Ethiopia Rising

Ethiopia Rising ጥላቻ፣ ዘውገኝነት፣ ቂ እና ጽንፈኝነት በፍቅር፣ ይቅርታ እና
(1)

አዲስ ሰልጣኝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በዛሬው ዕለት በብር ሸለቆ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ስልጠና መጀመራቸውን ከሠራዊቱ ገፅ ተመልክተናል። ይህ ወታደራዊ ስልጠና 40ኛ ዙር ነው ተ...
06/10/2024

አዲስ ሰልጣኝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በዛሬው ዕለት በብር ሸለቆ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ስልጠና መጀመራቸውን ከሠራዊቱ ገፅ ተመልክተናል። ይህ ወታደራዊ ስልጠና 40ኛ ዙር ነው ተብሏል።

ይሄ ፖስት የቁርጥ ቀን ወዳጆችን እንደሚያስከፋ አልጠራጠርም😅🥩 🥩🥩🥩🥩ይሄ ፎቶው ላይ ግስጥ ብሎ የሚታየው ሸበላ የኮሶ ትል ነው። ጥሬ ስጋ መብላት ከሚያስከትላቸው መዘዞች ሁላችንም በስፋት የ...
06/09/2024

ይሄ ፖስት የቁርጥ ቀን ወዳጆችን እንደሚያስከፋ አልጠራጠርም😅
🥩 🥩🥩🥩🥩
ይሄ ፎቶው ላይ ግስጥ ብሎ የሚታየው ሸበላ የኮሶ ትል ነው። ጥሬ ስጋ መብላት ከሚያስከትላቸው መዘዞች ሁላችንም በስፋት የሰማነው ስለኮሶ ነው። ነገር ግን ያልበሰለ ስጋ መብላት ከኮሶ ባሻገር ሌሎች መዘዞች አሉት::
🥩🥩🥩🥩
በቅድሚያ ግን ለመሆኑ አንዳንድ የቲክታክ ወትዋቾች እንደሚደሰኩሩት ጥሬ ስጋ መብላት ለጤና ጥቅም አለው ወይ? ጥሬ ሙዳ ስጋ ጋር በሚደረገው ትንቅንቅ ከሚፈረጥመው የመንጋጋ ጡንቻ ባሻገር ጥሬ ስጋ ከበሰለ ስጋ የተሻለ አንዳችም ጠቀሜታ የለውም🤪 እንዲያውም በተቃራኒው የበሰለ ምግብ በቀላሉ ስለሚፈጭ አንጀታችን ንጥረነገሮችን በቀላሉ ለማግኘት ይመቸዋል።
🥩🥩🥩🥩
ጥሬ ስጋ ከኮሶ ባሻገር ሌሎች በርካታ ኢንፌክሽኖችን ሊያስከትል ይችላል። በተለይ ለተለመዱት አንቲባዮቲክ የማይበገሩ አደገኛ ባክቴሪያዎች የሚያመጡት የምግብ መመረዝ ከኮሶ የበለጠ አሳሳቢ ሆኗል።
ህፃናት፣ ነፍሰጡሮችና የመከላከል ሀይላቸው የተዳከመ ህሙማን ጥሬ ስጋ ቀርቶ የተነካካ ምግብ እንዳይበሉ ይመከራል። የእነዚህ ባክቴሪያዎች የብከላ አቅም በጣም ሀይለኛ ከመሆኑ የተነሳ እንኳን ጥሬ ስጋውን ራሱን እሱ የነካውን ምግብ መብላት በራሱ መመረዝ ሊያስከትል ይችላል።
👉እንደመፍትሄ - ጥሬ ስጋ ባለበት ምግቦችን ስንገዛ ስናዘጋጅና ስናቀርብ ሌላኛው ተመጋቢ “ፆመኛ” እንደሆነ ማሰብ ነው። የ”ፆመኛው" ምግብ እንዳይነካ የምናደርገውን ጥንቃቄ እዚህ ላይ መተግበር። ለምሳሌ ጥሬ ስጋ ስንገዛ ለብቻው በፌስታል ማሸግ፤ ጥሬ ስጋ የከተፍንበት ቢላና መክተፊያ ማጠብ፣ ጥሬ ስጋና ሌሎች ጥሬያቸውን የሚበሉ ነገሮችን(ለምሳሌ ሰላጣ) አለማነካካት፣ ለይቶ ማቅረብ…you get the point
🥩🥩🥩🥩🥩
በነገራችን ላይ የምግብ መመረዝን እንደቀልድ ባናየው መልካም ነው። በአለም ዙሪያ በየአመቱ ግማሽ ሚሊየን የሚጠጉ ሞቶችን የሚያስከትል ከባድ የጤና ችግር ነው። ከዚህ ቁጥር ውስጥ ከጥሬ ስጋ ጋር የተያያዘው ምን ያክሉ እንደሆነ መረጃ የለኝም። you get the point…
🥩🥩🥩🥩🥩
“ጥንታዊው ሰው ጥሬ ስጋ ስለሚበላ ጤናማ ነበር” ይልሃል የቲክታክ ኃሳዊ ተመራማሪ (pseudopaleontologist)። ጥንታዊው ሰው አማካይ እድሜው ከሰላሳ ሳይዘል እንደሚሞት ልብ ሳይል። እውነተኞቹ ተመራማሪዎች እንደሚሉት ጥንታዊው ሰው እሳትን አግኝቶ ምግቡን ማብሰል ሲጀምር ነው አንጎሉ መጎልበት ሲጀምር ነው ከዋሻ ወጥቶ አለምን በቁጥጥሩ ስር ያዋለው።

Abiy Meaza

ሰላማዊ ሰልፍ በማስተባበራቸው በአዋሽ አርባ ታስረው ከቆዩ እስረኞች የተወሰኑት ወደ አዲስ አበባ ተዘዋወሩባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ በአዲስ አበባ ከተማ ሊካሄድ የነበረን ሰላማዊ ሰልፍ ሲያስተ...
06/09/2024

ሰላማዊ ሰልፍ በማስተባበራቸው በአዋሽ አርባ ታስረው ከቆዩ እስረኞች የተወሰኑት ወደ አዲስ አበባ ተዘዋወሩ

ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ በአዲስ አበባ ከተማ ሊካሄድ የነበረን ሰላማዊ ሰልፍ ሲያስተባብሩ ከነበሩ ግለሰቦች መካከል አራቱ፤ ለሁለት ወር ገደማ በእስር ላይ ከቆዩበት ከአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ከትላንት በስቲያ አርብ አመሻሽ ወደ አዲስ አበባ መዘዋወራቸውን ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገለጹ። ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ የነበሩት እና ላለፈው አንድ ሳምንት በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የነበሩት አቶ የሺዋስ አሰፋ በትላንትናው ዕለት ከእስር ተለቅቀዋል።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ሊቀመንበር በነበሩት አቶ የሺዋስ እና በሌሎች ፖለቲከኞች አስተባባሪነት፤ በአዲስ አበባ ከተማ ህዳር 30፤ 2016 ሊካሄድ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ “የእርስ በእርስ ጦርነት ይብቃ፤ ሰላም ይስፈን” የሚል መሪ ቃል ነበረው። ሰላማዊ ሰልፉ ካነገባቸው ሶስት ዓላማዎች መካከል፤ የመከላከያ ሰራዊት “የአገር ሉዓላዊነትን ከማስጠበቅ ሚናው ውጪ” በኦሮሚያ እና አማራ ክልል ከሚሳተፍባቸው “ደም አፋሳሽ ተግባሮች” ተቆጥቦ፤ “ወደ ጦር ሰፈር እንዲመለስ” መጠየቅ የሚለው አንዱ ነበር።

ከሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ቀርተው የነበሩ አራት እስረኞች፤ ከትላንት በስቲያ አርብ ግንቦት 30፤ 2016 አመሻሹን ወደ አዲስ አበባ እንዲዘዋወሩ መደረጋቸውን ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት ቅጽር ግቢ ወደሚገኘው የእስረኞች መቆያ የተዘዋወሩት የሰልፉ አስተባባሪዎች፤ የኢህአፓ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ዝናቡ አበራ፣ ጠበቃ አበራ ንጉስ፣ ዮሴፍ ተሻገር እና እዮብ ገብረ ስላሴ መሆናቸውን ምንጮቹ ጨምረው ገልጸዋል።

አራቱን የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪዎች ጨምሮ ባለፈው አርብ ከአዋሽ አርባ ወደ አዲስ አበባ የመጡት እስረኞች 17 መሆናቸውን ምንጮች ጠቁመዋል። የእስረኞቹ ቤተሰቦች ትላንት ቅዳሜ ጠዋት በተለምዶ “ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ” ወደሚባለው የእስረኞች ማቆያ በሄዱበት ወቅት፤ በስፍራው የነበሩት ፖሊሶች ያመጡትን ምግብ እና ልብስ እንደተቀበሏቸው አስረድተዋል። ሆኖም ቤተሰቦች እስረኞቹን ለማነጋገር ሲጠይቁ “እንደማይቻል” እንደተነገራቸው አክለዋል።

🔴 ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2024/13273/

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ የብር መግዛትን አቅም ካዳከመች የዋጋ ንረቱ እንደሚባባስ አስጠነቀቀ የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅም ከተዳከመ የዋጋ ንረት እንደሚባባ...
06/09/2024

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያ የብር መግዛትን አቅም ካዳከመች የዋጋ ንረቱ እንደሚባባስ አስጠነቀቀ

የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅም ከተዳከመ የዋጋ ንረት እንደሚባባስና የነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋ እንደሚጨምር ማስጠንቀቁን ከአንድ የድርጅቱ ሰነድ ላይ መመልከቱን ሪፖርተር ዘግቧል።

መንግሥት የውጭ ኩባንያዎች በአስመጭነትና ላኪነት እና በችርቻሮና ጅምላ ንግድ እንዲሳተፉ የፈቀደው፣ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅትና ከዓለም ባንክ ብድር ለማግኘት ሲል ሊኾን እንደሚችል ሰነዱ ማመልከቱን ዘገባው ጠቅሷል።

ኹለቱ ተቋማት የብር የመግዛት አቅም እንዲዳከም እንደሚፈልጉና የእስካኹኑን የዋጋ ንረት ከአለመረጋጋትና ከዓለማቀፍ የሸቀጦች ዋጋ መጨመር ጋር እንደሚያያይዙት ሰነዱ ያብራራል ተብሏል።

ብሄራዊ ባንክ፣ በተያዘው በጀት ዓመት ማብቂያ የመደበኛውንና የጥቁር ገበያውን የምንዛሬ ልዩነት ልዩነት ለማጥበብና ለ25 ቀናት የሚበቃውን የውጭ ምንዛሬ ክምችት ወደ አንድ ወር ለማሳደግ ማቀዱን ሰነዱ ይጠቅሳል ያለው ዘገባው፣ ባንኩ በቀጣዩ ዓመት ሰኔ የውጭ ምንዛሬ ክምችቱን ወደ ኹለት ወር ለማሳደግ ማሰቡንም እንደጠቆመ አመልክቷል።

ኢትዮጵያ ከዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ ከእያንዳንዳቸው 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት ድርድር ላይ ናት።

Via ሪፖርተር - ዋዜማ

የሶማሌላንዱ  ፕሬዝዳንት  ሙሳ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያና የሶማሌላንድን የባህርበር ስምምነት  በዛሬው እለት ለፓርላማ  አቅርበዋል። "ሁለታችንም የምንፈልገው ይታወቃል  ኢትዮጵያ ባህር በር ትፈ...
06/09/2024

የሶማሌላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያና የሶማሌላንድን የባህርበር ስምምነት በዛሬው እለት ለፓርላማ አቅርበዋል።

"ሁለታችንም የምንፈልገው ይታወቃል ኢትዮጵያ ባህር በር ትፈልጋለች፣ እኛም እድሜ ዘመናችንን ሀገር ለመሆን ታትረናል ።

" ያሉት ፕሬዝደንት ሙሴ ...ለፓርላማው ባደረጉት ንግግር "ስምምነት ከሰሞኑን ይፈፀማል ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ግልፅ የሆነ ስምምነት ላይ ደርሰናል፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ታገኛለች እኛም የሀገርነት እውቅና ከኢትዮጵያ ይሰጠናል ሁሉም ስምምነቶች አልቀዋል መፈረም ብቻና ለፓርላማዎቻችን ማፅደቅ ነው የቀረን ብለዋል።

በሌላ በኩል ሁለቱ ሀገራት የተግባር እንቅስቃሴዎችን እያደረጉ ሲሆን የሶማሌላንድ ፖሊስ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ሀዋሳ ከተማ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል። በተጨማሪም የሶማሌላንድ አየር መንገድ ለማቋቋም ዝግጅት የተጀመረ ሲሆን ሶማሌላንድ 4 የመለማመጃ አነስተኛ አውሮፕላኖችን መግዛቷን ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ ተናግረዋል።

Address

Los Angeles, CA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Rising posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share


Other Social Media Agencies in Los Angeles

Show All