Aminadab MEDIA

  • Home
  • Aminadab MEDIA

Aminadab MEDIA Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Aminadab MEDIA, Media/News Company, .

የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ።የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር)  ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና  መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተ...
14/03/2022

የ2013ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል (ዶ/ር) ለጋዜጠኞች የ12ኛ ክፍል መለቀቂያ ፈተና መቁረጫ ነጥብ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

በሁለት ዙር ለተሰጠው የመልቀቂያ ፈተና የተሰጠው የማለፊያ ነጥብ የተለያየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤት የሚከተለውን ይመስላል

በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 363 ለሴት 351 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 351 ለሴት 339 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 300 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 380 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።

በመጀመሪያው ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 300 ሆኗል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 264፣ ለሴት 254 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 254፣ ለሴት 250 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 250 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 280 እንደሆነ ተገልጿል።

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ 250 ሆኗል።

በሁለተኛ ዙር ፈተናቸውን የወሰዱ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች ውጤትም ይፋ የሆነ ሲሆን በዚህም መሰረት

በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ለመማር ለተፈጥሮ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞት ማለፊያ ነጥብ ለወንድ 423 ለሴት 409 ሲሆን በተፈጥሮ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 410 ለሴት 396 ማለፊያ ነጥብ መሆኑ ተገልጿል።ለተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 350 ሆኗል።በተፈጥሮ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ማለፊያ ነጥብም 443 ሆኖ መቆረጡ ተገልጿል።

በሁለተኛ ዙር የተፈተኑ እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የተፈጥሮ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ350 በላይ መሆኑ ተነግሯል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መደበኛ ተፈታኞች የማለፊያ ነጥብ ለወንድ 317 ፣ ለሴት 305 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ በታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ላሉ መደበኛ ተፈታኞች ለወንድ 305፣ ለሴት 300 ማለፊያ ነጥብ ሆኖ ተቆርጧል።

ለማህበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ሁለቱም ፆታዎች ማለፊያ ነጥብ 300 መሆኑን እና በማህበራዊ ሳይንስ ድጋሜ ተፈታኞች ለሁለቱም ፆታ የማለፊያ ነጥብ 335 እንደሆነ ተገልጿል።

በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የማህበራዊ ሳይንስ መቁረጫ ነጥብ ከ 300 በላይ መሆኑም ተገለጿል።

ውጤቱ ለመጀመርያ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ500 የተያዘ መሆኑን እና በሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ700 እዲሁም ለማህበራዊ ሳይንስ ከ600 የተያዘ መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር


https://t.me/+L57_9BSTiR1iZTA0

በጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በህወሓት ተይዘው የነበሩ ተጨማሪ ቦታዎች ነፃ ማውጣቱ ተገልጿል። የፀጥታ ኃይሎች ጥምረቱ ፦- የመሐል ሜዳ፣ - ጨፋ ሮቢት፣...
04/12/2021

በጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በህወሓት ተይዘው የነበሩ ተጨማሪ ቦታዎች ነፃ ማውጣቱ ተገልጿል።

የፀጥታ ኃይሎች ጥምረቱ ፦
- የመሐል ሜዳ፣
- ጨፋ ሮቢት፣
- ሐርቡና መኮይ ከተሞችና አካባቢውን ነጻ እንዳወጣ የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አሳውቋል።

የኢትዮጵየ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ " ጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ በጥልቀት ገብተው በየቦታው የተበተነውን የአሸባሪውን ጀሌ በመልቀም ላይ ናቸው " ብሏል።

አክሎም ፥ " በጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ የተመታው አሸባሪ ኃይል ዘርፎና አውድሞ፣ መሣሪያውንም ይዞ እንዳይወጣ የየአካባቢው ሕዝብ ተደራጅቶ መንገድ በመዝጋት ፣ የአሸባሪውን ጀሌዎች በመማረክ ፣ እምቢ ባሉትም ላይ ርምጃ በመውሰድ የተለመደ ጀግንነቱን እንዲደግም " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

  ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከነገ ጀምሮ ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ አሳወቁ።ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ዛሬ ምሽት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰራጩት ፅሁፍ ኢትዮጵያ አሁን እያደረገችው ያለው...
23/11/2021


ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከነገ ጀምሮ ወደ ግንባር እንደሚዘምቱ አሳወቁ።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ዛሬ ምሽት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰራጩት ፅሁፍ ኢትዮጵያ አሁን እያደረገችው ያለው ትግል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ትግል ነው ብለዋል።

"ትግሉ ልጆቻችን ሀገር እንዲኖራቸው የሚደረግ ትግል ነው። ልጆቻችን ክብርና ነጻነትን ለብሰው፣ በዓለም አደባባይ በኩራት ቀና ብለው እንዲሄዱ የሚደረግ ትግል ነው፤ በዓለም ላይ በክብር የምንጠራበት ስም እንዲኖረን የሚደረግ ትግል ነው። መኖር ወይም አለመኖራችንን የሚወስን ትግል ነው። ያለ ጥርጥር ግን እናሸንፋለን። ኢትዮጵያን ጠርቶ መሸነፍ ፈጽሞ የማይታሰብ ነው" ነው ሲሉ ገልፀዋል።

"ጊዜው ሀገርን በመሥዋዕትነት መምራት የሚያስፈልግበት ጊዜ ነው" ያሉት ዶ/ር ዐቢይ፥ " ከእንግዲህ እኔ መከላከያን በግንባር ሆኜ ለመምራት ከነገ ጅምሮ ወደ ትግሉ ሜዳ እዘምታለሁ። ታሪክ ከሚያደንቃቸው የኢትዮጵያ ልጆች አንዱ ለመሆን የምታስቡ ሁሉ ለሀገራችሁ ስትሉ ዛሬውኑ ተነሡ፤ ግንባር ላይ እንገናኝ" ብለዋል።

ዶ/ር ዐቢይ፥ "የእኛ መዝመት የሚፈጥረውን ክፍተት ከግንባር የቀሩት በሙሉ ዐቅማቸው ሸፍነው ይሠራሉ" ያሉ ሲሆን "በግንባር ያልተሰለፉ የክልልና የፌደራል አመራሮች ከመቼውም ጊዜ በላይ የልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሙሉ ዐቅማቸው ይከውናሉ" ብለዋል።

https://youtu.be/0vw9QL0F67s
09/10/2021

https://youtu.be/0vw9QL0F67s

THANKS FOR WATCHING 🚩DON'T FORGET TO LIKE COMMENT & SUBSCRIBE!🔴 TikTok Ethiopian Funny Video Compilation 2021 እጅግ አስቂኝ ቀልዶች ስብስብ 9th shi drama,9 shi,new et...

01/10/2021

https://youtu.be/xTmiG8fJ2VE
04/09/2021

https://youtu.be/xTmiG8fJ2VE

THANKS FOR WATCHING 🚩DON'T FORGET TO LIKE COMMENT & SUBSCRIBE!🔴 ምርጥ ፊልም ማያ ዌብሳይት|| Best Movie watching site ||Part 19th shi drama,9 shi,new ethiopian movie...

Address


Telephone

+251941120840

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Aminadab MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Aminadab MEDIA:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share