03/01/2024
እንዲሁ ኋለኞች ፊተኞች፥ ፊተኞችም ኋለኞች ይሆናሉ፤ የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።
ማቴዎስ 20:16
"በኔ ተራ ነዉ የቆምሽዉ.. ብሎ ጅማ ላይ ሊደበድበኝ ነበር!!"😭😭
ዘማሪት ዘርፌ ከበደ
እንደዉ ሲነሳ ነገሩ ገርሞኝ ነዉ። ጌታ በጊዜዉ ነገሮችን ይገልጣል፤ ቤቱንም ራሱ ያጠራል። ከወንድሜ ኤፍሬም ዓለሙ ጋር በአገልግሎት በሁለት የአገልግሎት መድረኮች ተገናኝተን አገልግለን ነበር። እናም ተራ ተሰጥቶኝ አገልግዬ ከመድረክ ስወርድ "በኔ ተራ ነዉ የቆምሽዉ!" ብሎ ሰድቦኝ የሙዚቃ ተጫዋቾቹ ቢያረጋጉትም ካልደበደብኳት ሁሉ ብሎ እንደነበር ቤዝ ጊታር ተጫዋች እነ አማኒ ገላግለዉ ነዉ ከኤፍሬም ቡጢ የተረፍኩት፡፡ ኤፊ በጣም ስሜታዊ ነዉ፡፡ እባካችሁ ጌታን እንደሚያዉቅ ሰዉ እንዲሆን ምከሩት፡፡ እኔ እሱ ባለበት መድረክ ሁለተኛ ላለመገኘት የወሰንኩት ከተረበሽኩበት የጅማዉ የአገልግሎት መድረክ በኋላ ነዉ።"