Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ

  • Home
  • Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ

Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ ይህ የኖሎት ሚዲያ ነው

❣️ ዲያቆን መኩሪያ ጉግሣበሺህ የሚቆጠሩ መዝሙራትን ለኦርቶዶክስ ዘማሪያን ያበረከተ[ በወፍ በረር ... ]  | ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ከዝማሬ ጀርባ የነበረውና በሺህ የሚቆጠሩ መዝሙራት...
20/04/2024

❣️ ዲያቆን መኩሪያ ጉግሣ
በሺህ የሚቆጠሩ መዝሙራትን ለኦርቶዶክስ ዘማሪያን ያበረከተ

[ በወፍ በረር ... ]

| ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ከዝማሬ ጀርባ የነበረውና በሺህ የሚቆጠሩ መዝሙራትን ለኦርቶዶክስ ዘማሪያን ያበረከተው ዲያቆን መኩሪያ ጉግሣ ፣ ስሙ ሥራውና ጸጋው በስቲከርና በከቭር ላይ ብቻ ተለጥፎ ይኖር ከነበረበት አገልግሎት ወጥቶ ወደ አደባባይ ብቅ ብሏል !!

ለዝማሪ ቴዎድሮስ ዮሴፍ፣ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ፣ ዳግማዊ ደርቤ ፣ ቸርነት ሰናይ ፣ ፍቃዱ አማረ ፣ አቤል መክብብ ፣ ገብረ ዮሐንስ ገብረ ፃድቅ ፣ እስጢፋኖስ ሣህሌ ፣ ኢዮብ ዘለቃ፣ ለምለም ከበደ ፣ ፀዳለ ጎበዜ አዲስ ለማ ፣ ህይወት ተፈሪ፣ የትምወርቅ ሙላት፣ ቅድስት ምትኩ ፣ ትዕግስት ስለሺ፣ ትንቢት ቦጋለ ... በመቶዎች ለሚቆጠሩ ዘማሪያን መዝሙሮችን ደርሷል ...

ደራሲው የብርሃን ሽግግር እና ዝማሬ ተዋህዶ ቁጥር 1 የተሰኙ ሁለት የግጥም መጽሐፍትን ያሳተመ ሲሆን በቅርቡም ለሦስተኛ መድብሉ እየተዘጋጀ መሆኑን አውቀናል።

ዲያቆን መኩሪያ በዘፈኑ ዓለም ለሚታወቁ ባለሙያዎችም ሥራዎችን እንዳበረከተ ሰምተናል ። አፈሩ ይቅለላቸውና ለጥላሁን ገሠሠና ለታምራት ሞላ ሙሉ ሥራ መስራት ተጀምሮ በጤና ችግር ምክንያት ሳይጠናቀቅ እንደቀረ ዲያቆን መኩሪያ ነግሮናል ።

በአሜሪካ ቨርጂንያ ለሚገኝ የልደታ ቤተክርስቲያን ማሰሪያ እንዲውል ለአንጋፋው መሐሙድ አህመድ ፣ በዛወርቅ አስፋውና አለም ከበደ ሙሉ አልበም ሰርቶ አበርክቷል ።

የዘፈን ህይወታቸውን አቁመው በንስሃ ህይወት ላሉት አቦነሽ አድነው ፣ ማርታ አሻጋሪና በዛወርቅ አስፋው ስራዎቹን አበርክቷል።

በቅርቡ ራሱ ደራሲው በከፈተው በዜማ ሰማያት የተለቀቅውን የዘማሪት በዛወርቅ አስፋውን " ፈራሁ " የሚለውን ዝማሬ ለህዝብ አቅርቦም በሚሊዮኖች እየተደመጠ ይገኛል ።

በዛወርቅ አስፋው አስቀድማ የሰራችውን "ይቅርታ" የሚለው ዝማሬም የዲያቆን መኩሪያ ድርሰት ነበር ...

አብነት በአዴ ሜዳና አለሙ ሜዳ መሃል ተወልዶ ከወላጆቹ ጋር ወደ አየር ጤና በመሄድ በአየር ጤና ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ያገለግል የነበረ ሲሆን ዛሬ ኑሮውን ካባለቤቱና ከሦስት ልጆቹ ጋር በአሜሪካ ቨርጂንያ ካደረገ አሥራ አምስት ዓመታት ተቆጥሯል !!

ዲያቆን መኩሪያ የደራሲ ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) ጎረቤት እንደነበረና የገጣሚነት መንፈሳቸው አርፎብኝ ይሆን? እያለ ቢጠይቅም ፣ ግጥምን ግን ከቤተ መቅደስ የግእዝ ጸሎቶች እንደተማረ በመደጋገም ይናገራል !!

20/04/2024
ማኅበረ ቅዱሳን "ኑ ቸርነትን እናድርግ " በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀበአገራችን በሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመደገፍ የሚያስችል ልዩ ...
23/03/2024

ማኅበረ ቅዱሳን "ኑ ቸርነትን እናድርግ " በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ

በአገራችን በሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመደገፍ የሚያስችል ልዩ መርሐ ግብር በሚሊኒየም አዳራሽ የፊታችን መጋቢት 15 ቀን 2016 ዓ.ም "ኑ ቸርነት እናድርግ " በሚል መሪቃል መዘጋጀቱ ተገልጿል።

ጉባኤውን በማስመልከት በማኅበሩ ጽ/ቤት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉኅን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እንደገለጹት ማኅበሩ ከሚያከናውናቸው በርካታ ተግባራት መካከል አንዱ የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንደሆነ ገልጸው ከችግሩ ስፋት አንጻር ባልድርሻ አካላት ለየብቻ የሚያደርጉት ድጋፍ ውጤት ማምጣት ስለማይችል ማኅበሩ ከምእመናን እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እንደሚሠራ አሳውቀዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን የሙያ እና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ ም/ኃላፊ የሆኑት ዲ/ን ንጉሤ ባለውጊዜ እንደተናገሩት በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ወገኖች እንዲሁም በድርቅ እና በተለያዩ ጊዜያት በሚከሰቱ ግጭቶች ምክንያተ በከፈተኛ ችግር ውስጥ የሚገኙ አድባራት እና ገዳማት እንደሚገኙ ገልጸው ማኅበሩ እስካሁን ድረስ አጋር አካላትን በማስተባበር የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ ቆይቷል ብለዋል።

ምክትል ኃላፊው አያይዘው ምእመናን ማኅበሩ በመልሶ ማቋቋም ረገድ እያደረገ ያለውን ድጋፍ እንዲደግፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የማኅበሩ ምክትል ዋና ጸሐፊ ዲ/ን አንድነት ተፈራ እንደገለጹት ምእመናን መጋቢት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ በሚደረገው መርሐ ግብር ላይ በመገኘት የማኅበሩን አገልግሎት በመደገፍ አጋርነታቸውን እንዲያሳዩ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
(ማኀበረ ቅዱሳን)

የቡልጋሪያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ኒዮፊት የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጸመ !ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኒዮፊት የቡልጋሪያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ባሳለፍነው ...
19/03/2024

የቡልጋሪያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ኒዮፊት የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጸመ !

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኒዮፊት የቡልጋሪያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ባሳለፍነው መጋቢት 5 ቀን 2016 ዓ.ም በ78 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ይታወሳል።የፓትርያርኩ የቀብር ሥነ ሥርዓት የሃይማኖት መሪዎች እና የመንግስት ባለሥልጣናት እንዲሁም ቡልጋሪያውያን በተገኙበት የተፈጸመ መሆኑ ተገልጽዋል። ለፓትርያርኩ በሶፊያ ዋና አሌክሳንደር ኔቪስኪ ካቴድራል ሽኝት እና ጸሎተ ፍትሐት ተደርጓል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ የቅዱስነታቸውን ዕረፍት ተከትሎ በቀጣዮቹ 4 ወራት ውሰጥ አዲስ ፓትርያርክ እንደሚሾም እየገለጸ ይገኛል።የቡልጋሪያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ቤተሰብ ስትሆን የኦርቶዶክስ ክርስትና የቡልጋሪያ ዋነኛ ሃይማኖት እና ከጠቅላላ የሀገሪቱ ሕዝብ 85% ኦርቶዶክሳውያንመሆናቸውን መረጃዎች ያመላክታሉ።

Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ

➕ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወልደ ነጎድጓድ➕ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ፍቁረ እግዚእ፣ ነባቤ መለኮት/ታኦሎጎስ/፣ቁጽረ ገጽ በመባል ይታወቃል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ...
13/03/2024

➕ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወልደ ነጎድጓድ➕

ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ፍቁረ እግዚእ፣ ነባቤ መለኮት/ታኦሎጎስ/፣ቁጽረ ገጽ በመባል ይታወቃል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን የመጀመሪያው ወጣት የመጨረሻው ሽማግሌ ሐዋርያ እሱ ነበር፡፡ ቅዱስ ዩሐንስ የተወለደው በገሊላ አውራጀ በቤተ ሳይዳ ነው፣ አባቱ ዘብዴዎስ ይባላል፡፡

ቅዱስ ዩሐንስ ገና በወጣትነቱ ዘመን ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮ የጌታውን እግር ተከትሎ አድጓል፡፡ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የጌታ ደቀ መዝሙር ከመሆኑ በፊት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበሩት ደቀ መዛሙርት አንዱ ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ለጌታውና ለፈጣሪው ለመድኃኔዓለም ክርስቶስ ባሳየው ልዩ ቀረቤታና ፍቅር ምክንያት “ፍቁረ እግዚእ” የሚል ስያሜ አግኝቷል፡፡ ፍቅሩንና ታማኝነቱንም ጌታ በተሰቀለ ጊዜ “እሱን ያገኘ ያገኘኛል፡፡” ብሎ ሳይፈራ ከእግረ መስቀሉ በመዋል በጽኑ እምነት አስመስክሮአል፡፡ በመሆኑም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ በመጨረሻዋ ሰዓት ቅዱስ ዮሐንስን ከእመቤታችን ጋር ከእግረ መስቀሉ ባየው ጊዜ እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምን “እነሆ ልጅሽ ይርዳሽ፣ ያጽናናሽ”፤ ብሏታል፡፡ ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስም “እነኋት እናትህ ታጽናናህ” ብሎታል፡፡ ዩሐ. 19፥26፡፡

ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እነሆ ልጅሽ ይርዳሽ ያጽናናሽ” ማለቱ እኛን ለቀረነው ክርስቲያኖች በቅዱስ ዮሐንስ አማካኝነት ለእመቤታችን መስጠቱን፣ ደቀ መዝሙሩን ቅዱስ ዮሐንስ “እነኋት እናትህ ታጽናናህ” ማለቱ እኛን እመቤታችሁ እናታችሁ ቅድስት ድንግል ማርያም ናትና ታጽናናችሁ፣ ተስፋ አለኝታ ትሁናችሁ ማለቱ እንደሆነ በግልጽ እንረዳለን፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ እንደ ጌታው ቃል እመቤታችንን ወደ ቤቱ ይዟት
ስለሄደ እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ አስራ አምስት አመት ተቀምጣለች፡፡ከዚህም ኃይለ ቃል የምንማረው እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ እንደኖረች ሁሉ በልበ ምእመናንም አድራ በሃይማኖት የምታጸና፣ ምግባረ ሃይማኖትን፣ ሕገ ትሩፋትን የምታሰራ፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ድኀነተ ስጋንና ድኀነተ ነፍስን፣ በረከተ ስጋንና በረከተ ነፍስን የምታሰጠን መሆንዋን ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ የጌታ ትንሣኤ በተነገረ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ቀድሞ ከመቃብረ ክርስቶስ ከጎልጎታ እንዲገኝ ያደረገው የፍቅሩ ጽናት ነበር፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ የድንግልና ሕይወትም ረቂቁን
ምስጢረ መለኮት /ምስጢረ ሥላሴ/ ለማየት አስችሎታል፡፡ ምስጢረ ሥጋዌን አስተካክሎ አደላድሎ በመጻፍ አምልቶ አስፍቶ አስተምሯል፡፡ የፍቅረ እግዚአብሔርን እና የፍቅረ ቢጽን ጠቃሚነት በስፋት የጻፈ ቅዱስ ዮሐንስ ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ረቂቁን ምስጢር አጉልቶ አምልቶ አስፍቶ ያስተማረ በመሆኑም ቤተክርስቲያን እንዲህ እያለች ታወድሰዋለች፡፡

ባሕረ ጥበባት፣አበ ልሳናት፣ ንስር ሠራሪ ልዑለ ስብከት፡፡

ዮሐንስ ወንጌላዊ ረአዩ ኀቡአት፡፡ ነገሩኒ ቅሱም በፄወ መለኮት። ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት፡፡ ቀዋሚሃ ለቤተክርስቲያን፣
ኮከብ ስርግው፣ ውስተ ሕፅነ ገጽ ዘተሐፅነ፣ ዘኀቡአ ይኔጽር ምስጢረ መለኮት ። ዘመንክረ ይገብር አምሳለ መላእክት

ዮሐንስ ድንግል ባሕረ ጥበባት የጥበባት ባሕር፣ የልሳኖች አባት፣

ሰማያትን ሰንጥቆ የሚበር ንስር፣ ልዑለ ስብከት፣ ኀቡአትን / ምሥጢራትን/ የሚያይ ወንጌላዊ ዮሐንስ ወዘተ ይባላል፡፡


ዲያቆን ኤሳሁን ተክሌ

የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አራም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች ጋር ተወያዩብፁዕ ወቅዱስ አራም የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን...
10/03/2024

የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አራም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች ጋር ተወያዩ

ብፁዕ ወቅዱስ አራም የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በሊባኖስ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና የማኅበረሰብ አመራሮች ጋር በሳምንቱ መጀመሪያ ተወያይተዋል።

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች የቤተክርስቲያኒቱን ኃላፊዎች መንፈሳዊና ወንድማዊ ሰላምታ አቅርበዋል ቅዱስነታቸው ላሳዩት እንክብካቤ እና ደማቅ አቀባበል አድናቆታቸውን ገልጸው፤ በአካባቢው በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በሊባኖስ ወደ 70,000 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በተለያየ የሥራ መስክ ተሰማርተው እንዳሉ የተነገረ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 50,000 የሚሆኑት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሆናቸው ተገልጽዋል።

ዘገባውን ለማሰናዳራት የአርመን ቤተ ክርስቲያንን ይፋዊ ድረ ገጽ ተጠቅመናል።

07/03/2024

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜንየካቲት 28-ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ ከስድስት ሺህ ሦስት መቶ አራት ማኅበርተኞቹ ጋር በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ በቴዎድሮስ ስም የሚጠሩ...
07/03/2024

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 28-ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ ከስድስት ሺህ ሦስት መቶ አራት ማኅበርተኞቹ ጋር በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ በቴዎድሮስ ስም የሚጠሩ ከዘጠኝ በላይ ቅዱሳን ሰማዕታት አሉ፡፡ በተለይም ታላላቆቹ ሰማዕታት ማለትም ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት፣ ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ፣ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ የእነዚህን የሦስቱን ታሪክ የመደባለቅ ችግር አልፎ አልፎ ይታያል፡፡ ዛሬ በዓመታዊ የዕረፍቱ በዓል አስበነው የምንውለው ሮማዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ ነው፡፡ ይኽም ሮማዊው ቴዎድሮስ በዘመነ ሰማዕታት በነገሥታቱ መክሲሞስና መክሲምያኖስ ዘመን የነበረ ከእስያ አውራጃ አስጢር ከሚባል አገር የተገኘ ከታላላቅ ሰማዕታት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ በነገሥታቱ ዘንድ ‹‹የእናንተን አማልክትን አያመልክም›› ብለው ወነጀሉት፡፡ በግልጽ ወደ አደባባይ ወጥቶ በዐላዊያን ነገሥታት ፊት ስለ እምነቱ መስክሮና አስተምሮ ብዙዎችን ወደ እምነት መልሷል፡፡

ነገሥታቱም አስጠርተው ለጣዖታቸው ለምን እንደማይሰግድ ሲጠይቁት ‹‹እኔ ክርስቲያን ነኝ፣ ከሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬና ከፈጣሪዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አላመልክም›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ነገሥታቱ በእሳት እያቃጠሉና ሌሎችንም እጅግ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሱበት፡፡ የበርብዮስጦስ ልጅ ንጉሥ ‹‹ለአማልክቶቼ ብትገዛ በወታደሮቼና በመኳንንቶቼ ሁሉ ላይ አዛዥ አለቃ አድርጌ እሾምሃለሁ፣ ብዙ ወርቅና ብር የከበሩ ልብሶችም እሰጥሃለሁ…›› አለው፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስም ንጉሡን ‹‹ወርቅህና ብርህ ለጥፋት ይሁኑህ፣ እኔስ በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ባለጸጋና አለቃ ነኝ›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹ለአምላክ ልጅ አለውን?› ብሎ ጠየቀው፡፡ ቅዱሱም ‹‹አዎን ከመለኮቱ ባሕርይ የተገኘ ከእርሱ ጋራ ዓለምን የፈጠረ በእውነት ልጅ አለው›› ብሎ መለሰለት፡፡ ንጉሡም ‹‹አምላህን ብናውቀው ልናገኘው እንችላለን?›› ሲለው ቅዱስ ቴዎድሮስም ‹‹ወደ እርሱ ከተመለስክ እንደእኔ አገልጋዩ ትሆናለህ፣ የተወደደ መሥዋዕትም ያደርግሃል›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ‹‹ነገር አታብዛ ብዙ ገንዘብ እሰጥህ ዘንድ ለአማልክቶቼ መሥዋዕትን አቅርብ›› ብሎ ብዙ በተከራከረው ጊዜ ቅዱስ ቴዎድሮስ አማልክቶቹን ሰደበበት፣ ንጉሡንም ረገመው፡፡ ንጉሡም ተቆጥቶ ራቁቱን ካስገረፈው በኋላ በትምህርቱ ካመኑት ክርስቲያኖች ጋር በጨለማ ቤት አሠረው፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስም ከጸለየ በኋላ ሌሊት ወጥቶ እንጨት ከሰበሰበ በኋላ ጣዖታቱን ሁሉ አመድ እስኪሆኑ ድረስ በእሳት አቃጠላቸው፡፡ እንዳይሰሙም እግዚአብሔር በጣዖታት አገልጋዮቹ ላይ ከባድ እንቅልፍ ጥሎባቸው ነበር፡፡ ንጉሡም በኋላ ይህን በሰማ ጊዜ ቅዱስ ቴዎድሮስን በጽኑ ሥቃይ አሠቃይቶ ይገድለው ዘንድ ለመኮንኑ አሳልፎ ሰጠው፡፡

የንጉሡ መኰንንም ቅዱስ ቴዎድሮስን በመጀመሪያ የንጉሡ ትእዛዝ እንዲቀበልና ለጣዖታት እንዲሰግድ አግባባው፡፡ ቅዱሱም ‹‹እኔስ ለረከሱ አማልክት አልሠዋም፣ ለከሃዲ ንጉሥም አልታዘዝም›› አለው፡፡ መኮንኑም ቅዱስ ቴዎድሮስ በእምነቱ እንደጸና እና ትእዛዛቸውን ቸል እንዳለ ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ ዘሎ በመነሣት አንገቱን አነቀው፡፡ ይዞም በጽኑ ሥቃይ ሲያሠቃየው ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ መኰንኑን ገድሎ በአዘቅት ውስጥ ካሰጠመው በኋላ ለከበረ ቴዎድሮስ በእስያ ሀገር እየተዘዋወረ ወንጌልን እንዲያስተምር መንፈሳዊ ፀዓዳ ፈረስ ሰጠው፡፡ ንጉሡም ይህን ሲሰማ ከነፈረሱ እንዲይዙት በእርሱ ትምህርት ያመኑትንም እንዲይዙአቸው መቶ ፈረሰኞችን ላከ፡፡ መቶው ፈረሰኞችም ከሴቶችና ከልጆች በቀር ስድስት ሺህ አርባ ስምንት ያመኑ ክርስቲያኖችን በመሰየፍ ሰማዕትነትን እንዲያገኙ አደረጓቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ሊይዙት ፈልገው ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ በተጠጉ ጊዜ ፈረሱ በላያቸው ተወረወረ፡፡ ከፈረሱም አፍ እሳት ወጥቶ አመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጠላቸው፡፡ ፈረሱ ፀዓዳ ቀይ ሲሆን ትንፋሹ እሳት ስለነበር አላዊያንን የፈረሱ ትንፋሽ እያቃጠለ ይፈጃቸው ነበር፡፡ እነርሱ ግን በዚህ የሚድኑ መስሏቸው የቴዎደሮስንም ሆነ የፈረሱን አፍ ለመለጎም ቢያስሩም የፈረሱ ትንፋሽ ቢያገኛቸው 7 ሺህ ዐላዊያን በአንድ ጊዜ ሞተዋል፡፡

በሌላም ጊዜ ቅዱስ ቴዎድሮስን ይዘው ካሠቃዩት በኋላ አሠሩት፡፡ በእሥር ቤትም ሳለ ጌታችን ተገለጠለትና ታላቅ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ በማግሥቱም ዘቅዝቀው ሰለቅለው ደሙ እንደ ውኃ እስኪፈስ ድረስ ጽኑ ግርፋትን ገረፉት፡፡ በዚህም ጊዜ ደሙ ያረፈባቸው ብዙ ሕመምተኞች ስለተፈወሱ ሁሉም በጌታችን አመኑ፡፡ ይህንን የቅዱስ ቴዎድሮስን ታላቅ ተአምር ያዩትና በዕለቱ ካመኑት ውስጥ 148 ሰዎች የጌታችንን አምላክነት መስክረው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡

የእነዚህን በሰማዕትነት ያረፉትን ሰዎች አስክሬናቸውን ለማቃጠል ወደ እሳት ምንደጃ ውስጥ ከቅዱስ ቴዎድሮስ ጋር ጨመሯቸው፡፡ ወዲያውም ነፋስ ነፍሶ መብረቅና ነጎድጓድ ሆኖ እሳቱን አቀዘቀዘው፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስንም ከሰማዕታቱ አስክሬን ጋር አብረው በእሳት ውስጥ ቢጨምሩትም እሳቱ ምንም ሳይነካው ደህና ሆኖ ወጣ፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የሚያደርግበትን ሲያጣ እጆቹንና እግሮቹን ቸንክሮ አፉን በልጓም ለጉሞ ለተራበ አንበሳ ሰጠው፡፡ ነገር ግን አንበሳው እንደ ሰው ዕንባውን አንጠባጥቦ አለቀሰለት ለክብሩም ሰገደለት እንጂ ምንም አልነካውም፡፡ ጌታችንም ዳግመኛ ለቅዱስ ቴዎድሮስ ተገለጠለትና ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ዕድል ፈንታውን ከእርሱ ጋር በመንግሥተ ሰማያት እንደሚያደርግለት ታላቅ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ ዳግመኛም ‹‹በስምህ የዘከረ በመንበረ ጸባኦት ስሙ ይጻፋል›› የሚል አስገራሚ ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የ200 ሰው ሸክም ዕንጨት አስመጥቶ ጉድጓድ አስቆፍሮ በውስጡ ባሩድ፣ ነሐስና ሌሎችም ሰውነትን ቆራርጠው የሚጥሉ ነገሮችን ጨምሮ እሳት አስነደደና ቅዱስ ቴዎድሮስን በዚያ በነደደው እሳት ውስጥ ጨመረው፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስም ሰማዕትነቱን ከስድስት ሺህ ሦስት መቶ አራት ማኅበርተኞቹ ጋር የካቲት 28 ቀን በድል ፈጸመ፡፡
የመላእክት አለቆች ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤልም የቅዱስ ቴዎድሮስን ቅድስት ነፍሱን ተቀበሉትና ሦስት አክሊላትን አቀዳጁት፡፡ ሥጋውንም አውሳብያ የተባለች የመኰንኑ ሚስት ወስዳ ዋጋው እጅግ ውድ በሆነ ሽቱ በክብር ገንዛ ወደ ገላትያ ወሰደችው፡፡ የተዋበች ቤተ ክርስቲያንም ሠራችለት፡፡ ከቅዱስ ቴዎድሮስ ሥጋ ብዙ ተአምራት ተገልጠው ታዩ፡፡ የቅዱስ ቴዎድሮስ ማኅበርተኞች የሆኑ የ6304 ሰዎችም የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ በዓል በዚሁ ዕለት በየካቲት 28 ተፈመ፡፡ የዚህ ታላቅ ሰማዕት በሀገራችን በጣና ቂርቆስ ገዳም ውስጥ በጣም ትልቅ ገድል አለው፡፡
የቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን! Youtube channel subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://m.youtube.com/channelUCJxEO4QM1BY0Xy5H2LdekYA?Sub_confirmation=1

በወላይታ ሶዶ በአታ ለማርያም ቤተክርስትያን ይዞታ "ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል" በሚል ምክንያት በጸጥታ አካላት በጉልበት እየፈረሰች ነው***በአንድ ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን ስጦታ ሰጪነት በተገኘ ...
06/03/2024

በወላይታ ሶዶ በአታ ለማርያም ቤተክርስትያን ይዞታ "ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል" በሚል ምክንያት በጸጥታ አካላት በጉልበት እየፈረሰች ነው
***

በአንድ ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን ስጦታ ሰጪነት በተገኘ መሬት ላይ የተተከለችው በወላይታ ሶዶ ከተማ የምትገኘው ዋዱ በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን

የወላይታ ዞን ስፍራውን ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል በሚል ምክንያት መቃኞ ህንጻ መቅደሱን ለማፍረስ የጸጥታ ኃይል ያሰማራ ሲሆን

የጸጥታ አካላት የጦር መሳርያ በመጠቀም ምዕመናንን ከአከባቢው ለማራቅ ቢሞክሩም አሁን ድረስ ህዝቡ ቤተክርስቲያኒቷን ከበ በመያዝ የማፍረስ ተግባሩን ለማስቆም እየሞከረ ይገኛል።

የጸጥታ አካላት እና የወላይታ ዞን መንግስት ከቅድስት ቤተክርስቲያን አሳዳጅነት እራሱን አቅቦ ከፍትህ እና ከእውነት ቆም በተረጋጋ ማሰብ ቢችል መልካም ነው።

Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Nolot Media -ኖሎት ሚዲያ:

Videos

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Videos
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share