጵያ በሀውርታዊ ሕብረተሰብ ዕድገት ሰፊ ፖለቲካዊ መንገድና መሠረት አበጅ። በአገሪቱ ረጅም ታሪክ የአገው ስርወ መንግሥት በተለይ የሰላም ዘመን ነበር ።
3ኛ ፤በድህረ አክሱም በአገሪቱ የዉጭ ግንኝነት ጉዳይ በዘመኑ በአከባቢው አዲሱን የእስላም ሃይማኖትና ሥርዓት ከሚከትሉ ሃይለኛ የየመንና የግብፅ አጎራባች መንግሥታት ጋር በተላይም በንግድና በሃይማኖት መስኮችና ጉዳዮች እንደ ወቅቱ ተጨባጭ ዓለም አቀፍ ሁኔታና አሰራር የተሸለ መግባባት ለመፍጠር ብርቱ ብሔራዊ ጥረት አድርጎል ።
4ኛ ፤በዘመኑ ከ1095 እስከ 1365 በመካከለኛው ምስራቅና በግብፅ እስትራቴጂያዊ አገሮች በአውሮፓ ክርስቲያንና በአከባቢው እስላም መንግሥትና ህዝቦች መከካል ከተካሄደው ሁሉ አቀፍ "የመስቀል ጦርነት "አገሪቱን ገለልተኛ ብሔራዊ ጥቅምና ደህንነት ሊደርስበት ከሚችለው ጉዳት በጥበብ አድኖዋል።በመሆኑም በዘመኑ በቅድስት ኢየሩሳሌም ከተማ ለአገሪቱ ቤተክርስቲያን ከእስላም ባላሥልጣኖች የአምልኮ ቦታ ለመገኘትም ችሎአል ።ይህም ለአገው መነግሥታት ዲፕሎማሲያዊ ጥበብና ችሎታ ታሪካዊ ምሳሌ ነው ።
5ኛ ፤የአገው ብልህ ነገሥታት በላስታ ከቋጥኝ ድንጋይ አስፈልፍለው ያሰሩት የላሊበላ የቤተክርስቲያን ህንፃዎች እንደ አክሱም ሾጣጣ የድንጋይ ሀውልቶች የአገሪቱ ብቻ ሳይሆኑ እንደ ታላቅ የዓለም ባህላዊ ቅርስ ናችው ።በመጨረሻም በኢትዮጵያ በሀውርታዊ መንግሥትና ሕብረተሰብ ከጥንቱ የግዕዝ ፊደልና ጽሐፈት ጋር ዛሬ ብሔራዊ የመገናኛ መሣሪያ ሊሆን የበቃው የአማረኛ ቋንቋ "ልሳነ አፄ / ልሳነ ቤተመንግሥት " ተብሎ በአገው ስርወ መንግሥት ዘመን በቤተ መንግሥት አከባቢ እንደ ተከስተ ብዙ የታሪክ ድርሳናት ይነግራሉ ።
ንብረት ተሠማ
ምንጩ ላጲሶ ጌ.ድሌቦ(ዶር)
April 26-2022
ቁጥር 2 ይቀጥላል
Also follow tele add https://t.me/muwa12

You can view and join right away.

በእንግሊዙ ዘጋርዲያን ጋዜጣ ለማጭበርበሪያነት የዋለው የዋግኽምራ ተፈናቃይ እናቶች ምስል እውነታ ተጋለጠ።ሚያዝያ 18/2014 ዓ.ም  የጌቲ ኢሜጅስ የፎቶ ጋዜጠኛ  ጀማል ኮንተስ ሰቆጣ ላይ ያ...
26/04/2022

በእንግሊዙ ዘጋርዲያን ጋዜጣ ለማጭበርበሪያነት የዋለው የዋግኽምራ ተፈናቃይ እናቶች ምስል እውነታ ተጋለጠ።

ሚያዝያ 18/2014 ዓ.ም የጌቲ ኢሜጅስ የፎቶ ጋዜጠኛ ጀማል ኮንተስ ሰቆጣ ላይ ያነሳውን የዋግኽምራ ተፈናቃይ እናቶችን ምስል የእንግሊዙ ዘጋርዲያን በትግራይ ክልል የኢትዮጵያ መንግሥት የፈጸመው በደል በማስመሰል የተጎዱ እናቶችን ምስል ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተሳሳተ መረጃ በመጠቀም ማጭበርበሩን አጋለጠ፡፡

የጌቲ ኢሜጅስ ጋዜጠኛው ጀማል ኮንተስ ያነሳው ምስል፥ አሸባሪው ሕወሓት በአማራ ክልል አገው ዋግኽምራ ከፈጸመው የሽብር ጥቃት ሸሽተው በሰቆጣ መብራት ኃይል ጣቢያ የተጠለሉትን ተፈናቃይ እናቶች መኾኑን በትዊተር ገጹ አስፍሯል፡፡

ምስሉንም በዚህ ዓመት በፈረንጆቹ መጋቢት 30 ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይፋ እንዳደረገው አመላክቷል።

ነገር ግን ዘጋርዲያን ይህንን ምስል የተጠቀመው “በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ” በተሳሳተ መልኩ ለማሳየት እና ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማጭበርበር ነው ሲል የፎቶ ጋዜጠኛው አጋልጧል፡፡

ዘጋርዲያን የፈጸመውን አሳፋሪ ተግባርም አሜሪካዊቷ ጋዜጠኛ አን ጋሪሰን ኮንናዋለች፤ ጀማል ኮንተስ ፎቶውን ሲያነሳ አብራው በሰቆጣ መጠለያ ጣቢያ እንደነበረችም በትዊተር ገጿ ምስክርነቷን ሰጥታለች፡፡

እንደ ፋብኮ ዘገባ ምስሉ በትግራይ ክልል ውስጥ ያሉትን እናቶች ሳይኾን የሚያሳየው አሸባሪው ሕወሓት በአማራ ክልል ዋግኽምራ ላይ ከፈጸመው ወረራ ራሳቸውን ለማዳን ሸሽተው በሰቆጣ የሰፈሩትን ተፈናቃይ እናቶች ነው ስትልም ዕውነቱን በትዊተር ገጿ አስፍራለች፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን በቴሌግራም አድራሻ መገኘት ይችላሉ https://t.me/muwa12

You can view and join right away.

አገዎች : የውሀ - ሽታ : እስኪሆኑ : አልታገሥም!============================ (በ Mulugeta Zegeye)" ዶሮን: ሲያታልሏት : በመጫኛ: ጣሏት"  አገዎች :  ዶሮ ...
19/04/2022

አገዎች : የውሀ - ሽታ : እስኪሆኑ : አልታገሥም!
============================
(በ Mulugeta Zegeye)
" ዶሮን: ሲያታልሏት : በመጫኛ: ጣሏት"
አገዎች : ዶሮ : ነው : የሆነው::
" ልዩ : ዞን" : ተብሎ : እንኳን: አገውኛ : ሊችል: አገዎችን: የሚንቅ : ሲሾምባቸው : ንቀት : ነው::
አገው : ሆናችሁ : ቋንቋውን: የማትችሉ:
አገውኛ: ተማሩ::
መማር : ካልፈለጋችሁ:-
አመራሩን: ለሃገሬ : ብልህ : አገው : አርሶ - አደሮች ልቀቁ::
አገው " : የህዳር : አህያ " : አይደለ:ም!!
ዝምታን: የመረጥነው : ኢትዮጵያ : ሃገራችን: ስለምናፈቅር : እንጂ :-
እንቶ - ፈንቶ : ከተባልን: መንገዱ : ጨርቅ : ነው::
አገዎች : ይህ : ምርጫችን:አይደለም:
ሃይለኛ : ቃል: ነው : የተጠቀምኩት::
ወገኖቼ : የውሃ - ሽታ : እስኪሆኑ : ግን አልጡብቅም! በቃ - ይብቃ! Enough!
=================================
( አንዳንድ : ሙሁራን: ብለው : የሚተቹ: አሉ)
ይተቸቹ:: መብታቸው : ነው::
ግን: ምንም: ሳያደርጉ : ለሀገርና- ወገን: በሚጥሩት : ላይ : ጣት : መቀሰር: አይገባም::
ብማርም: - የቻልኩትንም: ባደርግ:-
እኔ : እራሴን: ሙሁር : ብዬ : አላውቅም::
ባወቅሁ : ቁጥር : የጥበብ: ጉዞ : እሩቅ - ጥልቅ: መሆኑን: ነው : የማውቀው::
ምንም- ይሁን: ምን: ጊዜው : ሳይመሽ: የሚቻለውን: ሁሉ : ማድረግ: ብልህነት: ነው!!

የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ከአገው ህዝብ ጥቅም የሚያስበልጠው ምንም ምድራዊ ምክነያት የለውም።----------------ቀጥሎ ያለውን የወንድሜ የይደግ አለሙን ጽሁፍ  ሳነብ መጀመሪያ ለምን እንደ ...
17/04/2022

የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ከአገው ህዝብ ጥቅም የሚያስበልጠው ምንም ምድራዊ ምክነያት የለውም።
----------------
ቀጥሎ ያለውን የወንድሜ የይደግ አለሙን ጽሁፍ ሳነብ መጀመሪያ ለምን እንደ ኃላፊነቱ የሸንጎው ስራ አስፈጻሚ እያለ የተነጋገርነውን ያልተሳካ የፓርቲውን ሚስጢር ለህዝቡ ለጠፈ ብዬ አሰብኩ ቆይቼ ሳገናዝብ ግን እንዳውም ጥሩ አጋጣሚ ነው ምክኒያቱም የአገው ሸንጎ መሪዎች ለአገው አያስቡም፣ንጎውን ወያኔ ነው ያቋቋመው፣ያለ ወያኔ ፈቃድ ምንም የማድረግ መብት የለውም፣ ወዘተ....እያሉ ለሚቃዡ አሳሳቾች የሸንጎውን በነጻ የመወሰንና ማንም እንደማያዘው በሌላ በኩል ደግሞ የአገውን ህዝብ ይጠቅማል ብሎ ካመነበት እራሱን እስከ ማክሰም እንደሚወስን ይሄ ድር አረጋጋጭ በመሆኑ።
በርግጥ ሸንጎው እንደ ፅኑ አላማ ያለው የተፈተ በታላቁ የታሪክ አውራ በአገው ህዝብ ስም እንደተቋቋመ ፓርቲ የአገውን ህዝብ ሊጠቅሙ የሚችሉ የተሳኩና ያልተሳኩ አሁንም በሂደት ላይ ያሉ ከዚህም የከበዱ ሚስጢራዊ ድርድሮችን ያከናወነና እያከናወነ ያለ ቢሆንም።
ከብልፅግና ጋር እንድንደራደር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሽማግሌ ሲልኩብን በዙሪያቸው ያሉ የአገውን መደራጀት የማይወዱና በተለይ ሸንጎው እራስ ምታት የሆነባቸው አካላት .."እባከዎ አይድከሙ ወያኔ ካልፈቀደ እሽ አይልም"..።
ብለዋቸው እሳቸው ግን የደህንነት ሰው በመሆናቸው ማን ተለጣፊ ማን ነፃ ማን ለህዝብ እንደቆመ ማን ለጥቅምና ለስልጣን እንደሚሰራ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ሽማግሌውን ላኩብን ።
እኔም ወዲያው የሽማግሌውን መልክት እንደሰማሁ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኛ ጋር ለመደራደር ለምድር የከበደ የአገው ሰው መላካቸው ለአገው ህዝብ ያላቸውን ክብር የሚያሳይ በመሆኑ በቶሎ ከስራ አስፈጻሚው ጋር ተወያይተን ውሳኔያችን እንደምንገልፅ በአክብሮት ነግሬ ወዲያው ስራ አስፈጻሚው ተገናኝቶ በመወያየት ጥያቄውን በክብር የተቀበለው መሆኑንና የአገውን ህዝብ እስከጠቀመ ድረስ መከፈል የማይገባም ቢሆን ለመክፈል ዝግጁ መሆናችን አሰረግጠን። ሸንጎው ለቀጣዩ ድርድርም እኔን ጨምሮ 3 አመራሮችን የወከለ መሆኑን በ48 ሰዓት አሳወቀ።
ጠቅላዩም ለኛ ጨዋነትና ልበሙሉነት ለተሞላበት መልስ አድናቆታቸውን ችረው በደረሳቸው በሰዓታት ውስጥ
በከፍተኛ የብልፅግናና የመንግስት ሚኒስትሮች አዋቅረው የመደራደሪያ ነጥቦቻችን ይዘን እንድንቀርብና ተደራድረን በፍጥነት ለውጤት እንድንበቃ አሳሰቡን።
ሸንጎው 8 ነጥቦችን ለመደራደሪያ መርጦ ተከታታይ ድርድሮችን አድርጎ በፌደራል መንግስትና በጠቅላዩ ትንሽ ማስተካከያ ብቻ ተደርጎ ሁሉም ነጥቦቻችን ተቀባይነት አገኙ።
በነሱ በኩል የቀረቡት ላይም ብዙዎቹን ጥለን ያቀረብነውን ብዙ ተነጋግረን ተስማሙ።
የፊርማ ቀጠሮ ለመያዝ ተቀጣጥረንከተደራዳሪ ከሚኒስትሮቹ ተለያይተን ለሸንጎው ስራ አስፈጻሚ በየጊዜው የደረስንበትን እያቀረብን ስለምናስገመግም ዛሬም በደረስንበት ጉዳይ ስንነጋገር ያልጠበቅነው ሃሳብ ተነሳ እሱም "በዚህ ድርድር የአማራ መንግስት (ብልፅግና) ካልተገኘ ከፌደራል ጋር ብንስማማም አፈጻጸም ላይ ያሽቸግራል የሚል ነው ብዙ ተወያዬን የአማራ መንግሥት መገኘት ግድ ሆነ ያለኔ የሁሉም ውሳኔ አፀናው።
እኔም ሃሳቡን ሳልቃወም ዝም ብለን አሁን በተስማማነው መሠረት ከጠቅላዩ ጋር እንፈራረም ሸንጎውን ለማፍረስ የ3 ወር ጊዜ ስላለን በውሉ መሠረት ካልፈጸሙ መተው እንችላለን የሚል ነበር።
በነገራችን ላይ የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ጋር ለመዋሃድ እየተደራደርን ነው የሚል አጀንዳ ቀርቦለት ተቀብሎ አፅድቆ ነበር የኔም ሃሳብ ማዕከላዊ ኮሚቴ የአማራ ብልፅግናም ስላለ በሚል ነበር።
ስራ አስፈጻሚው ግን ትላንት ተስማሙ ዛሬ አፈረሱ ከመባል የአማራ ወኪሎች በድርድሩ ይኑሩ በሚል አቋም ፀኑ ።
የቤኒሻንጉል ተወካይም ይኑር የሚል ተጨመረ እኔም ሽንፈቴን ተቀብዬ የብልግናን ተደራዳሪ ለሚመሩት ሚኒስትር የሸንጎውን ስራ አስፈፃሚ ውሳኔ አሳወቅሁ።ከተወሰኑ ቀናት በኋላ የአማራና የቤኒሻንጉል ወኪሎች ተጨምረውበት ድርድሩን እንደገና ከስሩ ጀመርን በ3ኛው ዙር የአማራ ወኪል የሆኑት አንዱን የመደራደሪያ ነጥባችን አጥብቀው ተቃወሙ ይሀኸውም "..ሸንጎ የሚለው ስም በውህደት ፈርሶ.የአገው ብልፅግና ፓርቲ ተብሎ ይጠራል ተጠሪነቱም ለፌዴራል ብልፅግና ፓርቲ ነው.." የሚል ነው (ልክ እደ አማራ ፣ኦሮሞ ፣አፋር ወዘተ ማለት ነው) ተቃውሟቸው በአማራ ክልል እንዴት ሁለት ብልፅግና ፓርቲ ይኖራል የሚል ነበር።
የሚገርመው ግን ከነጥቦቹ ውስጥ ።
-አሁን የአገው ዞን ተብለው የሚጠሩትን አዊ አገውን፣ዋግ ኽምራን፣ ኮረም ኦፍላን፣ ጣቋ አበርገሌን (ፊናሯን) ሙሉበሙሉ ተረክቦ ያስተዳድራል ።
መተከል፣ባምባሲ፣ቋራ፣የላሊበላ ወረዳዎችን፣በለሳ፣ተምቤን ፣ሳምረ ሳህርቲ፣ቦራ ሰለዋ (በዋግ ያለው ሳይሆን በትግራይ ያለውን) ወረዳዎች በአካባቢው ካሉ ሌላ ህዝቦች ጋር በጋራ አገው ብሔራዊ ሸንጎ ያስተዳድራል ።
-የቅማንትን ህዝብ የማንነት ጥያቄን መንግስትንና ብልፅግና ፓርቲን ወክሎ አገው ብሔራዊ ሸንጎ ይፈታል በህዝቦቹ ፍላጎት መሰረት አስተዳደሩን ያቋቁማል።
የሚሉ ነጥቦችን ፌደራሉ ያጸደቃቸውን አልተቃዎሙም።
ሁሌም ግን በሌላ አማራጮች ድርድር አልተቋረጠም
ዞሮ ዞሮ ብዙ የተገቡም ያልተጋቡምነገሮች ተነጋግረን በዚሁ ድርድሩ ቆመ ።
ሁሌም ግን በሌላ አማራጮች ድርድር አልተቋረጠም ።
ይህ የሆነው ህወሐትም የትግራይ መንግስትም በህጋዊ ተቋምነታቸው እያሉ ከመጋቢት እስከ ግንቦት 2012 ዓ/ም ነው።
አላምረው ይርዳው 09/08/2014
===========================
ተጻፈ በይደግ አለሙ ታረቀ
ሸንጎን አፍርሳችሁ የአገው ብልጽግና ብላችኁ ከኛ ጋር ተቀላቀሉ የሚል ሰነድ እና ድርድር በዶ/ር አለሙ ሰሜና በሸንጎ ተጀምሮ ነበር፡፡ እኔ ሸንጎ ቢፈርስ የአገው ህዝብ ብዙ ነገሮችን ያጣል ፤ ሸንጎ ከህጋዊ ፓርቲነቱ ይከስማል ፤ የሚል ጥያቄ አንስቸ ነበር፡፡ አቶ አላምረው አያጣም ለምሳሌ፡-
1) አገው ክልላዊ መንግስት ጥያቄን አብረን እንታገላለን ( የፓርቲውን አላማ ዋና አላማ ካሳካን..ሌላ ምን ይፈለጋል)
2) ክልሉ በሸንጎ እና በብልጽግና ይዋቀራል
3) አከባቢወ በሰው ሰራሽ/ተፈጥሮ የተጎዳ ነው በልዩ ሁኔታ በበጀት ሊደገፍበት የሚችል ሆኔታን ይመቻቸል ( አሁን 1 ቢሊያን ያልሞላ ብር ነው የሚበጀተው እስከ 10 ቢሊየን ብር እንዲበጀት እንጠይቃለን) የሚል ነበር፡፡
4) )በስም ብልጽግና ይባል እንጂ የኢሃዴግ አብኛው (የፓርቲው) ሃብት ብልጽግና ውስጥ ይገኛል ይህም ሸንጎ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ይሆናል እያለ ቀጠለ…
ድርድሩን የሰማው ብአዴን- ራሴን ከብልጽግና አገላለሁ አለ፡፡ ሰሞነኛ ኦሮ-ማራ የሚል ጋብቻ ላይ የነበረው ኦፒዲኦ ብአዴንን ማጣት አልፈለገም- አቶ ዩሃንስ ቦያሌው ሰሞኑን ያለው ነገር ግን ገርሞኛል፡፡ ከ እኔ አንዳንድ አቋም ጋር ተመሳሳይነተ አይቸበታለሁ ያልኩት ጓደኛየ ፡፡ ልክ እንደ አቶ ጸጋ አብይ ለሰሞነኛው ፓለቲካ ማብረጃ በል ብሎት ነው አለኝ፡፡

17/04/2022

አማራን ከሌሎች ወንድሞቹ ለመነጠል የሚደረገው ሴራ መቆም አለበት፡፡

ህዝባችን ኢትዮጵያን በመገንባት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ሚና እንዳለው ሳይታለም የተፈታ ሃቅ ነው፡፡ በማህበራዊ ህይወቱ ተግባቢ፣ ሰው አክባሪ፣ ለቃሉና ለኃይማኖቱ የቆመ፣ አርቆ አሳቢና ከሌሎች ማህበረሰቦች ጋር አብሮና ተደጋግፎ የመኖር ፍላጎት ያለው እና መገለጫው ሆኖ እያለ ከራሳችን አብራክ የወጡ ለፖለቲካ ፍጆታቸው ሲሉ ከወንድም ህዝቦች ጋር እንዲጋጭ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ሁሌም ቢሆን በኢትዮጵያዊነቱ የማይደራደር ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ተጋግዞ እና ተባብሮ የሚኖረውን ህዝባችንን አብሮነቱን የሚሸረሽሩ ነገሮችን ሲመለከት በዝምታ ማለፍ የለበትም፡፡

አንድነታችን እና ከሌሎች ጋር ለመኖር ያለንን ህብረታችንን ማስቀጠል ሲገባን ይሄንን እሴታችንን ወደ ጎን በመተው ትላንት በህወሃት ወረራ ሲፈጸምብን አለውልህ ካሉን ሌሎች ወንድም ብሄር ብሄረሰቦች ጋር ለማጋጨት ሲጥሩ እየተመለከትን ነው፡፡ አሁን ላይ ከአብራኩ የወጣን አዋቂነን ባዮች በችግሮቻችን ጊዜያት ሁሉ አብረውን ሲቆሙ ከነበሩት ወንድም ህዝቦች ጋር በማጋጨት እና ቅራኔን በመፍጠር ሰላም እንዳያገኝ የማድረግ አባዜ ተጠናውቶናል፡፡ ታዲያ አብሮ ለመኖር ዋናው አስቻይ ነገር መከባበር ሆኖ ሳለ ልዩነትን እና ጥላቻን እየሰበኩ አማራ ከሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ጋር የተረጋጋ ህይወት እንዳይኖረው እንዲሁም ከሌሎች ጋር አብሮ የመኖር ጥያቄ ውስጥ በመግባት ላይ ነው፡፡ እስከመቼስ የፖለቲከኞችን ፍላጎት ለማሳካት ሲባል አማራ ያልሆነ መስዋትነት እየከፈለ ይኖራል!

ከዚህ በፊት የትግራይ ወራሪ ሃይል ባደረሰብን መከራ እና ስቃይ ለማገገም በራሱ ብዙ አመታት ይፈጅብናል። ይህ አልበቃ ብሎን ዛሬም እኛ እናውቅልሃለን ባይ ፖለቲከኞች እና አክቲቪስቶች ሊያስወርሩን እየሄዱበት ያለው ርቀት ጤናማ አይደለም፡፡ ከወንድም የኦሮሞ ህዝብ ጋር እያጋጩን እንዲሁም ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦችን በላያችን ላይ በማነሳሳት ሊያስጨርሱን ቆርጠው ተነስተዋል፡፡ ከሁሉም ጋር ተነካክሰን እንዴት መኖር ሊቻለን?
አይበለውና ትላንት የተፈጸመብን ቁስል ሳይደርቅ ሌላ ችግር ቢነሳብን ማንስ ነው ከጎናችን የሚቆመው ? በዚህ መልኩ ተዚህም ተዚያም የተወጣጠረው ፖለቲካችን ሊጎዳን እንጂ ሊስተርፈን አይችልም፡፡ እንደሚታወቀው ጥቂት የማይባል ቁጥር ያለው ከክልላችን ውጪ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ተጋብቶ እና ተዋልዶ የሚኖረው ህዝባችን ጉዳይስ አያሳስበንም ? እጣ ፈንታው ምንድን ነው ? ስለዚህ ለራሳችን ብለን ከሌሎች አጎራባች ክልሎች ጋር ሰላም መፍጠር ለነገ የምንለው አይደለም፡፡ በዚህ አካሄዳችን ተጎጂ እንጂ አትራፊ አንሆንም፡፡ አሁን ላይ የግጭት ነጋሪት የምንደልቅበት ሳይሆን ቆም ብለን ራሳችንን የምንመለከትበት ጊዜ ላይ ነው የምንገኘው፡፡
ሰላም ለህዝባችን!

14/09/2021

ታላቁ የአገው ህዝብና ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ‼️

👉 ክፍል ሁለት
👉ሼር አድርጉ‼️

የአገው ህዝብ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አማኝ ነው ።ግን ቤተክርስቲያን አማኝ ነው ብላ አላያችም ለዚህም ማሳያዎችን ላቅርብ‼️

በህገ ቤተክርስቲያን አንቀፅ 5ቁጥር 2 የቤተክርስቲያን የስራ ቋንቋ አማርኛ ግዕዝ እና በአካባቢው የሚነገረው ቋንቋ ነው ይላል።ይህ ህግ አገው ላይ ሲሆን አይተገበርም ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ለአዊ ዞን ለወንጌል ማስፋፊያ የተወሰነው የበጀት ውሳኔ በአባቶማስ አዊዞን ላይ ለታለመለት መንፈሳዊ ዓላማ አለመዋሉን እንይና ፍርዱን ለህሊናችን እንስጥ።

👉 በዓመት 250ሺ ብር ለአገውኛ ቋንቋ አብነት መምህራን ትምህርት ማደራጃና ማስፋፊያ ተብሎ ከጠቅላይ ቤተክህነት ይመደባል። የአዊ ዞኑ ፖለቲከኛው ጳጳስ ግን ከተመደቡበት ቀን አንስቶ አንድም ቀን ለአንድም መርጌታ ክፍያውን ሰጥቶ አያውቅም ብሩን በኪሱና በአበል መልክ ያወራርደዋል።

👉 80ሺ ብር በአገውኛ ተምረው ለሚያስተምሩ ዲያቆናት ካህናት ተብሎ በስብከተ ወንጌል መምሪያው ይመደባል አንድም ቀን አሰልጥነው ሲያስመርቁ ግን አይተናቸው አናውቅም።እንግዲህ ይህንን ሁሉ በጀት በኪሱ በማድረግ የአዊ ዞን ሀገረ ስብከት ፖለቲከኛው ሊቀ ጳጳስ ተጠያቂ ናቸው።

በቋንቋ ማገልገል ነውር ነው ብሎ ስለሚያምን በስንት ልፋት እና ድካም የአዊኛ መፅሐፍ ቅዱስ ትርጉም ስራ ሲጀመር ተርጓሚዎችን "ከሀገረ ስብከቱ እንዳይገቡ አገው የሚባል ከቢሮው ማየት አልፈልግም ተከራይታችሁ ስሩ" ብለው በማባረር ከውጭ ተከራይተው እየሰሩ እንደሆነም መረጃው አለኝ ።አገውኛ ተናገሪ ሊቅ ከአጋጠመው ከቤተክርስቲያን አገልግሎት ያባርርና ለአላስፈላጊ እንግልትና ወጭ እንዲዳረጉ ልጆች በረሃብ እና በጥም እንዲሰቃዩ በማድረግ መንፈሳዊ አገልግሎቱ እንዲስተጓጎልም እያደረጉ ነው።ለዚህም ማሳያ የምንጠቅሰው የዚገም ወረዳ ቤተክህነት ስራ አስኪያጅ የነበረውን መልአክ ህይዎት ሀብተማርያም አላምረውን "አገውኛ ባይናገርም አገዋዊ ስነልቦና አለው" በማለት ሊቀስዩማን መዝገቡ የሚባሉት ሊቅ አባት ላይ በደል ፈፅመዋል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ጥናት ተደርጎበት ወንጌል እንዲዳረስ ምዕመናን በራሳቸው ቋንቋ የእግዚአብሔርን ቃል እንዲማሩ መደረግ አለበት የሚለውን ትዕዛዝና ህግ በመተላለፍ አማርኛ የማይሰሙ ምዕመናን በቋንቀቸው ወንጌል ተደራሽ እንዳይሆን እንቅፋት በመፍጠር ላይ ይገኛሉ።

👉 ቤተክርስቲያን መሪዎችም ኽምታጛ ፣የጉራጌ፣የወላይታ፣የከንበታ ፣የኦሮሞ፣የሲዳማ ወዘተ..ቋንቋ ተናጋሪ ሊቃነ ጳጳሳትን ቋንቋን መስፈርት አድረጋ ስትሾም የአገውኛ ተናጋሪዎችን ዘላቸዋለች ። የተመረጡ ሊቃነጳጳሳት በቋንቋቸው ስብከተ ወንጌል እያስፋፉ እና ተልእኮውም እየተከናወነ ነው ።

የሚገርመው ቲዎሎጂ ለመማር ለአዊ ዞን በተሰጠው ኮታ ዘመዶችን እንደሚልኩ ራሱ ታውቁ ነበር?
ለአዊዞን አገው ምድር ግን የዚህ እድል ተጠቃሚ ሳይሆን ቀርቶ የማኀበረ ቅዱሳን ቢሮ ሲታሸግ እና ሲባረሩ ፣ወጣቱ ሰ/ት/ቤት በፓለቲከኛው ጳጳስ ተብዬና ጀሌዎቹ በአውደምህረት ሲደበደቡ፣ሊቃውንቱ ሲባረሩ ፣በተመደበው ብር ዘመድ አዝማድ ስራ ሲያስጀምሩ ፣ገመድ አፍ ቁልፍ አፍ ተብታባ ተብለው ሲሰደቡ በቋንቋቸው እንዲሸማቀቁ ሲያደርጉነው የሚኖሩት ምን አለ እንደሌሎች ቋንቋዎች ተመሳሳይ ውሳኔ ቢተላለፍላቸው።ህዝቡም ይግባኝ ለክርስቶስ እንዳለ ቀኑ መሽቶ እየነጋ ነው‼️
ክፍል ሦስት ይከታተሉ....

የምንናገረው እውነት ነው‼️ዛጉዌዎች ነንና‼️

Like 👇Comment 👇Share👇
Zagwe's Informer

14/09/2021

ታላቁ አገው ህዝብ እና ኦርትዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ‼

ክፍል አንድ

ይነበብ እና ኮሜንት ሼር ይደረግ‼

እግዚአብሔር ሐዋርያትን በጊዜው በዓለም ይነገር በነበረው በ72ቋንቋዎች ወንጌልን ለዓለም እንዲሰብኩ አሰማራቸው።በዚህም ከቋንቋ ቋንቋ ሳታበላለጥ ለብዙ ዘመናት ቤተክርስቲያን ወንጌል አግልግሎት ይሰጥባት ነበር።

ይህ ቋንቋ ቅዱስ ይህ ርኩስ ነው ብሎ የገደበውም አልነበረም ይህ ብቻ ነው የቤተክርስቲያን ልሣን ብሎ የገደበው ትዕዛዝ የለም።ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንዳንድ የክህደትና የጥርጣሬ መንገድ መሪዎች ለራሳቸው ዓላማ ማስፈፀሚያ ይሆናቸው ዘንድ ሴራ እየሸረቡ ቤተክርስቲያናችንን ምሽግ አድርገው በተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳዊ ማህበረሰብ ክፍል በደል አድርሰዋል።

በቤተክርስቲያን ለአገልግሎት ከምንጠቀማቸው መፅሐፍትም በስርወፅ ብዕለ ነገሥት፣ገድለ
ተክለሃይማኖት፣ገድለመብአ ፅዮን በዋልድቢት ማርያም ገዳም የታተመው እና መሠል የደብተራ የክፋት ቀለማት ያረፉባቸው ብራናዎች አገውን አምርረው የሚረግሙና የሚጠሉ ናቸው።እነዚህን ህፀፆች በድጋሜ በቤተክርስቲያን እንዳይገኙ ተወግዘው እንዲቃጠሉ የቤተክርስቲያን ጠንካራ ሊቃውንት ስምምነት ላይ የደረሱ መሆናቸውን አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ።ነፍሳቸውን ይማረው በረከታቸውም ይድረሰንና እና አለቃ አያሌው ታምሩ በዚህ በጣም ጥሩ የሆነ ስራ እንዲሰራ ጥረት አድርገዋል ሰርተዋልም‼

አሁን ግን ያን ሰው ሳያውቅ የተሰራ ሴራን ያለፈውን ጭምብል ለመጠቀም የሚሯሯጡ አካላት በየጊዜው ብቅ እያሉም ነው።ለዚህም በእንጅባራ አዊዞን ሀገረስብከት አባቶማስ በሚባለው ፖለቲከኛ ባለወፍራም ደሞዝ ተከፋይ ጳጳስ እና ጀሌዎቹ እየተደረገ ያለው ሸፍጥ ከቤተክርስቲያን ማምለክን ሳይሆን ይህንን ተንኮል የሚሰሩ ሰዎች ላይ ርምጃ ቢወሰድባቸው ራሱ ፅድቅ የሚያስመስል ነገር እየተሰራ ያለው ትልቅ ማሳያ ነው።ታላቁን የአገውን ህዝብን ከቀደመችዋ ከኦርቶዶክሳዊ እምነት ለማሸሽም እየተሞከረ ነው።

በቅርቡ ከታዩ ክስተቶች እና ምልክቶች አንዳአንድ እያልን እንዘረዝራለን። ይህንን ሀሳብ ከበድ ያለ የቤተክርስቲያን ነፃነትና ገለልተኛ መሆንን ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከት ክስተት በመሃል እንጅባራ ሰሞኑን የተፈጠረው ክስተት ነው።ነገሩ እንዲህ ነው።ባሳለፍነው ሳምንት የተፈፀመ ነው።አዲስ በእንጅባራ ከተማ በተሰራው ቤተክርስቲያን ላይ የቤተክርስቲያን ሊቃውንትን እና አገልጋዮች ለመቅጠር በዝግጅት ላይ የሚገኝ ሆኖ አዲስ ለሚገባው ታቦት ምዕመናን መድኃኔዓለም ታቦት ይግባ ሲሉ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ አቡነ ቶማስ የዑራኤል ነው የሚገባው ይላሉ።ሁሉም የእሳቸውን ቃል በመቀበል በአንድነት ተስማሙ ።

ነገርዬው የከፋው ግን በቀዬው ያሉት ከተለያዩ ቦታዎች ከሞት ተርፈው የመጡ ተፈናቃይ ካህናት እና የተማሩ ሊቃውንት በክፍት ቦታው እንዲቀጠሩልን ሲሉ ለትምህርት አኮፋዳ ይዘው አገው ምድር የገቡት ኋላም ቀድመው ሁሉን ነገር የተቆጣጠሩትን አቡነ ቶማስን "አባታችን እኔን አገው አይደለህም ብለው እንጀራ አይሰጡኝም" ብሎ ዘበኝነት ተቀጠረ ።አሁን እኒሁ ሰውዬ ስራ አስኪያጅ ሁነው አገው ምድር ያለችውን ቤተክርስቲያን እየመሩ አሁን ከተመደበው አባቶማስ (ፖለቲከኛው ጳጳስ)ጋር ሁነው "አገውን የምንበቀልበት ጊዜው አሁን" ነው በማለት ካሉት 21 ሰራተኞች 3ሰው ብቻ አዊዞን ከአስገባ በኋላ ሌሎችን ከደምበጫ እና ከቋሪት ሰብስበው "አዲሱ ቤተክርስቲያን ላይ ቁልፍ አፍ የሆነ ተዐምረ ማርያም መድገም የማይችል አገው አልቀጥርም፤ተዐምረ ማርያም ቁልፍና ተብታባ ገመድ አፍ ሆናችሁ እያለ እንዴት አድርጋችሁ ልታነቡ ነው ታስቀስፉናላችሁ አማርኛ በደንብ የሚችል ከሌላ ቦታ አምጥተን እንቀጥራለን እንጂ እናንተ በፍፁም እዚህች ቤተክርስቲያን አትቀድሷትም " በማለት የእግዚአብሔርን ቤት ለግል ፍላጎት ማስፈፀሚያ እየተጠቀመ ይገኛል።

ምዕመናን ማንኛውም ሊቃውንት የኦርትዶክስን አስተምህሮ እስከተከተለ ድረስ እንደማንኛውም መንፈሳዊ አባት እኩል የመቀጠር ዕድል ሊኖረው ይገባል።ዓላማው አገውን ከኦርቶዶክስ መግፋት ነው ?ወይስ ብሔረተኝነትን ማስፋፋት?

👉 ስለዚህ የአገው ኦርቶዶክሳዊት ወጣት ስራ አስኪያጁ ዘርአዳዊት እና አባ ቶማስ (ፖለቲከኛው ጳጳስ) በአገውምድር ኦርቶዶክስ እንዳያብብ ለማድረግና በቋንቋው መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኝ ለማድረግ የሚሰራውን ሸፍጥ ተረድተህ ከአባቶችህ ጎን ቁም‼️
ክፍል2 ይቀጥላል
የምንናገረው እውነት ነው‼ዛጉዌዎች ነንና‼
Like Coment Share
Zagwe's Inf

14/07/2021

አገዎች በዚህ አሸናፊና ተሸናፊ በማይኖርበት የአንድ
እናት ልጆች ጦርነት ተሸናፊ ታሪክ እንዳንሰራ አደራ።
=============================
አገዎች በዚህ ከባድ የፈተና ወቅት አገው ሆነን ለሰላም ልዕልና ከመቆም የተሻለ አማራጭ የለንም።
ኢትዮጵያችን አገው ወላጆቻችን ከሌሎች ኢትዮጵያን ጋር በደማቸውና በአጥንታቸው አፅንተው በጥበብ ያቆሟት ባለድንቅ ታሪክ አገር ናት።
ዛሬ ሃገራችን ጉልበት እንጅ ጥበብና ፈሪሃ እግዚአብሔር በሌላቸው እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው እንስሳ ለተውልድ በማያስቡ በድሃ ልጅ ደም ቁማር በሚጫወቱ ግዴለሾች እየታመሰች ነው።
እኛ አገዎች ከጥንታዊያን ወላጆቻችን የተማርነው ሃገርን በጥበብ ህዝብን በፍቅር መምራትንና በኛ ላይ ሊደረግብን የማንወደውን በሌሎች ላይ አለማድረግን ነው።
ለዚህም ማሳያው የዛጉዊዬ ስርዎ መንግስት ከ337 ዓመት በላይ ኢትዮጵያን ሲያስተዳድሩ የስልጣን ጉጉት ሳይኖራቸው ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እያደረጉ ለአገራቸው ለሐይማኖታቸወና ለህዝባቸው ቀናኢ ሆነው እራሳቸውን እንደ ህዝብ አገልጋይ ቆጥረው ያለ ኮሽታ ኖረዋል።
ይሁን እንጅ ከዛጉዬ የሴራ ውድቀት በኋላ ባለፉት 750 ዓመታት በላይ ኢትዮጵያዊያን ለስልጣን የመገዳደል ታሪካቸው ጎልቶ የህዝቡ ድህነት በዝቶ የመከራ ዘመናትን አሳልፏል።
ይሄ ለስልጣንና ለጥቅም የመገዳደል ታሪካችን ከኛ አልፎ አለምን አማሯል።
በዚህ በኛ ዘመን ደግሞ በብሔር ዝቅ ብሎም በመንደር ተከፋፍለን እስከ መገዳደልና መጠቃቃት ተደርሷል።
በእውነቱ ይሄ አሳዛኝ፣አሳፋሪ አክሳሪ እንደ ሃገርም አንገት አስደፊ ነው ።
በዚህም አልበቃም ጉልበተኞቹ ዛሬም ወደፊትም የበለጠ ሊያጫርሱን ኢትዮጵያችን ያለሃፍረት ሊያፈርሱ ጎራ ለይተው ሰፊ ጦርነት ውስጥ ገብተዋል።
ለሃገራችን እዚህ የውርደት ደረጃ መድረስ በተለይም ሁሉም ባለፉት 50 ዓመታት አለመግባባቶችን በጦርነት ለመፍታት ጎራ እየለዩ ህዝቡን ለርስ በርስ ፍጅት የዱረጉ አካላት በታሪክ ተጠያቂ ናቸው።
በኔ እምነት ሲጀመር ጀምሮ በዚህ በሰለጠነ ዘመን አለመግባባትን መተኪያ የሌለውን የሰው ህወት ገብሮ በኃይል ለመፍታት ከመሄድ በሁለቱም ወገን ለሰላም ከበቂ በላይ ዋጋ ቢከፍሉ ይሻል ነበር ።
በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ በጦርነት አሸናፊነት ዘላቂ ሰላም ማምጣት የተቻለው በጥቂት ምክንያታዊ አጋጣሚዎች ብቻ ነው።
አብዛኛዎቹ እንደኛ ሃገር ሰፊ የማያቋርጥ ደም አፋሳሽ ፍዳን ያስተናገዱ ናቸው።
የኛ ዘመን ጉልበተኞች ካለፉ ክፉዎች መማር ተስኗቸዋል።
በፍፁም ውጊያቸውን የሚደግፍ ካልሆነ በስተቀር ሁለቱም ሌላ የሰላም መፍትሔን አያዳምጡም እንዳውም ከሚጠሉት ጎራ ጋር ደምረው ይጠሉሃል ።
ለማንኛውም ለነሱ ፈጣሪ የሰላም ልቦና ይስጣቸው ።
ወደ መነሻዬ ልመለስና የአገው ህዝብ በዚህ እንደ ኳስ ጫወታ በዙር የጦርነት ግጥሚያ በሚሸናነፉበትና ለሰው ህይወት ደንታ በሌላቸው ጉልበተኞች ዘመን የራሱን ቦታ ለይቶ ማወቅ አለበት።
እንደ ጥንታዊያን አገዎች ወላጆቻችን ጥበበኞች እንሁን ። የሰላም አመንጭዎች ግጭት አድራቂዎች መሆን አለብን ።
አሸናፊና ተሸናፊ በሌለው የወንድማማቾች ጦርነት
አገዎች ተሸናፊ ታሪክ እንዳንሰራ አደራ እላለሁ ።
አላምረው ይርዳው
ሐምሌ 7 ቀን 2013 ዓ/ም
አዲስ አበባ

Source:- Alamerw Yirdaw

07/05/2021

የአዊ ብልጽግና የት ገባ???

የአዊ ብልፅግና በአሚኮ የሚድያ ድልድል አገው መጎዳቱን አላየሁም፣አልሰማሁም እያለ ነው።የአሚኮ የቦርድ ሰብሳቢና የክልል 3 ብልፅግና ኃላፊ አቶ አብርሀምን እንኳን መጠየቅ አልቻለም። የውሸት ተወዳጅነት ለማግኘት ግን በየቀኑ በቀጠራቸው ፌስቡከኞች ስለአገው እቆረቆራለሁ ይላል!!!

26/04/2021

ይድረስ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ............................................
አገው አገውነቱን ሲዘረፍ ትኢትዮጵያዊነቱን ሲቀማ ዝም ትለናለህ ብየ አላስብም። አገው በኢትዮጵያ ታሪክ ዘመን ተሻጋሪ ህዝባዊ አስተዋፅኦ እንዳበረከተና ለአገሪቱ መስዋዕትነት እንደከፈለ ማስረዳት ለቀባሪ እንደማዳርዳት ነው። የአገው ህዝብ ከመላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በሰላምና በፍቅር እንዲሁም በመከባበር የኖረ ለወደፊትም የመኖር ከፍተኛ ፍላጎት ያለው ህዝብ ነው።

ይሁንጅ ከሁለት ዓመታት ወዲህ ከላይ የተጠቀሱትን ህዝባዊ እሴቶች በናቁና ቡድናዊ ጥቅሞችን ለማሳካት በሚጥሩ አካላት በእጅጉ እየተፈተነ ይገኛል። የሚያሳዝነው ደግሞ እነዚህ ጥቅመኛ አካላት መነሻቸው ከአገው ህዝብ ጋር ተዛዝነውና ተደጋግፈው ለብዙ ዘመናት ከሚኖሩት ከአማራ ህዝብ መሆኑ ነው- "ጠላት ከሩቅ አይመዳም" እንዲሉ። ከጨዋው የአማራ ህዝብ አብራክ የተፈጠሩ፤ ነገር ግን አማራዊ ስብዕና የማይታይባቸው እነዚህ የጥቅም ቡድኖች በአገው ላይ የሚፈፅሙት በደል ፈርጀ ብዙ ቢሆንም ለጊዜው ባንደኛው ላይ ብቻ እናተኩራለን። መላው የኢትዮጵያ ህዝብም እንዲያውቀው አጥብቀን እንፈልጋለን።

የኢፌዴሪ ህገመንግስት ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ በየትኛውም የአገሪቱ አካባቢ ፅህፈት ቤቱን መክፈትና በኢፌዴሪ ምርጫ ቦርድ አቅጣጫና መመሪያ መሰረት የይመረጡኝ ቅስቀሳ ማድረግ እንደሚችል በግልፅ ይፈቅዳል። ይሁን እንጅ የአገውን ህዝብ ያማከለና ህጋዊነቱ በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የተሰጠው "የአገው ብሔራዊ ሸንጎ (ሸንጎ) በአማራ ክልል ውስጥ በአማራ ብልፅግና ካድሬዎችና በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የተደራጁ ሃይሎች በደል እየደረሰበት ይገኛል። የበለጠ ግልፅ ለማድረግ የሚከተሉትን ጥቂት የበደል ማሳያዎች እንደሚከተለው እናነሳለን።

አንደኛ፦ የአማራ ብልፅግናና የአብን አመራሮች የአገው ህዝብ ብሶት ለወለደው የአገው ብሔራዊ ሸንጎ (ሸንጎ) የተለያዩ የመወንጀያ ስያሜዎችን አውጥተውለታ። "ሸንጎ ከፋፋይ፣ ፀረ አማራ፣ የህውሃት ተላላኪ፣ የኦነግ ተልዕኮ ፈፃሚ፣ ወዘተ በማለት በይፋና በስውር ህጋዊ ስሙን አጠልሽተውታል። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡ ይህ የአማራ አብራክ ውላጅ ፖለቲከኞች አካሄድ በአገሪቱ ህግ መሠረት ወንጀል እንደሆነ አይጠፋህም እንላለን።

ሁለተኛ፦ የአማራ ብልፅግናና የአብን አመራሮች የአገው ብሔራዊ ሸንጎ (ሸንጎ) የአገው ህዝብ በሚገኝበት በአማራ ክልል የሚዲያ ሽፋን እንዳያገኝ በተለያዩ አጋጣሚዎችና ስውር መንገዶች ከልክሏል። ሸንጎ በሌሎች ክልሎች አማራጭ ሚዲያዎችን ለመጠቀም በሞከረበት አጋጣሚ ደግሞ አገውን ከአማራ ለመለየት እንደተወሰደ እርምጃ በመውሰድ በተሳሳተ መልኩ ሲኮንኑ ተስተውሏል። ፍቅር አስቀዳሚው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡ አገው የአገሪቱ ህግ የሰጠውን መብት ተጠቅሞ በኦሮሚያ ወይም በትግራይ (ኢትዮጵያ) ሚዲያ ሃሳቡን ቢገልፅ እንዴት ከአማራ ወንድሙ እንደመሸሽ ይቆጠራል? ሁኔታው በዚህ አላበቃም።
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በ2013 ዓ.ም ለሚወዳደሩት ሁሉም የፖለተካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ የሚያደርጉበት ነፃ የአየር ሰዓት ማመቻቸቱ ይታወቃል። የአገው ብሔራዊ ሸንጎ (ሸንጎ) ግን በአማራ ብልጽግና ካድሬዎችና በውስጡ በተሰገሰጉ የአብን ህዋሳት የአየር ሰዓቱን እንዳይጠቀምበት ተከልክሏል። ይህ ድርጊት በአንድ በኩል የኢትዮጵያን ህግና የአገሪቱን ምርጫ ቦርድ መመሪያ ጥሷል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ለአገው ህዝብ ያለውን ንቅት በግልፅ አሳይቶል።

ሦስተኛ፦ የአማራ ክልል መንግስትና የፀጥታ ዘርፉ የአገው ብሔራዊ ሸንጎ (ሸንጎ) ፅህፈት ቤቶች እንዲዘፉ፣ አመራራሮቹ እንዲዋከቡ፣ እጩዎቹ የግድያ ሙከራ እንዲደረግባቸው በር ከፍቷል። ለአብነት ያህልም በቀን 15/8/2013 ዓ.ም በጃዊ ወረዳ የሚገኘው ጽህፈት ቤቱና አመራሩ በጣም ከባድ ችግር አስተናግዷል። የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ፅህፈት ቤት፡ ጃዊ ቅርንጨፍ ከለሊቱ 5:30 አካባቢ 'አማራ ነን' እያሉ በሚፎክሩ ወንበዴዎች በጥይት ተደብድቦበታል። ባነሩን ጨምሮ ብሩ ቁሳቁሶች ተዘርፎበታል። የፅህፈት ቤቱን ያከራየው ግለሰብም ምጣኔ ሃብታዊና ሰብዓዊ መብቱ ተገፎ መኖሪያ ቤቱ ጦይት ተተኩሶበታል። የህዘብ ተወካዮች ምክርቤት የፓርቲው እጩ አቶ አለነ ጌታሁን መኖሪያ ቤቱ የጥይት ሩምታ ተከፍቶባቸዋል። በተከፈተው ሩምታም ማቀዝቀዣውን ጨምሮ ብዙ የቤት እቃዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። አምላክ ይመስገን! የጠፋ የሰው ህይወት የለም-የአይን እማኞች።
ይሁን እንጅ የፌዴራል መንግስትም ሆነ የአማራ ክልሉመንግስት፣ የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞንም ሆነ የጃዊ ወረዳ አስተዳደር ፅህፈት ቤት ስለአሳዛኝ ክስተቱ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት መግለጫም አልሰጡም።

አገው ተበድሏል። አገው በጎረቤቱ ውንብድና እጅግ አዝኖል። አገው ሰብዓዊና ደሞክራሲያዊ መብቱን ተነፍጓል። አገው ካለወንጀሉ ተዋክቧል። አገው ፍትህ ይሻል። አገው የኢትዮጵያን ህዝብ ድጋፍ ይፈልጋል። አገው ካለኢትዮጵያውያን፣ ኢትዮጵያውያን ካለአገው ሙሉ አይሆኑም። አንዱ የሌላው ድምፅ ይሆን።
ይህ የአገው ህዝብ የብሶት ጥሪ ነው።
ታላቅ ኢትዮጵያዊነት ከደማቅ አገውነት ጋር!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

የአገው ህዝብ ሚያዝያ 18/2013

23/04/2021

ከአብይ በፊት ራስህን ውቀስ፡፡
ምያዝያ 15፣ 2013 ዓ.ም

አብይ አህመድ የዚህ ስርዓት ሌጣ መሪ ቢሆንም፣ እኔ ግን እየሆነ ላለው ክፉ ነገር ሁሉ እርሱን ተወቃሽ የማደርገው በሦስተኛ እና በመጨረሻ ደረጃ ነው፡፡

ከሁሉም አስቀድሞ የሰውዬው ማሽንክ ፍልስፍና ገና ከማለዳው ጀምሮ ንፁሃንን ሲቀጥፍ እየታዬ “የእኔን ዘር አልነካም” በሚል ስንኩል እሳቤ ሰውዬውን በጭብጨባ ለዚህ ያበቃችሁትን በርካታ ግልብ ደጋፊዎች አንደኛ ተጠያቂ አደርጋለሁ፡፡ ያለእናነት ማህበራዊ መሠረትነት እስከ አሁን ያለቁት ዜጎች ቁጥር ቢያንስ ይቀንስ ነበርና፡፡ ያለእናንተ አጋፋሪነት ህዝብ በህዝብ ላይ ልቡ እስኪደማ ድረስ አያዝንም ነበርና፡፡ በሁለተኛ ደረጃ በጠቅላዩ ዙሪያ ያሉ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ በጥቅም የተያዙ ቅቤ አንጓች አርቲስቶች፣ ቅልብ ጋዜጠኞች እና አጠቃላይ ዘረኛ ልሂቃን ከሃገር ይልቅ የግል ጥቅማቸውን አስቀድመዋልና አይነተኛ ተጠያቂዎች ይሆናሉ፡፡

ዶ/ር አብይ አህመድ ከዚህ በኋላ ነው በተጠያቂነት የሚሰፍሩት፡፡ ሰውዬው ካለባቸው የአእምሮ ህመም እና የአስተሳሰብ አለመብሰል በተጨማሪ በባዶ ጭብጨባ እንዲሰክሩ በመደረጋቸው ሦስተኛ ተጠያቂ ብቻ ይሆናሉ፡፡ ለፍርድ ቢቀርቡ እንኳን ፍርድ ቤቱ ነፃ እና ገለልተኛ ከሆነ ቢያንስ የአእምሮ ጤናቸውን እና የብስለት ደረጃቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት በነፃ የሚያሰናብታቸው ይመስለኛል፡፡

ማስገንዘቢያ፡
ያም ሆኖ ግን “ለበጎ ሥራ የረፈደ ጊዜ የለም” ይባላል፡፡ በህወሓት ስም ዜጎች ለአውሬ ሲሰጡ “ግፋ በለው” ሲባል መክረሙ ሊኮነን የሚገባው ቢሆንም፣ አሁን በነፍጠኛ ስም የሚገደሉ ዜጎችን ለመታደግ የሚደረግ ትግል ግን ሙሉ በሙሉ ሊደገፍ ይገባል፡፡ ከነገው የሰቆጣ ከተማ ሰልፎ ጎን የምቆመው በዚህ መርህ ነው፡፡ በዚህ ሰልፍ ላይ እንደተለመደው በሳል፣ ህዝብ አክባሪ እና “ነጥሎ መቺ” ሃሳቦች እንደሚንፀባረቁ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ፡፡

በአጠቃላዩ ግን “ሌላው” ሲጠቃ እያጨበጨቡ “የእኔ” የምንለው አካል ሲጠቃ ብቻ ጠብቆ መቃወም የዘራችን እንጂ የሃገራችን ጠባቂዎች አያደርገንም፡፡ እንባው ለሁሉም ዜጎች ይሁን፡፡ ተቃውሞው በሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ከተማዎችም እንዲቀጥል የምንሻው በዚህ እሳቤ ነው፡፡

አሸናፊ ፈንቴ (አዲስ አበባ)

31/03/2021

#መተከል
update

ዛሬ ማንዱራ ወረዳ ሚኒባስ ላይ በጉሙዝ ታጣቂ በተከፈተው ተኩስ 8 ሰው እዛው ሲሞት 4 ሰው ፓዌ ሆስፒታል መግባታቸው ታውቋል አሁን በደረሰኝ መረጃ 4ቱ ቁስለኛ ሕይወታቸው አልፏል።

ከአጠቃላይ 12 ሟች 6 ቱ የአገው ተወላጆች 3 ቱ ወሎዬ 1 ከንባታ 2 ቱን መለየት አለመቻሉ ታወቃል ።

ትናት ድባጤ ወረዳ በተፈፀመ ግድያ 1 ኦሮሞ 1 አገው መገደላቸው ይታወሳል ።
ይህ እንደሚመጣ ግምቴን ነበር !!!

30/03/2021

የዛሬ መረጃ
========
በዋግ ኽምራ ዞን ፃግብጅ ወረዳ ፃታ ከተማና ወርቃ ዲኑ አካባቢዎች
የአማራ ክልል መንግስት መንግስት ከመጋቢት 8 ጀምሮ የዋግን ሚኒሻ እንጨት አሸክሞ እስከ አፍንጫው የታጠቀን የወያኔ ጦር እንዲወጉ ያደረገበት መንገድ ሆን ብሎ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደፈጸመ ስለሚያስቆጥረው የአገው ብሐራዊ ሸንጎ በአለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንዲከሰስ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ በሙያው የላቀ እውቀት ካላቸው ዓለም አቀፍ የህግ ተቋማት ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል ።
በጻግብጅ ስለተፈጸመው ጭፍጨፋ መረጃ ያላችሁና እራሳችሁም ምስክር ለመሆን ፈቃደኛ የሆናችሁ ሰሞኑን በምናሳውቃችሁ ስልክ ቁጥር እየደወላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ
የሚፈለገው መረጃ
- ስለጦርነቱ የሚያውቁትን ማስመዝገብ
- የተሰው ሚኒሻዎችን ስምና አድራሻ መግለፅ
- ከሚኒሻዎቹ ጋር ጦርነት የተደረጉባቸው ቦታዎቸን ስም
- የመንግስት ባለስልጣናት በወቅቱ ምናሉ እነማን
- ሚኒሻዎቹ ወደ ጦርነቱ እንዲገቡ ያዘዘው ማነው የሚሉና በዚህ ዙሪያ ሌላም የሚያውቁት ነገር ካለ ማስመዝገብ ይቻላል
የአገው ብሔራዊ ሸንጎ የአገው ህዝብ ደም በከንቱ ፈሶ ሲቀር ዝም የማለት ተፈጥሮ የለውም ።
አላምረው ይርዳው
መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓም

20/03/2021

ቀንደኛ የአገው ህዝብ ተለት ትግሬ ወይም ኦሮሞ አይደለም አንድ ነን ሚሉት ፖስተሮች ናችሁ

20/03/2021
13/03/2021

ለመላው የአገው ህዝብ ❗
*
የክልል ባለቤት መሆን የሚያስገኛቸው ገፀ_በረከቶች የትየለሌ ናቸው። ለዛሬ በአጭሩ ጥቂት ነጥቦችን ለመጠቆም እሞክራለሁ።ክልል ሲኖርህ፦
1) ቋንቋህን ወዲያውኑ የስራ ቋንቋ ማድረግ ትችላለህ።ቋንቋህ የስራ ቋንቋ ሆነ ማለት ደግሞ ቋንቋህ በፍጥነት ያድጋል ማለት ነው።ቋንቋህ እያደገ ሄደ ማለት ደግሞ አገውነት እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ ባህልህ፣ታሪክህ፣እሴትህ፣ተጠብቆ ለትውልድ ይተላለፋል የአገውነት identity በጠንካራ መሠረት ላይ ይገነባል ማለት ነው።
*
2) ኢንቨስትመንትን በየትኛውም የአገው ምድር አካባቢዎች የህዝቡን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በሚገነባ መልኩ በጥናት ላይ ተመስርቶ ውሳኔ በመስጠት አገው ምድርን አበባ ለማድረግ የሚሳንህ ጉዳይ አይኖር።በዞን ስትወሰን ትላልቅ የኢንቨስትመንት ውሳኔዎች ተወስነው የሚመጡት ከክልል በመሆኑ ምስለኔው ራሱን በሚጠቅመው መንገድ ወስኖ ስለሚልክልህ የአገው ምድር ባለሃብቶች እየቀጨጩ ሌሎቹ እየፈረጠሙ ይሄዳሉ ማለት ነው።ይህ ሆነ ማለት ደግሞ በኢኮኖሚ የደቀቀ ደካማና አቅመ ቢስ የሆነ የአገው አካባቢ ስለሚኖርህ ማንነትህና የተፈጥሮ ሀብትህ እየተዘረፈ በቀላሉ እየከሰምክ ትሄዳለህ ማለት ነው።
*
3) የራስህ ቴሌቪዥንና ሬድዮ 24 ሰዓት ለመዘወር ያስችልሃል።ይህች ጉዳይ በጣም አስፈላጊና ወሳኝ ሀሳብ ናት። የራስህ ሚዲያ ሲኖርህ በቀላሉ የሶስቱን አገዎች አንድነት በማይናወጥ ገሃዳዊ በሆነና በሚታይ መልኩ ለመገንባት ያስችልሃል።የህዝብን የልማት ችግር፣ የመልካም አስተዳደርና የፍትህ እጦትና ህዝባቸውን የሚበዘብዙ ዘራፊዎችን ለማጋለጥ ሚናው ቀላል አይደለም።የባህል፣የሙዚቃና አጠቃላይ ለሆኑ የአገው ማንነቶች ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
*
4) የአገው ህዝብ አለኝታ የሆነ በጠንካራ ዲስፕሊን ላይ ህገ_መንግስቱን መሠረት ያደረገ ልዩ ኃይል ለመገንባት ያስችልሃል።ልዩ ኃይል አለህ ማለት ማንም እየተነሳ ህዝብህን ከለም መሬቶቹና ከእርስቱ እየገደለ አያፈናቅልብህም ህዝብህን አስተባብረህ በማስታጠቅ እየተከላከለ በለም መሬቶቹና ርስቶቹ ተረጋግቶ ሰርቶና ሀብት አፍርቶ እንዲኖር ለማድረግ ያስችልሃል።የታጠቀ ህዝብ ህልውናውን መጠበቅ ይችላል ማንም እየመጣ አይፈነጭበትም በሚገባው ቋንቋ ታናግረዋለህና።
*
5) የአገው ህዝቦች እንደፈለጉ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት፣ትብብርና ውይይት በፈለጉት ጊዜ ለማድረግ ምንም አይገድባቸውም። ምክንያቱም ባለቤቱ አንተ ነህና ይሸኝዲን በጭልጋ፣ሻደይን በሰቆጣ፣የአገው ፈረሰኞችን በዓል በእንጅባራ ሰብሰብ ብለህ በቀጥታ በራስህ ቴሌቪዥን እያስተላለፍክ በደማቁ ታከብራለህ።
*
6) ለአገው ባለሃብቶች ለም መሬቶቹን ፍትሃዊነትን መርህ በአደረገ መልኩ በነፃነት እንዲያለሙ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ትችላለህ የአገው ወጣቶም በኢንቨስትመንቱ እንዲጠቀሙ ለማድረግ ትችላለህ።
*
7) በአገው አጎራባች ክልል ከሚዋሰኑ ህዝቦች ጠንካራ ወንድማማችነትን በመፍጠር የአገው ህዝብ ከዚህ በፊት ካለው የአብሮ የመኖር ዕሴት የጎለበተ ልምድና ተሞክሮ በመጠቀም ግጭቶች ከመፈጠራቸው በፊት አዋሳኞችህን የሰላም ቀጠና ለማድረግ ያስችልሃል።ለዚህ ደግሞ አገው ችግር የለበትም ከማንም ጋር በቀላሉ መግባባት ይችላል።
*
8) የመሠረት ድንጋያቸው ተቀምጠው ያላለቁ የግንባታ ፕሮጀክቶችን ቀን ከሌት በመከታተል ለማጠናቀቅ ዕድልህ ሰፊ ነው።ምክንያቱም የአንተን ጉዳይ በወኪል ከመከታተል ይልቅ ባለቤቱ እራስህ ተከታትለህ እንዲጠናቀቁ የአንበሳውን ድርሻ ለመወጣት ሁኔታዎች ምቹ ናቸው።ለምሳሌ የዋግኽምራ ህዝብ የባህል ማዕከል ግንባታ ማስጀመሪያ የመሠረት ድንጋይ ይኸው 13 ዓመቱ ተጎልቶ ቀርቷል፣የአዊም እየአዊም እንደዛው በጥቂቱ ነው።እነዚህን በመከታተል እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ያስችልሃል።
*
9) በሶስቱም ዞኖች የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ፣ሆስፒታሎች፣ዮንቨርስቲዎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲገነቡ ከፌደራል መንግስት ጋር ትደራደራለህ።በጀትህን ቀጥታ ከፌደራል መንግስት ተቀብለህ ልማትህንና ታለማለህ ማህበረሰብህን በዘመናዊ እርሻና ከብት እርባታ ዕውቀት በማስጨበጥ ዘመናዊ እርሻና ከብት እርባታን እንዲተገብር ማድረግ ትችላለህ።
*
10) የተፈጥሮ መዳረሻዎችን ለማልማት Resorts ፣መናፈሻዎች፣ማራኪ ገፅታዎችን ለጥቅም ማዋል ይቻላል።ለዚህ ደግሞ አገው ምድር የተመቸ ነው ይህንን በዘንገና፣አሸንጌ፣ፅርባ፣ዶንዶር፣ጋርቹ፣ትስኪና በርካታ ያልጠቀስኳቸውን መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ እንዲለሙና የስራ ዕድል እንዲፈጠር ማድረግ ያስችላል።
*
ለዛሬ አንኳር ያልኳቸውን በጥቂቱ አካፈልኳችሁ።ታዲያ የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መመስረት እነዚህን ሁሉ ትሩፋቶች የሚያስገኝልን ከሆነ ምን እንጠብቃለን?
*
ስለዚህ የአገው ብሔራዊ ሸንጎ የአገው ህዝብ ያለምንም መሸራረፍ ህገመንግስታዊ መብቱን እስኪጎናፀፍ ያለ እረፍት የሚሰራ ድርጅት በመሆኑ በቀጣይ ምርጫ ድምፃችንን ለሸንጎ በመስጠት የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትን ለመመስረት እንዘጋጅ ❗❗❗
ታላቁ አገው ይነሳል ❗
*

*
የአዊ ዞን አገው ብሔራዊ ሸንጎ የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ ከአገው ምድር።
02/07/13 ዓ.ም

15/02/2021

ለኤርትራ ለትግራይና ለአማራ ህዝብ መሰረቱ አገው ነዉ ። አገው በኤርትራ ብሌን ፣በትግራይ ተምቤን ፣በጎንደር ቅማንት፣በወሎ ዋግ፣በጎጃም አዊ አለ ይላሉ ፀሐፊ ተውኔትና ገጣሚ አያልነህ ሙላቱ !!!

ምርጫችን ሞባይል ነው!!!
28/01/2021

ምርጫችን ሞባይል ነው!!!

የኢትዮጵያ ንጉሥ እንደሚሆኑ በእናታቸው ትንቢት  የተነገራቸው ጠቅላይ ሚንስቴር አቢይ አህመድ ኢትዮጵያ ማዳን  አልቻሉም።" ሊቀ ሊቃውንት አባ ወልደ ትንሣኤ  አባተ"    (አሻራ ጥር፣15፣2...
23/01/2021

የኢትዮጵያ ንጉሥ እንደሚሆኑ በእናታቸው ትንቢት የተነገራቸው ጠቅላይ ሚንስቴር አቢይ አህመድ ኢትዮጵያ ማዳን አልቻሉም።" ሊቀ ሊቃውንት አባ ወልደ ትንሣኤ አባተ"
(አሻራ ጥር፣15፣2013 ዓ•ም ባህርዳር)

ኢትዮጵያ በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን አሁን ወደ አለችበት ምስቅልቅል ትገባለች ብሎ ያሰበ አለ ብየ አላምንም።

ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካሉ ታልልቅ ሀገሮች
መካከል አንዷ የታሪክ የቅርስ የስልጣኔ የጠቢባን እና የጥበብ ሀገር የነገስታት ምድር ነበረች።
ኢትዮጵያ ዓለም በባርነት በቀኝ ግዛት ስር ወድቆ ነፃነቱ ተገፎ አንገቱን ደፍቶ በሄደበት በዚያን ዘመን ኢትዮጵያ ማንም ሳይደፍራት ታፍራ ተከብራ የኖረች የኩሩ የጀግናና የአርበኞች ሀገር ነበረች።

ሆሜር የሚባል አንድ ጀርመናዊ ምሁር ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያኑን ሲገልፃቸው
ከክርስቶስ ልደት ስድስት መቶ ዓመት በፊት
ኢትዮጵያውያን ደጎች ርህሩሆች እንግዳ ተቀባዮች ጠይምና መልከ መልካም ሰዎች የሚኖሩባት የጀግኖች ሀገር ነች ብሏታል።

አውሮፓውያን አቢሲንያ ይሏታል ።አረቦች ሐበሻ ይሉናል እኛ ግን ኢትዮጵያውያን ነን ሀገራችንም ኢትዮጵያ ናት እንላለን።ኢትዮጵያ በጣም ጀግኖች ሀገር ወዳድ መሪዎች የነበሯት ሀገር ነበረች።
በአኩሱም ዘመነ መንግስት አብርሃና አፅብሃ
እንድሁም አፄ ካሌብን የመሳሰሉ ነገስታት ነበሯት።
ወደ ሮሐ ስንመጣ ይምርሃነ ክርስቶስ ከባህር ላይ መቅደስ የገነባላት ጀግና እንደ ቅዱስ ላሊበላ ያለ ፃድቅ ንጉስ አለት ፈልፍሎ በድንጊያይ ላይ ታሪክ የፃፈላት ነበረች።

አፄ ዘራያ ያዕቆብን አባቱን አፄ ዳዊትን ስንመለከት በሀገር ፍቅር የተቃጠሉላት ኢትዮጵያውያን መሪዎች ነበሯት።የበጌምድርን ቤተ መንግስት ስንመለከት እንደ አፄ ፋሲል ያለ ገናና መሪ እንደ ፃድቁ ዮሐንስ ለሰው ልጅ ቀርቶ የእንስሳ መብት እንድከበር አዋጅ ያስነገረ እንደ መናኔ መንግስት ተክለ ሃይማኖት ያለ ዓለም በቃኝ ብሎ የመነነ መሪ ነበራት።

ኢትዮጵያ አሁን ባሉት አገር ወዳድ ሳይሆኑ ራስ ወዳድ መሪዎች እጅ ትገባለች ብሎ ያሰበ አልነበረም ሀገራችን በደም ባጥንት የተገነባች አባቶቻችን ራሳቸውን ክደው የሞቱላት ዋጋ የተከፈለባት የአፄ ቴዎድሮስና የአፄ ዮሐንስ የደም ምድር ነች የዛሬዎቹ ፖለቲከኞች ይህን ስንነግራቸው ሊረዱን አልቻሉም ኢትዮጵያን በራሳቸው ወርድና ቁመት ለክተው እንደ ቅርጫ ስጋ እየተከፋፈሏት ይገኛሉ።

የጉድ ሀገር  ዜና ፡፡ፈጣሪ   ምነው ለፍርድ  ዘገያህ? ሰርቶ አደሪ አገው ምን  በደለ? አገው በደይ  ከሆነ   አንተ ፍረድ፡፡  አገው አንተ  የበረክሀትን መሬት አርሶ  በይ እንጂ ፡፡ይህ...
17/01/2021

የጉድ ሀገር ዜና ፡፡ፈጣሪ ምነው ለፍርድ ዘገያህ? ሰርቶ አደሪ አገው ምን በደለ? አገው በደይ ከሆነ አንተ ፍረድ፡፡ አገው አንተ የበረክሀትን መሬት አርሶ በይ እንጂ ፡፡ይህ ነው የአገው ብልፅግና? ለካ ሬሳ ብሄር የለውም የተበለው ለካ ቁመር መሆኑ ነው ፡፡የኛ ብልፅግና በጨለማ ዘመን ለአገው ልብሰ የነበረውን ""አግዴፓ"" ንአባርራህ ሉዓላዊት ሀገር ላይ የአገው ሬሳ በጅምላ ተጨፍጭፈው በጅምላ ሲቀበር እናሆ ✍ሰብዓዊ መብት ተሞገጭ ፣ የሰፈር ህዝብ ተወካዮች ፣የፈጣሪን ቃል እናስተምረለን የሚለው እምነቶች ፡ይህን ሬሳ አለየችሁም? ምነልባት ይህ የተፈፀመበትን ቦታ ማተወቁ ከሆነ ልነግራቹህ ✍ሀገሪቷ ኢትዮጵያ ትባለለች ልዩ ሰፍረው መተከል ፡፡ሁላችሁም መተከል ብትሆኑ ኑሮ እንደዚህ በጅምላ እንደምትቀበሩ ምንም ጥርጥር የለኝም ፡፡ አልቻልንም ማለትም አንድ ውለታ ነው፡ ፡ አጨብጫቢዎች ሰብዓዊነት ይሰማችሁ ፡፡ ለብቻው የተቋቋመው አገው ጨፍጫፊ ፓርቲ (ከኦሮሚያ ፣ከአማራም ፡ከጉምዝም......ወዘተ ተውጣጥተው የተቋቋመ ስራው ከጀመረ በፍጥነት ወደ ፍፃሜ እየገሰገሰ ይገኘል፡፡ ቀልብ የገዛ ወጣት አለመኖር ፡ በሱስ የተጠመደ የአገው ወጣት ከሰመመን ንቃ እስኪ ፡፡ሚዲያ የሌለው ብቻኛው ህዝብ ፡ ልዩ ተጎጂ ህዝብ፡ ሰብዓዊ ና ዲሞክረሲያው መብት የማይከበርለት ህዝባ አገው ፡፡አነገም ወይ?

እባካችሁ የአማራ ፖለቲከኞች የእውነት በኩልነት እንኑር ==================የአማራ ፖለቲከኞች እና አክቲቪስቶች በአፋችሁ አገውና አማራ አንድነው እያላችሁ በተግባር አገውን መናቅ ማጥ...
31/12/2020

እባካችሁ የአማራ ፖለቲከኞች
የእውነት በኩልነት እንኑር
==================
የአማራ ፖለቲከኞች እና አክቲቪስቶች በአፋችሁ አገውና አማራ አንድነው እያላችሁ በተግባር አገውን መናቅ ማጥቃት ስሙ እንዳይነሳ ክብር እንዳይኖረው የመብት የኩልነት ጥያቄ ሲያነሳ ተባብራችሁ ማውገዝ ተው
በእውነት እንከባበር ያለዚያ የውሸት መኖር በቃን
ከምንም በላይ ደግሞ እውነተኛ አንድነት እንዲመጣ ከፈለጋችሁ በውሸት ለማደናገር ከምትረባረቡብን ምንድነው ችግራችሁ ብላችሁ አድምጡን የሰከነ ዘመናዊ የመከባበር ፖለቲካ ማካሄድ ለክልላችን ዘላቂ ሰላም አማራጭ የለውም ።
ከዚህ አንጻር እኩል የሚያደርገው ማጥቃትን ማቆም ፣ ቂምን መርሳት ወዳጅነትን ማብዛት ጉዳቱን መረዳት ነው አሁን ግን ሁኔታዎች በተቃራኒው እሄዱ ነው ለምሳሌ የቅማንት አገው ከጉዳቱ ከጥቃቱ እንዲያገግም ያለፈውን እንዲረሳ ከመጣር ይልቅ ቁስሉ እንዲያመረቅዝ እየተሰራ ነው ለዚህም ተጨባጭ ምልክቶቹ
1- ከህወሓት መልስ ወደ ቅማንት በሚል ሰፊ ቅስቀሳ ሲደረግ መንግስትና ፖለቲከኞቹ በደስታ እያዩት መሆኑ
2- የቅማንትን ትግል መሪዎችና አንቂዎችን ህዝቡ እንደ ዓይኑ ብሌን የሚያያቸውን እንደ ቄስ ይርጋ ተሻገር የመሰሉትን ያለምንም ጥፋት ያለ ክስ አስሮ ማሰቃየት
3- በሰላም ሚኒስቴር አደራዳሪነት በክልሉና በኮሚቴው መካከል የተፈረመውን ውል ለመተግበር መንግስት እያሳየ ያለው ዳተኝነት (ፍላጎት ማጣት) የሚያቀራርቡ አካሄዶች ሳይሆኑ ለሌላ ዙር መራራቅ በር ከፋችና መዘዛቸው የበዛ ነው
የኛ ፍላጎትና ትግል አገውና አማራ መካከል የማስመሰል አፋዊ አንድነት ሳይሆን እውነተኛ መሰረት ያለው በመከባበር ላይ የተገነባ ዘመንና እኩይ ምክኒያት የማይሽረው በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ወዳጅነት እንዲፈጠር ነው
አሁንም የአማራ ፖለቲከኞች ፣አክቲቪስቶችና የሕዝብ አንቂዎች የአብሮነት እውነተኛ ፍላጎት ካላቸው ዛሬም ሌላ የዘላቂ ሰላም ቀን ለመፍጠር አልረፈደም ።
አላምረው ይርዳው

የኢትዮዽያ ታሪክ እና የስነ ቋንቋዎች ጥናት!አማርኛ  የእኔ የግሌ ነው የሚለው ማህበረሰብ አለ ወይ?የአማርኛ ዕድሜ ስንት ነው? የእኔ ብቻ ነው እኔ ነኝ ባለቤቱ ካለስ ይህ ማህበረሰብ  ከገነ...
31/12/2020

የኢትዮዽያ ታሪክ እና የስነ ቋንቋዎች ጥናት!

አማርኛ የእኔ የግሌ ነው የሚለው ማህበረሰብ አለ ወይ?
የአማርኛ ዕድሜ ስንት ነው? የእኔ ብቻ ነው እኔ ነኝ ባለቤቱ ካለስ ይህ ማህበረሰብ ከገነት ወደ ምድር የተወረወረው ከ10ኛ ክ/ዘን በኃላ ነው🤣🤣

No way!

Amhara identity came after Amharic language.But Amharic was created as secretary and code communication in the palace and among military during Zagwe Dynasty( Agaw/Agow/Agew).

We have a number of references. Visit Libraries and Museums of European , and North America about history of ancient Abyssinia, in case you don’t find good source this in Ethiopia.

History is History, you can’t change it by fabricated narration.

is a fabricated narrator!

በድንቁርና ዲግሪ ሲኖርህ እንዲህ ማሰብ ይቻላል!!«አማርኛ ሲል እንኳን አማራ-ኛ እያለ ቋንቋው ራሱ አማራ መሆኑን እያገለፃ...»ይህ እንግዲህ አማርኛ የአማራ መሆኑን ለማስረዳት ያቀረበው ማስ...
31/12/2020

በድንቁርና ዲግሪ ሲኖርህ እንዲህ ማሰብ ይቻላል!!
«አማርኛ ሲል እንኳን አማራ-ኛ እያለ ቋንቋው ራሱ አማራ መሆኑን እያገለፃ...»
ይህ እንግዲህ አማርኛ የአማራ መሆኑን ለማስረዳት ያቀረበው ማስረጃ መሆኑ ነው።
ወይ ልጅ ተድላ ክምር እፈር!!!!
አማርኛን አገው ፈጠረው ከዛም በብዙ ብሄር ብሄረሰቦች ጥረት አደገ!!!
ቢመርህም ይህንን ሀቅ ዋጠው😎

የአገው ህዝብ ዝምታ ለወዳጅነት እንጅ ለውርደት አልነበረም=================በጉልበት  አገው የፈጠረውን ቋንቋ ማንነቴ ነው ብለው ሙጥኝ ያሉ የ30 ዓመት ጨቅላ ባለታሪኮች አገው አንገ...
29/12/2020

የአገው ህዝብ ዝምታ ለወዳጅነት
እንጅ ለውርደት አልነበረም
=================
በጉልበት አገው የፈጠረውን ቋንቋ ማንነቴ ነው ብለው ሙጥኝ ያሉ የ30 ዓመት ጨቅላ ባለታሪኮች አገው አንገቱን መድፋቱን እንደ ጥሩ አጋጣሚ ተጠቅመው አገውን አናሳ፣ንዑሳን ይላሉ
በመሠረቱ የአንድን ፍጡር እድሜ ለማወቅ ከሱ ቀድሞ የተፈጠረ ወሬ ነጋሪ ያስፈልጋል አገው በሰዋዊ አቆጣጠር የተፈጠረበትን ዘመን ለማወቅ ከፈጣሪ በስተቀር የሰው ማስረጃ የለም የሰው ዘሮች ሁሉ ተፈጥረው አዕምሯቸው የአካባቢያቸውን ፍጥረታት ሲለዩ አገው ሃገር እያቀና ነው ያገኙት አገው በፍላጎታቸው ወይም በሂደት በሁኔታ አስገዳጅነት የተለወጠ ማንነት አለመሆኑ በብዙ ድርሳናት ምስክርነት የተረጋገጠ ነው
እነ ጉራ በኪሱ ግን ማንም የ30 ዓመት እድሜ ያለው ሁሉ የማንነታቸውን የትውልድ ዘመን ከነፈጣሪያቸው በለዕራዩ መሪ ጠንቅቆ ያውቃል
እውነት እናወውራ ከተባለ አገውን አሳንሶ ለመጥራት እንኳን እነሱ የትላንት ባለ ጅምር ማንነቶቹ ነባሮቹ ህዝቦችም ሞራሉም እውነቱም የላቸውም ለዚህም ነው እንከባበር ጠበንጃና ስልጣን መያዝ ጉልበተኛ እንጅ የገናና ታሪክ ባለቤት አያደርግም አገውን ዝም አድርጎ በታሪኩ መኮፈስ ባለታሪክ አያደርግም
ይልቅ አሁንም እንምከራችሁ ማንም ታሪክ የሰራው ሀ ብሎ ጀምሮ ነው እናንተም የተፈጠረላችሁን አዲስ ማንነት ከወደዳችሁት ታሪክ ስሩበት ታዲያ እንደጀመራችሁት የመገዳደል ያም የኔ ይሄም የኔ የሚል የመጠፋፋት ሳይሆን እንደኛ ወላጆች ጥንታዊያን አገዎች ለሰው ልጅ የሚጠቅም ሃገርን የሚያኮራ ታሪክ ነው መስራት የእስካሀኑ የስህተት ታሪክ ነው ይብቃ በሉ ልብ ይስጣችሁ።

አላምረው ይርዳው
ታህሳስ 20 ቀን 2013 ዓም
አዲስ አበባ

ወንድምን መግደል መከበሪያ አጥርህን መንቀል ነው የአማራ ወፈፌዎች የመተማን በር ጠባቂዎች እንደዋዛ ነቅለው ጥለው ዛሬ እየየው ይላሉ ኢትዮጵያን  አሰደፈሯት። የሃገሩ ደጀን የቅማንት ጀግና አ...
21/12/2020

ወንድምን መግደል መከበሪያ አጥርህን መንቀል ነው የአማራ ወፈፌዎች የመተማን በር ጠባቂዎች እንደዋዛ ነቅለው ጥለው ዛሬ እየየው ይላሉ ኢትዮጵያን አሰደፈሯት። የሃገሩ ደጀን የቅማንት ጀግና አይገኝምና
እንግዲህ ሞክረው ወፈፌው ግባና
==================================
@መንጋቱ አይቀርም ጎንደር" በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም "
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ከትናንት ዛሬ የቅማንት ጀግኖች ሙተው መተማ በጠላት ተወረረች ።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
እነ ጠገነ የሉም-በሞት ተለይተዋል ፣
እነ አታላይ የሉም-በሞት ተለይተዋል ፣
እነ ጋሹ የሉም- በሞት ተለይተዋል ፣
እነ ይስማው የሉም-በሞት ተለይተዋል ፣
የቅማንት ጀግኖች- በጨካኝ ሞተዋል ፣
ተብሎ ተነግሯቸው-ሱዳኖች ሰምተዋል፣
ታሪኳን ከተማ - መተማን ወስደዋል ፣
የጠገነን መሬት - ደለሎን ወርሰዋል ፣
ከልካይ ስለለለ - ኢትዩጵያን ወረዋል ።

" በሉ እስኪ ቻሉት "
~~~~~~~~~~~~
ጀግኖችን አጥታ-መተማ ተወረረች ፣
ቅማንቶችን አጥታ-መተማ ጠፍታለች ፣
ቅማንቶችን ገላ - በሯን ከፋፍታለች ፣
ገናነው ገናነው - ብዙ ታለቅሳለች ፣
በቅማንቶች ላይ- ግፉን ፈፅማለች ።

የደንበሩን አጥር-ቅማንቱን ነክታቹህ ፣
የኢትዩጵያን መከታ-ቅማንቱን ገላቹህ ፣
በሩን ከፋፍታቹህ - ሱዳን ወረራቹህ ፣
በሉ እንግድህ ቻሉት-የት አሉ ጉራቹህ ?
በሉ እንግድህ ቻሉት-የት አለ ጉራቹህ ?።

~ ድል ለብሔር ብሔረሰቦች
~ ነፃነት ለሰፊው የቅማንት የህዝብ
~ ዘላለማዊ ክብር ለሰማዕቶቻችን
~ ውድቀት ለጨፍላቂውና ለተስፋፊው አምባገነን መንግስት
~ ለሟቾች ነብስ ሃራ ገነትን ያወርስልን ዘንድ የፈጣሪ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን ።

የ15ኛው የብሔር ብሄረሰቦች በዓል በአዊ ብሔረሰበ አስተዳደር መከበር ተጀመረ፡፡15ኛው የብሔር ብሄረሰቦች በዓል ቀን እኩልነት ህብረ-ብሔራዊነት በጋራ ብልፅግና በሚልመሪቃል 03/03/2013 ...
14/11/2020

የ15ኛው የብሔር ብሄረሰቦች በዓል በአዊ ብሔረሰበ አስተዳደር መከበር ተጀመረ፡፡
15ኛው የብሔር ብሄረሰቦች በዓል ቀን እኩልነት ህብረ-ብሔራዊነት በጋራ ብልፅግና በሚልመሪቃል 03/03/2013 ዓ/ም በአዊ ብሔ/ም/ቤትና በባህልና ቱሪዝም መምሪያ አማካኝነት የአዊ የመስህብ ሀብት በሆነው በዘንገና ሀይቅ ከዋልታ ሚዲያ ጋር በመተባበር የብሔ/አስተዳደሩን ባህል ወግና እሴቶችን በሚያንፀባርቁ አለባበሶች፣ ምግቦች፣ መጠጦችና ጭፈራዎች በአማረና በደመቀ መልኩ ተከብሯል፡፡
የብሔ/ም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አቡኔ ዓለም የበዓሉን አከባበር አስመልክተው እንደተናገሩት ይህ በዓል ስናከብር ከብሔ/አስተዳደር እስከ ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች አሁን ላይ ያለውን የህወህት ፅንፈኛ ቡድን የፀጥታ መደፍረስ ለመመከት ሁላችን በያለንበት የድርሻችንን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡ አያይዘውም በዓሉን ዛሬ የጀመርነው ስለሆነ በብሔረሰብ ዞኑና በወረዳና ከተማአስተዳደሮችም በደም ልገሳ፣ ቦንድ በመግዛት፣ የአረጋዊያን ቤት በመጠገንና የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ በቀጣይጊ ዚያት የሚከበር መሆኑን እሳስበዋል፡፡

Address


Telephone

0913631013

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agew Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Agew Media Network:

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share