25/04/2023
አንድ ንጉስ አስር ተናካሽ ውሾች (Wild dogs) ነበሩት ፤ እነዚህን ውሾችም አገልጋዮቹን ሲያጠፉ ለማሰቃየትና ለማስበላት ይጠቀምባቸው ነበር፤
:
ከዕለታት አንድ ቀን አንዱ አገልጋይ ያልተገባ ንግግር ንጉሱን ተናገረው ፤ በዚህም ምክንያት ንጉሱ እጅግ ተቆጣ ፤ ወዲውም ወደ ውሾቹ ጉድጓድ እንዲወረወር ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ አገልጋዩም በሀዘን "አስር አመታት አገለገልኩህ ፤ ተገዛውልህ ያልከኝን ሁሉ አደረኩልህ ፤ አሁን ግን ይህንን አደረክብኝ ፤ እባክህ ወደ ውሾች ጉድጓድ ከመወርወሬ በፊት አስር ቀን ስጠኝ" ብሎ ተማጸነው፡፡
፡
ንጉስም ተስማማ "ፈቀደለት" ፡፡ ይወረወር ዘንድ የተፈረደበት አገልጋይ ውሾቹን ወደሚንከባከበው ሌላኛው አገልጋይ ሔደና "እባክህ እነኝህን ውሾች ለአስር ቀን ልንከባከባቸው"ብሎ ጠየቀው፡፡ የውሾቹ ጠባቂም ግራ ቢጋባም ይፈቅለታል ፡፡
፡
የተፈቀደለት አገልጋይም ውሾቹን መንከባከብ ጀመረ ፤ ቆሻሻቸውን ማጸዳዳት ፤ ምግባቸውን በሰዓቱ ማቅረብ ፤ ማጠብና አስፈላጊውን እንክብካቤ ሁሉ አደረገላቸው ፤ አስር ቀኑም አለቀ፡፡
፡
ከዚያም በኋላ ከንጉስ ጋር በተነጋገሩት መሰረት …አገልጋዩ ተጠርቶ ወደ ተናካሽ ውሾቹ ጉድጓድ ይወረወር ዘንድ አዘዘ ፤ ወረወሩትም ፡፡ ወርዋሪዎቹም ይህ አሽከር እንዴት በውሾቹ ሊበላ እንደሚችል እየዘገነናቸው መመልከት እንደጀመሩ ያላሰቡትን ሁኔታ በአይናቸው አየ፤
፡
ንጉሱም በሚመለከተው ሁኔታ ግራ ተጋባና «እነዚህ ተናካሽ ውሾቼ ምን ሆነው ነው ዛሬ? ምንስ ገጠማቸው?» ማለት እንደጀመረ…
፡
የተወረወረው አገልጋይ በውሾቹ መሃል ውሾቹ እያተሻሹት በኩራት እየተራመደ እንዲህ አለ "እነዚህን ውሾች ለአስር ቀናቶች ብቻ መገብኳቸው ተንከባከብኳቸው እነርሱም ያደረኩላቸውን በፍጹም አልዘነጉም ፤ አንተን ግን አስር አመት ሙሉ ተገዛሁልህ አገለገልኩህ ነገር ግን በአንዲት ጥፋት ምክንያት ሁሉንም ረሳህና ለሞት አሳልፈህ ሰጠኸኝ" አለው ፡፡
፡
ንጉሱም ሁኔታውን ሁሉ በማስተዋልና ፤ ከውሾች እንዳነሰም በመገንዘብ አገልጋዩ ነጻ እንዲሆን አዘዘ ፤ ነጻም ሆነ፡፡
፡
ሰው በጣም ብዙ ውለታ ውሎላቸው ነገር ግን በአንድ ጥፋት ምክንያት የተደረገላቸውን ሁሉ እየረሱ በክፋት ለሚነሳሱ ሁሉ ይሁን፡፡ በመልካም ነገር የተሞላ ታሪክን ፤ በአንድ ስህተት ምክንያት ከንቱ አናድርግ፡፡
መልእክቱ አስተማሪ ሆኖ ካገኙት ሼር ላይክ እና ሼር በማድረግ ለሌሎች አጋሩ።
Tesfaye
photo credit - Teddy beer,Hyderabad
Source:[Occasion.com]