ያሬድ ያሲን - Yared Yasin

  • Home
  • ያሬድ ያሲን - Yared Yasin

ያሬድ ያሲን - Yared Yasin Personal Page

10/09/2022

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አክሊሉ ለማ የ2015 ዓ/ም አዲስ ዓመት በዓል በማስመልከት የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ለመላው ወላይታ ብሔረሰብና ለሀገራችን ህዝቦች እንኳን ለኢትዮጵያዊያን የዘመን መለወጫ አዲሱ አመት በዓል በሠላም አደረሳችሁ!አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤናና የብልጽግና እንዲሆን በራሴና በወላይታ ዞን አስተዳደር ስም መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

አገራችን ኢትዮጵያ የብዝሃ ብሔር፣ ኃይማኖት፣ ባህልና ቋንቋ ሀገር ስትሆን ሁሉም ብሔረሰቦች፣ ኃይማኖቶች፣ ባህሎችና ቋንቋዎች ለዘመናት ተቻችለው የሚኖሩባት የሁሉ እናት የሆነች ሀገር ነች።

ሆኖም የኢትዮጵያ ጠላት ሆኖ ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ሲያስተዳድራት የቆየው የጁንታው ቡድን በ"ከፋፍለህ ግዛ" የቅኝ ገዢዎች እሳቤ እርስ በርሳችን እንድንከፋፈልና እንድንናቆር አድርጎን ቆይቷል።

ከዛሬ አራት ዓመት በፊትም በህዝብ ማዕበል ሥልጣኑን ከለቀቀ በኋላ "እኔ የማልመራት ኢትዮጵያ ትፍረስ" በሚል አስተሳሰብ የአገራችን ምልክት የሆነውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ በመውጋት መንግስት ተገዶ ወደ ጦርነት እንዲገባ አድርጓል።

በዚህም ጦርነት ጁንታው ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከሆኑ ሀገራትና ኢትየጵያን እንደፈለግን ካላሾርናት ከሚሉ ምዕራባውያን ጋር በማበር በኢኮኖሚና በሚዲያ የከፈቱብን ወረራ በመመከት የሀገራችን አንድነትና ሉአላዊነትን በማስስከበር በፈተናዎች ውስጥ ሆነንም አኩሪ የልማት ድሎችን ማስመዝገብ ችለናል።

ያለጦርነት መኖር የማይችለው የትህነግ ጁንታው ቡድን ለዜጎች ደህንነት ሲባል የተደረገውን የተኩስ አቁም ስምምነት በማፍረስ የአለም አቀፍ የጦር ህግና ስምምነት በተፃረረ መልኩ ዕድሜያቸው ያልደረሱ የትግራይ ህፃናትን ከፊት በማሰለፍ ለሶስተኛ ጊዜ በአማራና በአፋር ክልሎች ጦርነት በመክፈት በርካታ ንፁኃን ዜጎች ሕይወታቸውን እንዲያጡ፣ ከቤት ንብረታቸውና ለዘመናት ከኖሩበት ቀዬአቸው እንዲፈናቀሉና ከፍተኛ መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ እያደረገ ይገኛል።

የዞናችን ህዝብ የመጀመሪያውን ወረራ ለመቀልበስ በሀብትና በገንዘብ ድጋፍና ለሠራዊቱ ስንቅ ዝግጅት በማድረግ እንደደገፈ ሁሉ አሁንም ለሶስተኛ ጊዜ በተቃጣብን ወረራ የዞኑ መንግስትና ህዝብ በገንዘብና በዓይነት ከ34 ሚሊየን ብር በላይ የሆነ ድጋፍ ለሠራዊቱ በማድረግ ደጀንነቱን እያረጋገጠ ይገኛል።

ለዚህም ለዞናችን አርሶ አደሮች፣ ለመንግስት ሠራተኞች፣ ለነጋዴዎች፣ ለባለሀብቱና ላስተባበሩ አመራሮች በራሴና በዞኑ አስተዳደር ስም ከፍ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ፤ ወደ ፊትም ጦርነቱ እስኪቀለበስ ድረስ ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነቴ የጸና ነው።

ሁሉም የልማት ዕቅዶች የሚሳኩት ሠላም ሲኖር ብቻ በመሆኑ ሁላችንም የአካባቢያችንን ሠላም ለመጠበቅ ዘብ ልንቆም ይገባል።

በአገራችን ላይ የተከፈተብን ጦርነት በግንባር ውጊያ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚ መስክ አንዳንድ አጋጣሚውን በመጠቀም በአቋራጭ ለመክበር በሚፈልጉ ስግብግብ ነጋዴዎች ዋጋ በመጨመርና ምርት አላግባብ በማከማቸት እንዲሁም በፕሮፓጋንዳው የማህበራዊ ሚዲያና የምዕራባውያን ሚዲያዎች በሚነዟቸው የሐሰት ወሬዎች ሳንሸበር አካባቢያችንን በትጋት ልንጠብቅ ይገባል።

የወላይታ ብሔር የብሔሩ መገለጫ የሆነው የዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓልም በዚህ ወር የሚከበር በመሆኑ ድርብ ደስታ የሚሰጥ ነው።

በበዓል የተጣላ የሚታረቅበት፣ የተራራቀ የሚቀርብበት፣ ያዘነ የሚፅናናበት በመሆኑ ሁሉም የዞናችንና የሀገራችን ሕዝብ የበዓሉን ዕሴቶች ተግባራዊ እንዲያደርግ ጥሪ አቀርባለሁ።

የምናከብረው በዓል ምሉዕ ደስታ የሚሰጠን የተቸገሩትን ስንረዳ፣ የተራቡትን ስናበላ፣ የታረዙትን ስናለብስ በመሆኑ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አረጋውያንንና የተቸገሩትን ለመርዳት ያሳየነውን በጎነት በበዓላቱም አጠናክረን ልንቀጥል ይገባል። በድጋሚም በዓሉ የሠላም የጤናና የብልጽግና እንዲሆን እመኛለሁ።አመሰግናለሁ!

08/09/2022
30/07/2022

የክልል አደረጃጀትን አስመልክቶ በዞን እና በልዩ ወረዳ ምክር ቤቶች እየተሰጠ ላለው በሳል ውሳኔ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ምስጋና አቀረበ

ላለፉት ዓመታት የህዝብ ጥያቄ ሆኖ ሲቀርብ የነበረው የክልል አደረጃጀት ጥያቄ በየደረጃው ያለው ህዝብ ውይይት በማድረግ በምክር ቤት ደረጃ ቀርቦ ውሳኔ እየተሰጠበት ይገኛል።

የአደረጃጀት ጥያቄው የህዝቡን የቆየ አብሮነት፣ወንድማማችነት፣መተሳሰብ፣ ብሎም ሌሎች ማህበራዊ መስተጋብሮችን በማይጎዳ መልኩ ተፈጻሚ እንዲሆን ፍላጎት መኖሩን የክልሉ መንግስት በአድናቆት ተመልክቶታል።

ከዚህ ቀደም የክልሉ መንግስት የህዝቡን ራስን በራስ የማስተዳደር ዝንባሌ በማክበር የአደረጃጀት ጥያቄዎች በህዝቦች መካከል ያለውን ብዝሃነት በማይጎዳ መልኩ እንዲከናወን ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል።

ሂደቱም በህዝቦች መካከል የነበረው የቆየ መልካም እሴት እንዲጎለብት፣ሰላማዊ ፍትሀዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ተፈጻሚ እንዲሆን መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶት ሲሰራ ቆይቷል።

መንግስት በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ቃል መግባቱ ይታወሳል።ቃል መግባት ብቻ ሳይሆን ለተፈጻሚነቱም በአንክሮ እየተመለከተ የህዝቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን እንደየ ቅደም ተከተላቸው ለመመለስ ጥረት በማድረግ ላይ ነው።

ከነዚህ የህዝብ ጥያቄዎች ውስጥ አንዱ እና ጎልቶ የወጣው የአደረጃጀት ጥያቄ መሆኑ እሙን ነው።

አሁን በየደረጃው ባሉ ምክር ቤቶች በሳል ውይይት በማካሔድ ክልሉ የሚታወቅበትን ህብረ ብሔራዊነት ለማስቀጠል ብሎም ከተናጠል ይልቅ በጋራ በመሆን መልማት እንደሚቻል የጋራ አቋም መያዙ በአብነት የሚጠቀስ ነው።

የመንግስት ዋነኛ ተግባሩ የህዝብ ፍላጎት በመረዳት ምላሽ መስጠት ነው።በእርግጥ ሁሉም ችግሮቻችን እና ፍላጎቶቻችንን በአንድ ጀንበር ይፈታሉ ማለት አይደለም እንደ ሀገር ያሉብን ችግሮች አያሌ ናቸው።በሌላ በኩል ኢኮኖሚያችን ሲያድግ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮቻችንን ለመፍታት የሚያግደን ነገር አይኖርም።

የክልል አደረጃጀት ሂደቱ ውጤታማ እንዲሆን የክልሉ መንግስት ከፌደራል መንግስት ጋር በጋራ በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል።

በፈተና ውስጥ እያለፍን የጋራ ችግሮቻችንን በጋራ መፍታት ይኖርብናል።በመሆኑም የህዝባችንን የክልል አደረጃጀት ጥያቄ በማስመልከት በምክር ቤቶች ደረጃ ውይይት በማካሔድ የቀረበውን አማራጭ ፍላጎት አስመልክቶ የክልሉ መንግስት በድጋሚ ምስጋና ማቅረብ ይወዳል ።

የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት።
ሐምሌ 23/2014

19/07/2022
08/07/2022

መልካምን መውደድ፣ ክፉ ተግባርን ማውገዝ የሁሉም ሃይማኖቶች እሳቤና ዕሴት ነው፦ አቶ ዮሐንስ በየነ

እንኳን ለ1443ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-አድሐ ዐረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

በፆም፣ በፀሎትና ክፉ ምግባርን በሚኮንን ሀይማኖታዊ ሥርዓት የሚከናወነው የአረፋና የሀጅ ሥርዓት ከእስልምና መሠረታዊ ምሶሶዎች መካከል አንዱ ሲሆን በእስልምና ሃይማኖት ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው ታላቅ በዓል ነው፡፡

በእስልምና እምነት አስተምሮ ነቢዩ ኢብራሂም በፈጣሪያቸው ትዕዛዝ አንድ ልጃቸውን እስማኤልን ለመስዋዕት አቅርበው ለፈጣሪያቸው ትዕዛዝ ከመገዛታቸው የተነሳ በልጃቸው ምትክ የበግ መስዋዕትነት የተተካላቸው መሆኑን የምናስታውስበት ዕለት በመሆኑ ሁላችንም ቂም በቀልን በማስወገድ ለአንድ ዓላማ ልንቆም ያስፈልጋል፡፡

ሁለንተናዊ ለውጥና ልማት ለማስቀጠልም ሰላም ዋነኛው በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ለሰላም ዘብ በመቆምና በመፀለይ በይቅርታ ወደ ፈጣሪው መመለስ ግድ የሆነበት ወቅት ላይ ደርሰናል፡፡

እንደ አንድ ሕግ አክባሪ ዜጋ መልካም ተግባርን የመውደድ እና ክፋትን የማውገዝ ኃላፊነት እንዳለብን ባለመዘንጋት የሀገራችንን ሁለንተናዊ ለውጥ በመደመር ለማስቀጠል መላው የዞኑ ህዝብ የበኩሉን ሁሉ እንዲያደርግም ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

የእኛ ዝምታ ሌሎች ሕገ-ወጦችን የጎበዝ አለቃ እንዳያደርጋቸው መንቃት የሚገባን ጊዜ ላይ መሆናችንንም በአክብሮት ላስታውሳችሁ እወዳለሁ፡፡

መላው በዞናችን የሚገኙ ሙስሊሞች ከመቼውም ጊዜ በላይ እርስ በርስ በመከባበር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ለከተማችንና ለሀገራችን ሰላም ዘብ በመቆም በዓሉን እንድታከብሩ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

አረፋ በዓል ደግነትንና ቸርነትን በመስጠትና በመለገስ የምናሳይበት በዓል በመሆኑ የተቸገሩና አንዳች ጥሪት የሌላቸው ወገኖቻችንን በመርዳት ከተቀረው ወገኖቻችን ጋር በዓሉን በጋራ እንድናከብርም ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

በመጨረሻም በዓሉ አብሮነታችን የሚፈካበት፣ የሚያብብበት፣ ሰላምና ሀገራዊ አንድነታችን ስር የሚሰድድበት የበረከት በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ፡፡

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!

ኢድ ሙባረክ።

ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ

08/07/2022

ለመላሙ የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ እንኳን ለ1443ኛዉ ዓመተ ሂጅራ ኢድ_ አልአደሃ የአረፋ በዓል አደረሳችሁ!!አደረሰን!

በዓሉ የሠላምና የበረከት እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ።

አገራችን ኢትዮጵያ የሃይማኖትና የእምነት ብዝሃነቶች የሚገኙባትና በማህበራዊ እሴት የታደለች ሀገር ናት። ህዝቦቿም በመንፈሳዊና በሞራላዊ ስብዕና የተገነቡ ናቸዉ።

ኢትዮጵያዊያን ብዝሃ ሃይማኖት ተከታይ መሆናቸዉ እንደተጠበቀ ሆኖ በአብሮነትና በመቻቻል መንፈስ የመኖር ልምዳቸዉ እጅግ አስደናቂ ነዉ።

ልዩነትን ያከበረ ጠንካራ ማህበራዊ መስተጋብር የገነቡ ናቸዉ ኢትዮጵያዊያን።

ይህንን የአብሮነትና የመተባበር መንፈስ ማጠናከር ለሠላማችን ዘላቂነት፣ ለብልጽግናዉ ጉዞ ቀጣይነት እንዲሁም የዉስጥና የዉጪ ጠላቶቻችንን ጥቃት በተባበረ ክንድ ለመመከት ወሳኝ ነዉ።

በመሆኑም ሙስሊሙ ህብረተሰብ የእርስ በርስ አንድነቱን ከማጠናከር ባሻገር እንደሀገር እየተደረገ ባለዉ የሠላም፣ የልማትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንቅስቃሴ የድርሻዉን ከፍተኛ ሚና አጠናክሮ እንዲያስቀጥል በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ ።

ኢትዮጵያን ከጀመረችዉ የለዉጥ ጉዞ ለማሰናከል ደፋ ቀና የሚሉ የዉስጥና የዉጪ የጥፋት ኃይሎችን ሴራ ለማክሸፍ የህዝቦቻችን አንድነትና ፅናት እጅግ መሠረታዊ አስፈላጊ ጉዳይ ነዉ። ስለሆነም አንድነታችንን እና ፅናታችንን ከፍ ማድረግ አለብን።

ኢትዮጵያ የጀመረችዉ የለውጥ ጉዞ ያልተመቻቸው እንዲሁም ያልተገባ ጥቅም የሚሹ የዉስጥና የዉጪ ኃይሎች አንድነታችንን እና ፅናታችንን ለማናጋት በከፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ተገንዝበን የተቃጣብንን አደጋ ለመቀልበስ በጋራ መቆም አለብን።

ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለአረፋዉ በዓል በሠላም አደረሳችሁ ፣ በዓሉ የደስታ፣ የፍቅርና የሠላም እንዲሆንላችሁ በድጋሚ እመኛለሁ ።
አመሠግናለሁ !
ጥላሁን ከበደ
በብልጽግና ፓርቲ
የደቡብ ብሔሮች ፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ

08/07/2022

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው 1ሺ 443ኛውን የኢድ አል አድሀ /አረፋ/በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል

የኢድ አል አድሀ(የአረፋ ) በዓል ህዝበ ሙስሊሙ በድምቀት ከሚያከብራቸው በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ በምዕመናን ዘንድ ትልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን የአንድነት እና የአብሮነት እሴቶቻችን በጉልህ የሚንጸባረቁበት በዓል ነው።

የተራበን ማብላት፣ የተቸገረን መርዳት እንዲሁም የታረዘን ማልበስ ደግሞ የአረፋ በዓል ልዩ መገለጫ ነው። ተራርቀው የቆዩ የቤተሰብ አባላት በናፍቆት ተገናኝተው በጋራ ጉዳዮቻቸው ዙሪያ ለመምከርም እድል የሚፈጥር ነው።

ሙስሊሙ ማህበረሰብም እንደ ከዚህ ቀደሙ የጋራ አንድነቱን በማጠናከር እምነቱ በሚያዘው መሰረት አቅመ ደካሞችን በመርዳት ያለውን በማካፈል በዓሉን ማሳለፍ ይኖርበታል።
በሌላ በኩል በዓልን በማይመች ሁኔታ ላይ ለሚያሳልፉ ወገኖቻችንን ማዕድ በማጋራት አለኝታችንን ማሳየት ይጠበቅብናል።

እንደ ሀገር የገጠመንን አያሌ ፈተናዎች ተሻግረን የሀገራችንን ክብር ከፍ ለማድረግ እርስ በእርስ መተሳሰብ እና መደጋገፍ ይኖርብናል።

በሀገራችን ላይ የሚሰነዘሩ የውስጥና የውጭ ጥቃቶችን መመከት የምንችለው አንድነታችንን ማጠናከር ስንችል ነው።
ጠላት ኢትዮጵያን ለማፍረስ አለኝ የሚለውን አማራጭ ሁሉ ተጠቅሟል እየተጠቀመም ይገኛል። ኢኮኖሚያችን እንዲዛባ ፣በብሔር እና በሀይማኖት እንድንጋጭ ህዝባችን በኑሮ ውድነት እንዲማረር እና መሰል ችግሮችን በመፍጠር ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲማረር ጥረት በማድረግ ላይ ነው።

ነገር ግን ይህንን የጠላት ሴራ በህዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ሀይላችን ብርቱ ጥረት እና መስዋዕትነት እያከሸፍን እንገኛለን።

የውስጥ እና የውጭ የኢትዮጵያ ጠላቶች በህዝባችን ላይ የከፈቱት መጠነ ሰፉ የሸፍጥ ሴራ በርካቶችን ለእልቂት ዳርጓል። ዜጎች በሰላም በሚኖሩበት አካባቢ ተገድለዋል። ከህጻናት እስከ አዋቂዎች ዘግናኝ ጭፍጨፋ ተፈጽሞባቸዋል።

የለውጡ መንግስት የህዝባችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት ለማደናቀፍ ያለሙ ሀይሎች የሀገራችን ብሎም የክልላችንን ህዝብ ለስቃይ እና መከራ የመዳረግ ሴራ በተባበረ ክንዳችን እየመከትን ሰላማችንን አስጠብቀን ወደ ፊት የምናደርገውን ጉዞ እንቀጥላለን።

በአሁኑ ሰዓት የተዳከመውን ኢኮኖሚያችን እንዲያንሰራራ መስራት በሌላ በኩል ደግሞ የተቃጣብንን የጠላት እኩይ ሴራ እየመከትን የበለጸገች ሀገር ለመፍጠር መትጋት ይኖርብናል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺ 443 ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በሰላም አደረሳችሁ።በዓሉ የሰላም፣የጤና የመተሳሰብ እና የአንድነት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ኢድ ሙባረክ!!

08/07/2022

ለ1ሺ 443ኛውን የኢድ አል አድሀ /አረፋ/በዓልን በማስመልከት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አክሊሉ ለማ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የኢድ አል አድሀ(የአረፋ ) በዓል ህዝበ ሙስሊሙ በድምቀት ከሚያከብራቸው በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ በምዕመናን ዘንድ ትልቅ ትርጉም ያለው ሲሆን የአንድነት እና የአብሮነት እሴቶቻችን በጉልህ የሚንጸባረቁበት በዓል ነው።

የተራበን ማብላት፣ የተቸገረን መርዳት እንዲሁም የታረዘን ማልበስ ደግሞ የአረፋ በዓል ልዩ መገለጫ ነው። ተራርቀው የቆዩ የቤተሰብ አባላት በናፍቆት ተገናኝተው በጋራ ጉዳዮቻቸው ዙሪያ ለመምከርም እድል የሚፈጥር ነው።

ሙስሊሙ ማህበረሰብም እንደ ከዚህ ቀደሙ የጋራ አንድነቱን በማጠናከር እምነቱ በሚያዘው መሰረት አቅመ ደካሞችን በመርዳት ያለውን በማካፈል በዓሉን ማሳለፍ ይኖርበታል።
በሌላ በኩል በዓልን በማይመች ሁኔታ ላይ ለሚያሳልፉ ወገኖቻችንን ማዕድ በማጋራት አለኝታችንን ማሳየት ይጠበቅብናል።

እንደ ሀገር የገጠመንን አያሌ ፈተናዎች ተሻግረን የሀገራችንን ክብር ከፍ ለማድረግ እርስ በእርስ መተሳሰብ እና መደጋገፍ ይኖርብናል።

በሀገራችን ላይ የሚሰነዘሩ የውስጥና የውጭ ጥቃቶችን መመከት የምንችለው አንድነታችንን ማጠናከር ስንችል ነው።
ጠላት ኢትዮጵያን ለማፍረስ አለኝ የሚለውን አማራጭ ሁሉ ተጠቅሟል እየተጠቀመም ይገኛል። ኢኮኖሚያችን እንዲዛባ ፣በብሔር እና በሀይማኖት እንድንጋጭ ህዝባችን በኑሮ ውድነት እንዲማረር እና መሰል ችግሮችን በመፍጠር ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲማረር ጥረት በማድረግ ላይ ነው።

ነገር ግን ይህንን የጠላት ሴራ በህዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ሀይላችን ብርቱ ጥረት እና መስዋዕትነት እያከሸፍን እንገኛለን።

የውስጥ እና የውጭ የኢትዮጵያ ጠላቶች በህዝባችን ላይ የከፈቱት መጠነ ሰፉ የሸፍጥ ሴራ በርካቶችን ለእልቂት ዳርጓል። ዜጎች በሰላም በሚኖሩበት አካባቢ ተገድለዋል። ከህጻናት እስከ አዋቂዎች ዘግናኝ ጭፍጨፋ ተፈጽሞባቸዋል።

የለውጡ መንግስት የህዝባችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት ለማደናቀፍ ያለሙ ሀይሎች የሀገራችን ብሎም የክልላችንን ህዝብ ለስቃይ እና መከራ የመዳረግ ሴራ በተባበረ ክንዳችን እየመከትን ሰላማችንን አስጠብቀን ወደ ፊት የምናደርገውን ጉዞ እንቀጥላለን።

በአሁኑ ሰዓት የተዳከመውን ኢኮኖሚያችን እንዲያንሰራራ መስራት በሌላ በኩል ደግሞ የተቃጣብንን የጠላት እኩይ ሴራ እየመከትን የበለጸገች ሀገር ለመፍጠር መትጋት ይኖርብናል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺ 443 ኛው የኢድ አል አድሃ አረፋ በአል በሰላም አደረሳችሁ።በዓሉ የሰላም፣የጤና የመተሳሰብ እና የአንድነት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ኢድ ሙባረክ!!

14/06/2022

"የተሰጠንን ጊዜ በአግባቡ ካልተጠቀምን ጊዜ የሰጠን አካል ይነጥቀናል፤ ክረምት በጋን ሊተካ እንደማይችል፤ ጨለማም ብርሃንን መተካት እንደማይችል አውቀን በተሰጠን ጊዜ ልንጠቀምበት ይገባል!"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር)

14/06/2022

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄ ከሰጧቸው ምላሾች በጥቂቱ፡- /የቀጠለ/

 ቤተሰብ አካባቢውን በአግባቡ ሳያጸዳ አገር አጸዳለሁ ማለት ዘበት ነው፤

 "ኢትዮጵያ አትፈርስም፤ አልፈረሰችም፡፡ ኢትዮጵያ ከመፍረስ አደጋ ወጥታ የብልፅግና መሠረቷን እየጣለች ነው!"

 "እስካሁን እያጋጠሙን የነበሩ ፈተናና ችግሮች ተቋማት ሳንፈጥር የገጠሙን ናቸው፤አሁን ላይ ችግሮችን መቋቋም የሚያስችሉ ተቋማትን ለመፍጠር አስችሎናል፡፡ ችግሮች ኢትዮጵያን በአስተማማኝ ቁመና ላይ እንድናደርስ እድል የሚፈጥሩ ናቸው፡፡"

 የሚሰራ ሰው አይለምንም፣ያካፍላል እንጂ ፤የሚሰራ ሰው አያባክንም እንዴት ደክሞ እንዳመጣው ያውቀዋልና፤

 በወሬ ችግር እንጂ ውጤት አይመጣም፤ምድር ከሰራህም ታከብርሃለች፤

 ለውጥ የሚመጣው በስራ ብቻ ነው፤ውጤት ለማምጣት ሰባት ቀን ነው የምንሰራው፤

 '...ያለፉት አራት ዓመታት ከበድ ከበድ ያሉ ፈተናዎች የነበሩባቸዉ ናቸዉ።...'

 ወንዶች ሴቶችን አያከብሩም፤ዜጎች ህግን አያከብሩም፤

14/06/2022

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄ ከሰጧቸው ምላሾች በጥቂቱ፡-

 " #ኢትዮጵያ አትፈርስም!! አትፈርስም ብቻ ሳይሆን የብልፅግና መሰረቶቿን እየጣለች ነው።"

 አገር የሚገነባውም የሚፈርሰውም ጭንቅላት ውስጥ ነው፣የፈረሰ ጭንቅላት አገር ሊገነባ አይችልም፣የተገነባ ጭንቅላት አገር ሊያፈርስ አይችልም፤

 ሰው ዛፍ ነው፤አገር ጫካ ነው፤አገር የጫካዎች ድምር ውጤት ናት፣

 በየተቋማቱ የሐሳብ ዘር እየተተከለ ስለመሆኑ ብዙ ጅማሮዎች አሉን፤

 በሀሳብ ላይ ስንግባባና ሀሳብ ስናደረጅ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለመሸጋገር ዕድል እናገኛለን፤

 ጊዜ ይሰጥሃል እንጂ አትገዛውም፤
 የተሰጠንን ጊዜ በአግባቡ ካልተጠቀመን ጊዜ የሰጠን አካል ይነጥቀናል፤ክረምት በጋን ሊተካ እንደማይችል፣ጨለማም ብርሃንን መተካት እንደማይችል አውቀን በተሰጠን ጊዜ ልንጠቀምበት ይገባል፤

14/06/2022

'...ያለፉት አራት ዓመታት ከባድ ከባድ ያሉ ፈተናዎች የነበሩባቸዉ ናቸዉ።...'_
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አሕመድ

14/06/2022

" #ኢትዮጵያ አትፈርስም!! አትፈርስም ብቻ ሳይሆን የብልፅግና መሰረቶቿን እየጣለች ነው።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ያሬድ ያሲን - Yared Yasin posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share