Wolo express / ወሎ ኤክስፕረስ

  • Home
  • Wolo express / ወሎ ኤክስፕረስ

Wolo express / ወሎ ኤክስፕረስ voice of people /የህዝብ ድምፅ

06/12/2023
23/11/2023

“ወሎ ክልል” - ለምን?

ወሎ ክልል እንዲሆን የብዙ ወሎየዎች ፍላጎት ነው፡፡ ይህ ፍላጎት በስሜታዊነት የሚቀነቀን አጀንዳ አይደለም፡፡ ይህ ፍላጎት የ30 ዓመት በደል የወለደው ነው፡፡ ወሎ ክልል ይሁን እያልን ያለነው፣ ወሎ በአማራ ክልል ካሉ ሌሎች አካባቢዎች በተለይም ከምዕራብ አማራ (የክልሉ ሰዎች ጭምር ምስራቅ አማራ ስለሚሉን) አንጻር ሲታይ በኢኮኖሚ እንዲደቅ፥ ማህበራዊ ስሪትና መስተጋብሩ እንዲናጋ፥ ፖለቲካዊ ተሳትፎው ከዜሮ በታች እንዲሆን በመደረጉ ነው፡፡ ወሎ ለክልሉ የሰጠውን ያህል እንዳያገኝ ሆን ተብሎ ስለተሰራበትና እየተሰራበት ስለሆነ መገፋት የወለደው የመነጠል ስሜት ነው፡፡
በቀድሞው ብአዴን፣ በመካከለኛው ዘመን አዴፓ እና በአሁኑ የአማራ ብልጽግና፣ በወሎ ላይ ሆን ተብለው የተፈጸሙ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ በደሎችንና የፖለቲካ ደባዎችን አንድ በአንድ መዘርዘር ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ዝርዝር መቅረብ ያለበት ለውሳኔ ሰጪው ህዝባችን መሆን ስለሚገባው በየጋዜጣውና በየሚዲያው ላይ በደል እየቆጠርን፣ በተበዳይነት ስሜት መጯጯህ ትርጉም የለውም፡፡
በሌላ በኩል፤ የአማራ ክልል ዲሞክራታይዜሽን፣ ለወሎየዎች ማህበረሰባዊ ጥያቄ መፍትሄ ሊሆን እንደማይችል ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡ ምክንያቱም አማራ ክልል ያለው የገነገነ አምባገነንነትና ጎጠኝነት በዲሞክራታይዜሽን ሂደት የሚቃና እንደማይሆን ባለፉት 30 ዓመታት በጥሩ ሁኔታ ታይቷል፡፡ እናም ወሎ ከዚህ “በሽተኛ ጥምረት” እስካልተፋታ ድረስ ለ30 ዓመታት የወረደበት መከራና የደረሰበት ጉዳት የሚቀጥል መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ እናም ራሱን የቻለ ክልላዊ አስተዳደርን መመስረት ቀዳሚ መፍትሄ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡
የወሎ የክልልነት ጥያቄ ከብሄርም ከሃይማኖትም የማይገናኝ በማህበራዊ፥ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥን በጉልህ የሚታይ ጥያቄ ነው፡፡ የአማራ ክልል ጉዳዬ ብሎ የማያያቸው፣ ምላሽ ለመስጠትም የማይፈልጋቸው፣ ወሎ ውስጥ ብቻ የሚታዩ በርካታ ችግሮች አሉ፡፡ እነዚህም ችግሮች የአካባቢውን ማህበረሰብ (በተለይም ወጣቶችን) ለስደትና ለእንግልት ዳርገዋል፤ የስራ እድል ባለመፈጠሩ ለሱስ ተጋላጭ እንዲሆኑ ተፈርዶባቸዋል፡፡ የስራ አጥ ቁጥር ጨምሯል። አካባቢውን ከልማት እንዲርቅ አድርገዋል። ታሪካዊ የሆኑ የወሎ የራያና የዋግ ህዝብና ግዛቶች ወደ ትግራይ እንዲካለሉ ሲደረግ፣ ክልሉ በቸልተኛነትና በንዝህላልነት አስወስዶ፣ አሁን አላስፈላጊ ንትርክና ጦርነት ውስጥ ማግዶናል። ከሌሎች የክልሉ ዞኖች አንፃር በአራቱ ዞኖች የሚገኘው የወሎ ህዝብ፣ በኢኮኖሚ ወደ ኋላ እንዲቀር ተደርጓል፡፡
ከመከላከያ ሰራዊት እስከ ክልል ልዩ ኃይል፣ ከፌዴራል ሚኒስቴር እስከ ክልል ባለስልጣን እየተገፋ ያለው የወሎ ተወላጅ ነው። ህዝቡ በጦርነት እየዳሸቀ፣ በርሐብ እየማቀቀ ነው፡፡ በህልውና ዘመቻ ስም በሬውን ሽጦ የታጠቀውን መሳሪያ እየተቀማ ያለው የወሎ ህዝብ ነው። የአማራ ልሂቃን ነን በሚሉ “እውቀት አልባ ምሁራን” እና በአማራ ክልል አመራሮች መርዝ እየተነሰነሰበት ያለውና ጥርስ እየተነከሰበት ያለው የወሎ ህዝብ ነው። ሌላው ቀርቶ ለህክምና እና ለሌላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ ወደ ሀገሪቱ ዋና ከተማ እንዳይገባ እየተከለከለ ያለው የወሎ ህዝብ ነው። ይህ ሲሆን ክልሉ ምን አደረገ? ስለ ወሎ ህዝብ ሆኖ ተከራከረ? ክልሉ ምንም ትንፍሽ ሲል አይሰማም! ስለሆነም፤ በፖለቲካና ኢኮኖሚው የተገፋው፣ ባህልና ማንነቱን ያጣው የወሎ ህዝብ፣ የራሱን የክልል አስተዳደር ለመመስረት ይገደዳል።
ይቀጥላል........

Address

Adis Abeba

Telephone

+251945527874

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolo express / ወሎ ኤክስፕረስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wolo express / ወሎ ኤክስፕረስ:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share