ነፃው ፕሬስ - Free Press

  • Home
  • ነፃው ፕሬስ - Free Press

ነፃው ፕሬስ  - Free Press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ነፃው ፕሬስ - Free Press, Media/News Company, .

ዛሬ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በነበረ ተኩስ የፋኖ አመራር ናሁሰናይ ተገደለ የተኩሱ መነሻ የጎንደር ፋኖ መሪ የነበረው ናሁሰናይ በመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች በመያዙ ምክንያት ነው ተብሏል።...
12/04/2024

ዛሬ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በነበረ ተኩስ የፋኖ አመራር ናሁሰናይ ተገደለ

የተኩሱ መነሻ የጎንደር ፋኖ መሪ የነበረው ናሁሰናይ በመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች በመያዙ ምክንያት ነው ተብሏል።

ናሁሰናይን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ሊያውለው ሲሞክር ከፀጥታ ኃይሎች ጋር የተኩስ ልውውጥ አድርጓል ያሉ ሲሆን አብረውት ከነበሩት ሁለት ሰዎች ውስጥ አንዱ ወዲያውኑ የሞተ ሲሆን ናሁሰናይ ቆስሎ ቢያዝም ህይወቱ አልፏል ተብሏል። አንደኛው ምንም ሳይሆን ተይዟል ተብሏል።

ከፀጥታ ኃይሎች በኩል አንድ የሞተ ሲሆን የቆሰሉም መኖራቸውን ነው የመረጃ ምንጮቹ የገለፁት።

ይህን ተከትሎ ከቦሌ snap plaza እስከ ቦሌ መድሃኒያለም ያለው መንገድ ዝግ ተደርጓል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ መግለጫ የሚከተለው ነው 👇
"
የጽንፈኛው ቡድን አባላት የሆኑት ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ የተባሉት የጽንፈኛው ቡድን አባላት በአዲስ አበባ ከተማ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ተልዕኮ ይዘው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የጸጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል ደርሰዉበት የሽብር ተግባራቸውን ሳይፈፅሙ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ ጽንፈኞቸ እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆናቸዉ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ አይሱዙ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ከፖሊስ አባላት ጋር በተደረገ የተኩስ ልዉዉጥ የጽንፈኛው ቡድን መሪ ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፡፡

አቤኔዘር ጋሻው አባት የተባለው የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ጽንፈኞቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገ እንቅስቃሴ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ሲቆስሉ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ ፅንፈኞቹ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበር በማለታቸው በፅንፈኛው አባላት ተገድለዋል፡፡

አቶ እንደሻው ሲያሽከርክሯት የነበረቸው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 80457 በጥይት ጉዳት እንደረሰባት አዲስ አበባ ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል ፡፡ በቀጣይ ፖሊስ የደረሰበትን ዝርዝር መረጃ እንደሚገልፅ አስታውቋል፡፡

ምንጭ:-ኢትዮ ቲዩብ

በሀገር  ውስጥ እና በውጭ ዜናዎች ትንታኔዎቹ  አድናቆትን ያተረፈው ጋዜጠኛ አባቱ መረቀ የራሱን የዮቲዮብ ቻናል ይዞ መጥቷል !' አባቱ መረቀ ኦፊሺያል ' መጠሪያው ነው።ወቅታዊ ፣ ትኩስ ፣ ...
12/04/2024

በሀገር ውስጥ እና በውጭ ዜናዎች ትንታኔዎቹ አድናቆትን ያተረፈው ጋዜጠኛ አባቱ መረቀ የራሱን የዮቲዮብ ቻናል ይዞ መጥቷል !

' አባቱ መረቀ ኦፊሺያል ' መጠሪያው ነው።

ወቅታዊ ፣ ትኩስ ፣ ሚዛናዊና ትክክለኛ ጉዳዮችን በትንታኔ ይዳሰሳል።

ቻናሉን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

ወቅታዊ ፤ትኩስ፤ ሚዛናዊና ትክክለኛ መረጃን በማድረስ የህዝብ ድምጽ ሚዲያ ነዉ

ሲታሰር ወደኔ ሲፈታ ወደሱ
08/04/2024

ሲታሰር ወደኔ ሲፈታ ወደሱ

https://www.facebook.com/share/tWrqgefwkyhJRJsq/?mibextid=oFDknk
05/04/2024

https://www.facebook.com/share/tWrqgefwkyhJRJsq/?mibextid=oFDknk

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ "ብሬን ወስደውብኛል" በሚል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ደጃፍ ላይ የለጠፈው የ'ተማሪ' ፎቶዎች በፖስተር።
🔴- ይህን ማድረግ (የይፈለጋሉ ዝርዝር ማውጣት ) የነበረበት ፌዴራል ፖሊስ ወይስ ባንኩ?

ስለፒያሳ ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ምን ጻፉ?የአዲስ አበባ 'ልማት ኮሪዶር' ፕሮጀክትን በተመለከተ ዘ ጋርዲያን የተነሺዎችን ቅሬታ የያዘ መረጃ አጋርቷል "ተነሺዎች ለዘመናት ከኖሩበት ቤት እንዲወ...
05/04/2024

ስለፒያሳ ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ምን ጻፉ?

የአዲስ አበባ 'ልማት ኮሪዶር' ፕሮጀክትን በተመለከተ ዘ ጋርዲያን የተነሺዎችን ቅሬታ የያዘ መረጃ አጋርቷል

"ተነሺዎች ለዘመናት ከኖሩበት ቤት እንዲወጡ አምስት ቀን ብቻ እንደተሰጣቸው፣ ከዛም ከሶስት ቀን በኋላ ውሀ ሆን ተብሎ እንደተቋረጠባቸው እና ንብረታቸውን በማውጣት ትርምስ ውስጥ ዝርፊያ እና ውድመት እንደደረሰባቸው ለሚድያው ተናግረዋል"።

ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ከስር ያለውን ሊንክ ተጫኑ

Ethiopia’s push to attract tourism and investment has seen the demolition of a historic district in the capital, with people’s homes and livelihoods destroyed

የዛሬው ምሽት የአርቲስት መቅደስ ጸጋዬ ምሽት ነው ማለት ይችላል።ለዘመናት ያለመችውን እውን አድርጋለች።አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ በ1 ቢሊየን ብር ወጪ የምታስገነባው የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል ...
05/04/2024

የዛሬው ምሽት የአርቲስት መቅደስ ጸጋዬ ምሽት ነው ማለት ይችላል።

ለዘመናት ያለመችውን እውን አድርጋለች።

አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ በ1 ቢሊየን ብር ወጪ የምታስገነባው የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል የመክፈቻ መርሐግብር ተካሂዷል።

አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ በ1 ቢሊየን ብር ወጪ የምታስገነባው የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል በዛሬው እለት የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት አካላትና እንግዶች በተገኙበት የመክፈቻ ሥርዓቱ ነው የተካሄደው።

መቅደስ የልጆች አድማስን ለማቋቋም ሃሳቡ የተፀነሰው ከ6 ዓመታት በፊት እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን፤ ሙሉ በሙሉ አገር በቀል የሆነና በአርቲስት መቅደስ ፀጋዬ የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው::

ድርጅቱን ሙሉ ለሙሉ በመገንባትና በሙሉ አቅሙ ስራውን እንዲጀምር ለማድረግ እስከ አንድ ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን ዛሬ መጋቢት 26/2016 ዓ.ም የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር ተካኺዷል

በአጠቃላይ በሃያ እንድ ሺ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ተቋም ነውም ተብሏል።

ዛሬ በተካሄደው ገቢ የማሰባሰብና ወደ ስራ የመግባት መርሐግብር ላይ ከፍተኛ የሀገራችን መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ባለሃብቶች፣ የኤምባሲ ተወካዬች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሐሳቡን የሚደግፉና ቀና ልብ ያላቸው ግለሰቦችም ተሳትፈዋል።

ይህ ድርጅት የመጀመሪያ ተቋሙን የሚገነባውና ስራውን የሚጀምረው በአዲስ አበባ ሲሆን ቀስ በቀስም ወደ ክልሎች ቅርንጫፎቹን የሚያሰፋ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር 200 ህፃናትን ከመላው ኢትዮጵያ ተቀብሎ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሲገባ ደግሞ 1000 ህፃናትን የመቀበል አቅም የሚኖረው እንደሚሆን ተነግሯል

ድርጅቱ በዋናነት ልዩ ትኩረት እና ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው ወላጅ አልባ ህፃናት ልጆች አስፈላጊውንና ሁሉን አቀፍ እንክብካቤ በመስጠት በቀጣይ የሕይወት ጉዟቸው ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ የበጎ አድራጎት ድርጅት ወይም ማዕከል እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ማእከሉን በአሁኑ ሰአት በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ያሉና በሀገራችን ተፅእኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦች በቦርድ አባልነት እንደሚመሩትም ተነግሯል፡፡ .

በማዕከሉ ውስጥ ለሚቆዩ ልጆች ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያ፣ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶችን ከመስጠትና፣ የአካል ብቃት ማጎልመሻ ከማደራጀት ባሻገር፤ የማኅበራዊ ሕይወትና የአእምሮ ማበልፀጊያ ስልጠናዎችን በመስጠት ሙሉ ጤንነታቸው የተረጋገጠ፣ በአካላዊ እድገታቸው የበቁ፣ በሥነ ልቦና፣ በግልና በማሕበራዊ ሕይወታቸው ጠንካራ የሆኑ እንዲሁም በአእምሮአዊ የፈጠራ ችሎታቸው የተደነቁ እና በዕውቀት የዳበሩ ሆነው፤ የመጪው ጊዜ ብሩህ እና ስኬታማ ዜጎችን እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል።

ምንጭ ፦በሶደሬ ዜና እና በ Zena 24 ሪፖርተር

05/04/2024

የደንብ ልብስ የለበሰ ፌዴራል ፣ መከላከያ እና ፖሊስ ሁሉ መፈራት ሳይሆን መከበር እና መወደድ እንዳለበት የሚያሳይ ግሩም ሰርቶ ማሳያ

ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ሲሰራጭ የነበረው በወሎ ዩኒቨርስቲ ተቀጥራ ትሰራ የነበረችውና ኋላ ከስራ ወጥታ ወደ ልመና የገባችው ትዝታ ገረመው አዲስ ስራ አግኝታ የቅጥር ውል ፈርማለች ተ...
03/04/2024

ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ሲሰራጭ የነበረው በወሎ ዩኒቨርስቲ ተቀጥራ ትሰራ የነበረችውና ኋላ ከስራ ወጥታ ወደ ልመና የገባችው ትዝታ ገረመው አዲስ ስራ አግኝታ የቅጥር ውል ፈርማለች ተባለ።
ትዝታ ገረመው አዲሱን ስራዋን በኢትዮጲያን ቢዝነስ ሪቪዊ (Ethiopian Business Review) የመረጃ ጥንቅር እና ምርምር ኦፊሰር (Data Researcher) ሆና ሚያዝያ 1 ሥራ ለመጀመር የቅጥር ደብዳቤ ዛሬ ተቀብላለች ተብሏል። ትዝታ ሁለተኛ ዲግሪዋን ጨርሳ ለሶስተኛ ዲግሪ እየተማረች መሆኑ ይታወቃል ።

ምንጭ፦ Seber Zena

https
03/04/2024

https

አይ ኤም ኤፍ ከኢትዮጵያ ጋር ሳይስማማ ቀረ
__________________

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር የብድር ስምምነት ላይ ሳይደርስ መቅረቱ ተነገረ።

የድርጅቱ ተወካዮች አዲስ አበባ መጥተው በብድር ጉዳይ ውይይት ሲያደርጉ የቆዩት ኢትዮጵያ አገር በቀል ኢኮኖሚያዊ ዕቅዷን ለመተግበር የሚያስችላትን የገንዘብ ድጋፍ ከተቋሙ መጠየቋን ተከትሎ እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል ።

የአዲስ አበባው ወይም የማዘጋጃው አሊያም የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው አዲስ ቲቪ በጧት ይህቺን ቀጥታ ሥርጭት አሳይቶ ወዲያው አቋርጦታል ። አቤት ጭንቀት !!! ኧረ ፖለቲካ እንዲህ አይሰራም ...
02/04/2024

የአዲስ አበባው ወይም የማዘጋጃው አሊያም የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው አዲስ ቲቪ በጧት ይህቺን ቀጥታ ሥርጭት አሳይቶ ወዲያው አቋርጦታል ። አቤት ጭንቀት !!! ኧረ ፖለቲካ እንዲህ አይሰራም ።
ለመሆኑ የድጋፍ ስልፉ ኦሮሚያን ብቻ መያዙና ዜናው መሠራቱ ምን እያመላከተን ነው???????

ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር የተደረገው መድረክ የከሸፈ ነው አሉ::" መድረኩ ጠቃሚ ነው ብለን ስላላሰብን ፓርቲያችን አልተገኘም "       ፕ/ር መረራ ጉዲና   ( ...
01/04/2024

ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር የተደረገው መድረክ የከሸፈ ነው አሉ::
" መድረኩ ጠቃሚ ነው ብለን ስላላሰብን ፓርቲያችን አልተገኘም "
ፕ/ር መረራ ጉዲና

( ዮናስ ወልደሰንበት ተቃዋሚዎችን አነጋግሮ እንደጻፈው)

ዛሬ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ከተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ጋር ጠቃሚ ውይይት ማድረጋቸውን በፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስታውቀዋል ።

ይሁን እንጁ የሰበር ዜና ዝግጅት ክፍል ያነጋገራቸው የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ጠቅላይ ሚንስትሩ ያስራጩት መረጃ ሀሰት ነው ብለዋል ።

በመድረኩ ከተገኙት ፓርቲዎች አንዱ የሆነው የመኢአድ አመራር ለስበር ዜና ዝግጅት ክፍል እንደገለፁት መድረኩ የሀገሪቱ አንገብጋቢ ጉዳዮች ያልተነሳበት ፣ እንደ ካድሬ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ውዳሴና አድናቆት ሲጎርፍ የዋለበት ነው " ሲሉ ተናግረዋል ።

እኚህ ፖለቲከኛ " እንደ ግሌም ፣ ሆነ እንደ ፓርቲ በቡድን በዚያ የከሸፈ መድረክ ላይ መገኘታችን ቆጭቶናል " ብለዋል ።

ጠቅላይ ሚንስትሩ ጠንካራና ሞጋች ጥያቄ ሊያቀርቡ ይችላሉ ብለው ላሰቧቸው ፓርቲዎች እድል እንዳልሰጧቸውም ሌሎች ተሳታፊዎች ለሰበር ዜና ተናግረዋል ።

አንድ የኢህአፓ አባል " በምርጫ ቢሸነፉ ስልጣን ይለቃሉ ወይ " ብለው ላቀረቡት ጥያቄ ፣ ጠቅላይ ሚንስትሩ ለጥያቄው ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ፣ የኢህአፓን የኋላ ታሪክ መሰረት አድርገው ፓርቲውን እንደወነጀሉና እንዳንቋሸሹም ሰበር ዜና ሰምታለች ።

በሌላ በኩል የኦፌኮ ፓርቲ ሊቀመንበር ፕ/ር መረራ ጉዲና " በመድረኩ ላይ እንድንገኝ ጥሪ ቢቀርብልንም ጠቃሚ አይደለም በሚል አልተገኘንም " ሲሉ ለሰበር ዜና ዝግጅት ክፍል ገልፀዋል ።

* * *
ዮናስ ወ/ሰንበት / ሰበር ዜና /

እነዚህን ጋዜጦች ያነብ የነበረ ማነው? ዛሬ በእጃቸው ጋዜጣ እንኳን ነክተው የማያውቁ ሰዎች ዜና በፌስቡክ እና በዩቲዩብ እየቸረቸሩልን ነው።
31/03/2024

እነዚህን ጋዜጦች ያነብ የነበረ ማነው? ዛሬ በእጃቸው ጋዜጣ እንኳን ነክተው የማያውቁ ሰዎች ዜና በፌስቡክ እና በዩቲዩብ እየቸረቸሩልን ነው።

በብዙዎች ተስፋ ተጥሎበት የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አለልኝ አዘነ በድንገት አረፈትልቅ ቦታ ላይ ይደርሳል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አለ...
28/03/2024

በብዙዎች ተስፋ ተጥሎበት የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አለልኝ አዘነ በድንገት አረፈ

ትልቅ ቦታ ላይ ይደርሳል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አለልኝ አዘነ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ቢቢሲ ከተጫዋቹ የቅርብ ጓደኞች ማረጋገጥ እንደቻለው ተጫዋቹ ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ.ም. ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፌስቡክ ገፁ ባወጣው መግለጫ በተጫዋቹ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገልጧል።

አርባ ምንጭ ከተማ በተለምዶ ልማት ሰፈር የሚባለው ሰፈር ተወልዶ ያደገው አለልኝ አዘነ፣ በብሔራዊ ቡድኑ በኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ እጀግ ተስፋ ከተጣለባቸው ተጫዋቾች መካከል ነበር።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተጫዋቹ በምን ምክንያት በድንገት እንዳረፈ ያለው ነገር የለም።

“አለልኝ አዘነ በተደጋጋሚ ለብሔራዊ ቡድናችን ተመርጦ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ እና በአሁኑ ወቅት በእግር ኳሳችን ላይ ምርጥ አቋማቸውን እያሳዩ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል የሚጠቀስ ተጫዋች ነበር” ይላል የፌዴሬሽኑ መግለጫ።

የባሕር ዳር ከተማ እግር ኳስ ክለብ እንደገለጠው አለለኝ አዘነ በጉዳት ምክንያት ከቡድኑ ተነጥሎ ለእረፍት ነበር ወደ አርባምንጭ ያቀናው።

የባሕር ዳር ከተማ ቡድን መሪ ሄኖክ ሀብቴ የክለቡ አመራሮች እና ተጫዋቾች በአለልኝ ድንገተኛ ሞት ማዘናቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“በጉዳት ምክንያት እረፍት ስለሚያስፈልገው ነው ወደ አርባ ምንጭ የሄደው። ሰኞ [መጋቢት 16/2016] አዲስ አበባ መጥቶ ሕክምና አድርጎ ነው የተመለሰው። ከዚያ በኋላ ነው ሌሊት ተደውሎልን ሞቱን የተረዳነው” ይላሉ።

የቡድን መሪው አክለው የባሕር ዳር ተጫዋቾች እና አመራሮች በተጫዋቹ ሕልፈት ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ መሆናቸውን ለቢቢሲ ገልጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚዬረ ሊግ አክሲዮን ማኅበር፣ የአርባ ምንጭ ከነማ እግር ኳስ ክለብ፣ የባሕል እና ስፖርት ሚኒስቴር እና ሌሎችም በተጫዋቹ ሞት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።

የአለልኝን ብቃት የሚያደንቁት በርካታ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችም በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ የተጫዋቹ ሞት ለአገሪቱ እግር ኳስ ሊያበረክት የሚችለውን አስተዋጽኦ ያሳጣ ነው በማለት ሐዘናቸውን እየገለጹ ነው።

አለልኝ ማን ነበር?

አርባ ምንጭ ተወልዶ ያደገው አለልኝ አዘነ ላለፉት ሁለት ዓመታት ለባሕር ዳር ከተማ ተጫውቷል።

የተከላካይ አማካዩ አለልኝ ከባሕር ዳር ከተማ በፊት ለሐዋሳ ከተማ እና ለመቀለ 70 እንደርታ ተጫውቷል።

በቅርቡ በኦርቶዶክሰ እምነት መሠረት ትዳር የፈፀመው አለልኝ ከኢትዮጵያ ወጥቶ እግር ኳሰ መጫወት እንደሚሻ ይናገር ነበር።

የተጫዋቹ የቅርብ ጓደኛ የሆነ ሰው አለልኝ ለቤተሰቡ “ከሚገባው በላይ የሚያዝን፤ ይህን አደረግኩ ብሎ የማይረካ ሰው ነበር” ሲል ለቢቢሲ ይናገራል።

“በጣም ትልቅ ሕልም ነበረው። ከአንድ ሳምንት በፊት [ትዳር በመመሥረቱ] እንኳን ደስ አለህ ልለው ደውዬለት ነበር። ከጉዳቱ አገግሞ ድሬ ዳዋ እንደምንገናኝ ተነጋግረን ነበር። ሁሉም የቡደን አጋሮቹ የሚወዱት ሰው ነበር።”

የባሕር ዳር ከተማ ቡድን መሪ ሄኖክም እንዲሁ “አለልኝ እጅግ መልካም ባሕሪ ያለው፤ የቤተ-ክርስትያን ልጅ ነው” ይላሉ።

ሄኖክ አክለው አለልኝ ለክለብም ሆነ ለአገር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት እግር ኳስ ተጫዋች እንደነበር ያወሳሉ።

የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ኮሜንታተር በመሆን ያገለገለው ጊልበርት ሴሌብዋል በተጫዋቹ ድንገተኛ ሞት የተሰማውን ሀዘን ለቢቢሲ ይገልጣል።

“እኔ ኮሜንታተር እያለሁ ያገባቸውን ሦስት ጎሎች አልረሳም። ከፍፁም ቅጣት ምት ሳጥን ውጭ አክርሮ የመታቸው ተመሳሳይነት ያላቸው ጎሎች ነበሩ። በጣም የሚገርም ተሰጥዖ የነበረው፤ አውሮፓ ሁሉ ሄዶ መጫወት የሚያስችል አቋም እና ቁመና የነበረው ተጫዋች ነው። በጣም ደንግጫለሁ” ብሏል ጊልበርት።

የአለልኝ አዘነ ሥርዓተ-ቀብር ረቡዕ መጋቢት 18/2016 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ በአርባ ምንጭ ከተማ ውስጥ በርካታ ሕዝብ በተገኘበት ተፈጽሟል።

ቢቢሲ

የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ተገደሉ ! በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዶዶታ የደብረ  ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2...
26/03/2024

የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ተገደሉ !

በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ዶዶታ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር ለጊዜው ማንንነታቸው ባልታወቁ በተባሉ አካላት ተገደሉ::

ግድያው የተፈፀመው ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ መሆኑንም ከአካባቢው ምእመናን ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

በተፈጸመው ግድያ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት አንድ መሪጌታና ዲያቆንን ጨምሮ አምስት የቤተሰብ አባሎቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ታውቋል።

በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በዶዶላ ከተማ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸው ይታወሳል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።



በመላው አፍሪካ ጨዋታ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ይገባል***በ13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታ ስምንተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ልዑክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ...
25/03/2024

በመላው አፍሪካ ጨዋታ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ይገባል
***

በ13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታ ስምንተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ልዑክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ይገባል።

የመላው አፍሪካ ጨዋታ ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 14 ቀን 2016ዓ.ም በጋና-አክራ መካሄዱ ይታወቃል። በውድድሩ ከ53 ሀገራት የተውጣጡ ከ5 ሺህ በላይ ስፖርተኞች በ29 የስፖርት ዓይነቶች ተሳትፈዋል።

ኢትዮጵያም በ5 የኦሊምፒክ ውድድሮችና በአራቱ ኦሊምፒክ ያልሆኑ ስፖርቶች በድምሩ በ9 የስፖርት አይነቶች መሳተፏ ይታወቃል።

በአትሌቲክስ፣ በእግር ኳስ፣ በውኃ ዋና፣ በጠረጴዛና ሜዳ ቴኒስ፣ በቦክስ፣ በቅርጫት ኳስ፣ በብስክሌትና ወርልድ ቴኳንዶ ኢትዮጵያ የተሳተፈችባቸው የውድድር አይነቶች ናቸው።

ኢትዮጵያ በ9 የወርቅ፣ 8 የብር እና 5 የነሐስ በአጠቃላይ 22 ሜዳሊያዎችን በማግኘት በሁሉም የስፖርት አይነቶች ስምንተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ኢትዮጵያ ካገኘቻቸው 22 ሜዳሊያዎች 18ቱ የተገኙት በአትሌቲክስ ሲሆን፤ 7 የወርቅ 7 የብርና 4 የነሐስ ሜዳሊያ በአትሌቲክሱ ተገኝቷል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ በቦክስ 2 የወርቅና 1 የነሐስ እንዲሁም በብስክሌት 1 የብር ሜዳሊያ አግኝታለች።

ልዑኩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች አቀባበል እንደሚያደርጉለት ከባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
(EBC)

“የኦሮሞን ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል”      አቶ ሽመልስ አብዲሳ    የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በግፍና በኢ-ፍትሀዊነት  ከቀየው ፊንፊ...
24/03/2024

“የኦሮሞን ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል” አቶ ሽመልስ አብዲሳ

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በግፍና በኢ-ፍትሀዊነት ከቀየው ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) እንዲሰደድ የተደረገውን የኦሮሞ ሕዝብ ወደ ቀደመ ስፍራው እንዲመለስ እያደረግን ነው ሲሉ በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ተናግረዋል።

የኦሮሞ ሕዝብ ለዘመናት ሲደርስበት በነበረው መገፋት የተነሳ ከተማዋን ለሌሎች ለቆ እስከመውጣት ደርሷል ያሉት ሽመልስ፣ይህም መገፋት ሄዶ ሄዶ እትብቱ በተቀበረባት ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) የባዕድነት ስሜት እንዲሰማውና በራሱ ቀየ ላይ ባይተዋር እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።

ከተማዋ በሌሎች የበላይነት ስር ሆና በተለይም የኦሮሞን ሕዝብ ለዘመናት እንደ ባዕድ የመመልከት አካሄድን ስትከተል ቆይታለች ያሉት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በከተማዋ አንዳችም የኦሮሞን ህዝብ ማንነት የሚገልጽ ምልክት (symbolic represention) አለመኖሩ ነበር በማለት ጠቁመዋል።

“ከዚህ በኋላ ግን መንግሥታችን፣ያለፈውን የውድቀት ታሪክ፣ጉዳትና መፈናቀል ማውራት፣ እንዲህ ተደረግን ብሎ ስሞታ ማቅረብ አይሻም” ሲሉ ገልጸዋል።

ይልቁንም የተገኘውን ዕድል በመጠቀም፣ትላንት በሕዝባችን ላይ ሲደርስ የነበረውን ግፍና በደል ለመካስ ብሎም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም አዲስ ምዕራፍ ከፍተን ወደ ሥራ ገብተናል ብለዋል።

በዚህም መሠረት፣መንግሥት በግፍ ከቀየው የተፈናቀለውን ሕዝብ በመመለስ በከተማዋ በሁሉም ዘርፍ ካሉ ዕድሎች ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ ይገኛልም ሲሉ ጠቁመዋል።

አዲስ አበባን በዚህ ወቅት ስንመለከት፣ በፖለቲካው፣በኢኮኖሚ፣በማኅበራዊ እንዲሁም በባሕል የሕዝባችንን ሰፊ ተሳትፎ የሚሹ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ይገኛሉ ያሉት ሽመልስ፣ይህም ሀሳባችንን ከግብ ለማድረስ ትልቅ መሳሪያ ይሆነናል ብለዋል።

እየተሠሩ ካሉት ከነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል፣የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣የኦቢኤን ሚዲያ ኮምፕሌክስ፣የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተፕራይዝ፣የኦሮሞ አርት ማሠልጠኛ ማዕከል፣የኦሮሞ ባሕላዊ ምግብ አሰራርና ዝግጅት ማዕከል፣የኦሮሞ ባሕላዊ እቃዎች ማሳያና የገበያ ማዕከል፣ሲንቄ ባንክ፣ቡሳ ጎኖፋ እንዲሁም የተለያዩ ኢንተርፕራይዞችን በጥቂቱ ማንሳት ይቻላል ሲሉ ገልጸዋል።

እስካሁን ያለው አፈጻጸም፣መንግሥት የሕዝባችንን የዘመናት ጥያቄና እውነትን ወደ ቦታዋ ለመመለስ እንዲሁም ቃል የተገባውን ለመፈጸም ያለውን ቁርጠኛነት ያሳየ ነው ብለዋል።

አሁንም የሕዝባችንን ያልተመለሱ ጥያቄዎች በሂደት ለመመለስ በትኩረት እንሰራለን ያሉት ርዕሰ መሥተዳድሩ፣ሕዝባችንን ከከተማው መግፋትና ማሳደድ ግን ከዚህ በኋላ አክትሞለታል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

[ዋዜማ]

ሩሲያ ማቅ ለብሳለችበሩሲያ ከደረሰው ዘግናኝ ግድያ በኃላ  ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ  11 ሰዎች እንደታሰሩ የደህንነት ባለስልጣናት ተናግረዋል፡ የሩስያ የኤፍ.ኤስ.ቢ የፀጥታ አገልግሎት ለፑቲን ...
24/03/2024

ሩሲያ ማቅ ለብሳለች

በሩሲያ ከደረሰው ዘግናኝ ግድያ በኃላ ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ 11 ሰዎች እንደታሰሩ የደህንነት ባለስልጣናት ተናግረዋል፡

የሩስያ የኤፍ.ኤስ.ቢ የፀጥታ አገልግሎት ለፑቲን እንደተናገረው አርብ በሞስኮ አቅራቢያ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት 11 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ።ከነዚህ መካከል አራቱ በቀጥታ የተሳተፉ ሰዎችን መሆናቸውም ገልጿል።

ተጨማሪ ተባባሪዎችን የመለየት ስራ እየተሰራ ነውም ሲል ኢንተርፋክስ የክሬምሊን ጠቅሶ ዘግቧል። ሌሎች ተጠርጣሪዎችም በአቅራቢያው ወደሚገኝ ጫካ ሸሽተው ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑንም አክለዋል።

ታጣቂዎቹ በሞስኮ አቅራቢያ በሚገኘው ታዋቂው የክሮከስ አዳራሽ ላይ ተኩስ ከፍተው ቢያንስ 150 ሰዎች ሲገድሉ፣ 187 ሰዎች መቁሰላቸውን የሩሲያ የደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል ።

ከሟቹቹ መካከል ስምንቱ ህፃናትን ናቸው።ስድስት ሰዎች በፅኑ ተጎድተዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል ።

ለጥቃቱ ታጣቂው የእስላማዊ መንግሥት (አይኤስ) ቡድን ኃላፊነቱን መውሰዱን በበይነ መረብ የወጣ አንድ ያልተረጋገጠ መግለጫ አመልክቷል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት በበኩላቸው አይኤስ ሩሲያን ለማጥቃት እንደሚፈልግ የሚያሳይ መረጃ ማግኘታቸውን ለቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ ተናግረዋል።

ከሁለት ሳምንታት በፊት በሩሲያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጎቹ በርካታ ሰዎች በሚሰባሰቡባቸው ሕዝባዊ ስፍራዎች እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ አስተላልፎ ነበር።

በዚህም ማስጠንቀቂያው ላይ “ጽንፈኞች በሞስኮ ሕዝብ በሚሰባሰቡባቸው ስፍራዎችን የጥቃት ዒላማ ለማድረግ ዕቅድ አላቸው” የሚል ሪፖርትን እየተከታተልኩ ነው ብሎ ነበር።

ኤምባሲው አርብ ምሽት ባወጣውም መግለጫ ጥቃቱ ወደደረሰበት ስፍራ ዜጎቹ ዝር እንዳይሉም ምክሩን አስተላልፏል።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጥቃቱን አስመልክቶ ለሕዝባቸው መግለጫ ባይሰጡም፣ ምክትላቸው በጥቃቱ የቆሰሉ በፍጥነት እንዲያገግሙ ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

ኦርቶዳክሳዊ ጥሪ" ምዕመናን   ለብሳችሁ እንድትገኙ እና የአቅማችሁን ያህል እድትለግሱ ጥሪ እናቀርባለን " - ማህበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት...
24/03/2024

ኦርቶዳክሳዊ ጥሪ

" ምዕመናን ለብሳችሁ እንድትገኙ እና የአቅማችሁን ያህል እድትለግሱ ጥሪ እናቀርባለን " - ማህበረ ቅዱሳን

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን " ኑ ቸርነትን እናድርግ " በሚል መሪ ቃል ነገ እሁድ ከቀኑ 7:00 ላይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል።

ገቢ ማሰባሰቢያው በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስና ድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን፣ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶችን ለመደገፍ የሚውል እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአዘጋጆቹ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

የመግቢያ ትኬቶች በ100 ብር እየተሸጡ ሲሆን ትኬቶቹን ፦
1. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 4ኛ ወለል (ቤተ አብርሃም)
2. በወረዳ ማዕከላት ጽ/ቤቶች
3. በማኅበረ ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቆች
4. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ የዕለት ገንዘብ መሰብሰቢያዎች
5. በአሐዱ ባንክ ሁሉም ቅርንጫፎች
6. በሰ/ት/ቤት ጽ/ቤቶች ማግኘት ይቻላል ተብሏል።

ነገ በመግቢያ በር ላይም ትኬት ማግኘት እንደሚቻል ተገልጿል።

ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች / ምዕመናን ነገ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ ሲሄዱ ክርስቲያናዊ አለባበስ እንዲለብሱ እና የአቅማቸውን ያህል እንዲለግሱ ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ- Zena24

ዛሬ አዳማ የተቀጣሁት ቅጣት ነው። ሰሞኑን አዳማ ነበርኩ። ዛሬ ወደአዲሳባ እንደምመለስ ያወቀው 5 ቀናት ያደርኩበት ሆቴል ማኔጀር "ባለቤቴና ልጆቼ ወደአዲሳባ ስለሚሄዱ ፍቃድህ ከሆነ ውሰድልኝ...
23/03/2024

ዛሬ አዳማ የተቀጣሁት ቅጣት ነው።

ሰሞኑን አዳማ ነበርኩ።

ዛሬ ወደአዲሳባ እንደምመለስ ያወቀው 5 ቀናት ያደርኩበት ሆቴል ማኔጀር "ባለቤቴና ልጆቼ ወደአዲሳባ ስለሚሄዱ ፍቃድህ ከሆነ ውሰድልኝ" አለኝ እሺ ተዘጋጅተው ሲጨርሱ ፍራንኮ ይምጡ እስከዛ ጎማ ላሳይ ብዬ ወደጎሚስታ ሄድኩ።

ለመሄድ ዝግጁ መሆናቸውን ደውለው ሲነግሩኝ ፍራንኮ ሄጄ እነርሱን ለማስገባት የመኪናዬን በር ከመክፈቴ ትራፊክ መጥቶ ከመንገድ ላይ እንደታክሲ ሰው እየጫንክ ነው እቀጣሃለሁ አለኝ።

እረ ባክህ ይሄ መኪና 5 ሰው ብቻ ነው የሚጭነው ምኑ ነው ታክሲ የሚመስለው እርሷም የጓደኛዬ ባለቤት ነች እያልኩ ላስረዳው ብሞክርም ሊሰማኝ ስልቻለ እንደአዲሳባ ቅጣቱ ከ300 እስከ 500 መስሎኝ አታክብድ በቃ ቅጣኝ አልኩት የቅጣት ወረቀት ሰጠኝ።

ቅጣቱ ስንት ቢሆን ጥሩ ነው? 3000 ሺህ ብር። ከፍዬ ስመጣ ደግሞ ትራፊኩ ስሜን በትክክል ስላልፃፈው መንጃ ፈቃዴ ላይ ካለው ስም ጋር ልዩነት አምጥቶ ሌላ መንገላታት።

ሁለተኛ አዳማ በግል መኪናዬ አልሄድም። ታክሲ ሹፌሮች ግን እንዴት ቻላችዃቸው? ደግሞ ግዴታ ስንቄ ባንክ ብቻ ክፈል የሚሉት ቢሮክራሲ የፈጣሪ ያለህ።

እዚህ ሀገር እየገባኝ ያለው ነገር ሰው ሲቀጣ ሲናደድ ነፍሳቸው ሃሴት የምታደርግ የSchadenfreude ተጠቂ ህግ አስከባሪዎች ብዙ ናቸው። ትንሽ ታገሱኝ ዲቪ ሞልቻለሁ!

Via Yihune Ephrem Kassahun

"ዶክተሩ የሞቱት ከከፍታ ቦታ ወድቀው ነው" ፖሊስዶክተር በሃይሉ ሀይሉ ከከፍታ ቦታ በመውደቅ በአካላቸው ላይ በተከሰተ ጉዳት ህይወታቸው ማለፉን የዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል የአስክሬን የምርመራ...
23/03/2024

"ዶክተሩ የሞቱት ከከፍታ ቦታ ወድቀው ነው" ፖሊስ

ዶክተር በሃይሉ ሀይሉ ከከፍታ ቦታ በመውደቅ በአካላቸው ላይ በተከሰተ ጉዳት ህይወታቸው ማለፉን የዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል የአስክሬን የምርመራ ውጤቱ እንዳረጋገጠ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራውን የቀጠለ ሲሆን ከከፍታው የወደቁበትን ሁኔታና ሌሎች ተያያዥ የምርመራ ውጤቶች ሲጠቃለሉ ለህዝብ ግልፅ እንደሚደረጉ አስታውቋል፡፡
***
የሰርጀሪ ህክምና ባለሞያ የሆኑት ዶክተር በሀይሉ ሀይሉ መጋቢት 8 ቀን 2016 ዓ ም በዕለተ እሁድ ሊነጋጋ ሲል ስፖርት ለመስራት ከቤት ወጥተው እንዳልተመለሱ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲገለፅ ቆይቷል።

ፖሊስ መረጃው ከደረሰው ሰዓት ጀምሮ ባደረገው ማጣራት የሟች ዶክተር በሀይሉ ሀይሉ አስከሬን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ከቦሌ ሚካኤል ወደ ሳሪስ አቦ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኝ ቀጠና 3 በተለምዶ ማሞ ድልድይ ስር ወድቆ በመገኘቱ በወቅቱ አስከሬኑ ተነስቶ የአሟሟታቸውን ምክንያት ለማወቅ ለአስክሬን ምርመራ ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል እዲሄድ ተደርጓል።

ከሆስፒታሉ የተገኘው የአስክሬን ምርመራ ውጤት እንደሚያስረዳው ከከፍታ ቦታ በመውደቅ በአካላቸው ላይ በተከሰተ ጉዳት ህይወታቸው ማለፉን የአስክሬን የምርመራ ውጤቱ ይገልፃል፡፡

ሟች ዶ/ር በይሉ ሐይሉ ከከፍታው ላይ ቁልቁል ወደ ገደሉ በመውረድ አካላቸው ድንጋይ ላይ ስላረፈ በጭንቅላታቸው፤ በእግራቸው በጀርባ አጥንታቸውና በውስጥ የሰውነታቸው አካላት ላይ በደረሰባቸው ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ከሆስፒታሉ የተገኘው የአስክሬን የምርመራ ውጤቱ ያብራራል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ስራውን የቀጠለ ሲሆን ከከፍታው የወደቁበትን ሁኔታና ሌሎች ተያያዥ የምርመራ ውጤቶች ሲጠቃለሉ ለህዝብ ግልፅ የሚደረጉ መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ፖሊስ በዶክተር በሃይሉ ሀይሉ አሟሟትን የተሰማውን ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸውና ለሙያ አጋሮቻቸው መፅናናት እንዲሰጣቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡

ምንጭ Zena24

ፋንታሁን ሙጬ ተሰደዱየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የብዙሀን መገናኛ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ሊቀ መምህራን ፋንታሁን ሙጬ ከሀገር መሰደዳቸው ሰምተናል።ምንጭ Zena24
23/03/2024

ፋንታሁን ሙጬ ተሰደዱ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የብዙሀን መገናኛ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ሊቀ መምህራን ፋንታሁን ሙጬ ከሀገር መሰደዳቸው ሰምተናል።

ምንጭ Zena24

አርሶ አደሯ በረከት በ45 ብር ቀይ ሽንኩርት በመሸጥ ላይ መሆናቸውንና ጥሩ ቲማቲሞችን በ12 ብር እየሸጡ መሆናቸውን ተናግረዋል። ሌሎች አትክልቶችን አርሶ አደሮች በሚሸጡበት ዋጋም እየሸጡ መ...
22/03/2024

አርሶ አደሯ በረከት
በ45 ብር ቀይ ሽንኩርት በመሸጥ ላይ መሆናቸውንና ጥሩ ቲማቲሞችን በ12 ብር እየሸጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሌሎች አትክልቶችን አርሶ አደሮች በሚሸጡበት ዋጋም እየሸጡ መሆናቸው አሳውቀዋል።

በረከት አትክልቶቹን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ ወደ ቤትዎ ወይም ቢሮዎ እንደሚያደርሱም ጠቅሰዋል።

አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ በ1 ቢሊየን ብር ወጪ የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል ልትገነባ ነውበአርቲስት መቅደስ ጸጋዬ የተመሰረተው “መቅደስ የልጆች አድማስ" የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል የፊታችን መጋ...
22/03/2024

አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ በ1 ቢሊየን ብር ወጪ የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል ልትገነባ ነው

በአርቲስት መቅደስ ጸጋዬ የተመሰረተው “መቅደስ የልጆች አድማስ" የህጻናት ማሳደጊያ ማእከል የፊታችን መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ወደ ስራ እንደሚገባ የማእከሉ መስራች አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ በዛሬው እለት አስታውቃለች

መቅደስ የልጆች አድማስን ለማቋቋም ሃሳቡ የተፀነሰው ከ6 ዓመታት በፊት እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን፤ ሙሉ በሙሉ አገር በቀል የሆነና በአርቲስት መቅደስ ፀጋዬ የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው::

በመግለጫው እንደተገለጸው ድርጅቱን ሙሉ ለሙሉ በመገንባትና በሙሉ አቅሙ ስራውን እንዲጀምር ለማድረግ እስከ አንድ ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፤ በአጠቃላይ በሃያ እንድ ሺ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ተቋም ነውም ተብሏል

ድርጅቱ በዋናነት ልዩ ትኩረት እና ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው ወላጅ አልባ ህፃናት ልጆች አስፈላጊውንና ሁሉን አቀፍ እንክብካቤ በመስጠት በቀጣይ የሕይወት ጉዟቸው ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ የበጎ አድራጎት ድርጅት ወይም ማዕከል እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ማእከሉን በአሁኑ ሰአት በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ያሉና በሀገራችን ተፅእኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦች በቦርድ አባልነት እንደሚመሩትም ተነግሯል፡፡ .

በማዕከሉ ውስጥ ለሚቆዩ ልጆች ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያ፣ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶችን ከመስጠትና፣ የአካል ብቃት ማጎልመሻ ከማደራጀት ባሻገር፤ የማኅበራዊ ሕይወትና የአእምሮ ማበልፀጊያ ስልጠናዎችን በመስጠት ሙሉ ጤንነታቸው የተረጋገጠ፣ በአካላዊ እድገታቸው የበቁ፣ በሥነ ልቦና፣ በግልና በማሕበራዊ ሕይወታቸው ጠንካራ የሆኑ እንዲሁም በአእምሮአዊ የፈጠራ ችሎታቸው የተደነቁ እና በዕውቀት የዳበሩ ሆነው፤ የመጪው ጊዜ ብሩህ እና ስኬታማ ዜጎችን እንዲሆኑ በትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል።

ማእከሉ እውን የሚሆንበትና በይፋ ገቢ በማሰባሰብ ወደ ስራ የሚገባበት ቀን መጋቢት 26 በስካይ ላይት ሆቴል ሲሆን፤ በዝግጅቱም ላይ ከፍተኛ የሀገራችን መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ባለሃብቶች፣ የኤምባሲ ተወካዬች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሐሳቡን የሚደግፉና ቀና ልብ ያላቸው ግለሰቦችም ይታደሙበታል ተብሏል።

ይህ ድርጅት የመጀመሪያ ተቋሙን የሚገነባውና ስራውን የሚጀምረው በአዲስ አበባ ሲሆን ቀስ በቀስም ወደ ክልሎች ቅርንጫፎቹን የሚያሰፋ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር 200 ህፃናትን ከመላው ኢትዮጵያ ተቀብሎ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ሲገባ ደግሞ 1000 ህፃናትን የመቀበል አቅም የሚኖረው እንደሚሆን ተነግሯል።
(በድሬቲዩብ ሪፖርተር)

ባይ ባይ አዲስ አበባ !! ባይ ባይ ፒያሳ!!       (ጋዜጠኛና የሕግ ባለሙያው ሰለሞን ጓንጉል)    በፒያሳ እየሆነ ያለው ማፍረስ  ህዝቡን ከፍተኛ  ድባቴ ውስጥ የሚጥል ነው ፡፡ በቀጥታ...
20/03/2024

ባይ ባይ አዲስ አበባ !! ባይ ባይ ፒያሳ!!

(ጋዜጠኛና የሕግ ባለሙያው ሰለሞን ጓንጉል)

በፒያሳ እየሆነ ያለው ማፍረስ ህዝቡን ከፍተኛ ድባቴ ውስጥ የሚጥል ነው ፡፡ በቀጥታ ቤት ߹ አካባቢ ߹ ስራ ߹ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ትስስሮሽ አብሮ ፈርሶ ኑሮ ፈተና ከሚሆንባቸው ዜጎች አንስቶ ባለብዙ ትዝታዎቹ የከተማ ነዋሪዎች ጭምር " ምን ታመጣላችሁ!" የተባልን ይመስለኛል፡፡

ስለሚሰራው ስራ በቅጡ እንድናውቀውና ለሕዝብ ጥቅም መሆኑን አምነን እንድንቀበል የሚያስችል ስራ በበቂ ሁኔታ አልተሰራም ፡፡ አካባቢው በመፍረሱ የሚመጣውን ፈተና ለመቀበል ፤ የሚሰራውንም ስራ አምነንበት እንድናወድስ በቂ ጊዜም አልተሰጠንም ፡፡

እንደ አንድ የከተማ ነዋሪና ባለቤት ሃሳባችን አልተጠየቀም ፤ አልተደመጥንም ፡፡ ባይተዋርነት እንዲሰማን ተደርጓል፡፡ የሚመለከታቸው ባለሙያዎች በተገቢነቱ ላይ ሙግት አላደረጉም፡፡ እየተሰራልን ይሁን እየተሰራብን ማወቅ አልቻልንም፡፡

ከሁሉም በላይ ታሪክ ߹ ቅርስና ባሕል ጉዳት አገኛቸው ߹ ማሕበራዊ ትስስሮሽ አደጋ ላይ ወደቀ ብለው የሚጮሁት ያገባናል የሚሉ የከተማዋ ነዋሪ ግለሰቦች ብቻ ሆነዋል ፡፡ ይህ ስራቸው የሆነ የከተማ አስተዳደሩም ሆነ የፌደራል የባሕልና ማሕበራዊ ጉዳይ ተቋማት ለጩኸትና ጥያቄው መልስ አልሰጡም ፡፡ የጥያቄዎቹን ተገቢ መሆንና አለመሆን ለማብራራት አልሞከሩም ፡፡

በ2011 ዓ.ም ተሻሽሎ የጸደቀውና ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አዋጅ ቁ 1161/2011 በቀዳሚነት አንድ ይዞታ እንዲለቀቅ የሚደረገው ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ስለመሆኑ ይደነግጋል ፡፡ አንድን ስራ ለሕዝብ ጥቅም የሚሰራ ነው ለማለት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ለሕዝብ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ በማበርከት የተሻለ የጋራ ጥቅምና እድገት የሚያመጣ መሆን ይኖርበታል፡፡
ከመነሻው ማሕበራዊና ኢኮኖሚያው ፋይዳ ከሌለው የሕዝብ ጥቅም የለበትም ፡፡ በመሆኑም ይዞታችሁን ልቀቁ የሚለው የመንግስት አካል ሊሰራ የታሰበው ስራ ለሕዝብ ጥቅም የሚሰራ ስለመሆኑና ምን እንደሆነ ߹ የባለይዞታው መብትና ግዴታ ߹ አፈጻጸሙንና ሌሎችንም ዝርዝር

ሁኔታዎችን ነዋሪዎችን በደብዳቤ በመጥራት ከመነሳታቸው አንድ ዓመት በፊት ማወያየት ይጠበቅበታል፡፡ የሚሰራው ስራ አስቸኳይ ቢሆን እንኳን ነዋሪዎቹ ከመነሳታቸው 6 ወራት በፊት ውይይቱ መደረግ እንዳለበት የሚኒስትሮች ም/ቤት ያወጣው ደንብ ቁጥር 472/ 2012 አንቀጽ 4 ንኡስ አንቀጽ 5 ይደነግጋል፡፡

የውይይት ጥሪው ለሁሉም ተነሺዎች በደብዳቤ መድረስ ያለበትና ስለመድረሱም ማረጋገጫ መቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከነዋሪው ቢያንስ 3/4ኛ የሚሆኑት ውይይቱ መደረግ እንደሚገባው ፤ ይህ ቁጥር ካልሞላ በድጋሚ ጥሪ ሊደረግ እንደሚገባና አሁንም ካልተገኙ በተገኙት ግማሽ አባላት ውይይት መደረግ እንዳለበት ደንቡ ይደነግጋል፡፡ በተገኘው ሰው ብቻ ውይይት የሚደረገው በሶስተኛው ጥሪ መሆኑም በግልጽ ተጽፏል፡፡

በሕጉ መሰረት ማወያየት ያስፈለገው ነዋሪው የሚለቀው ይዞታውን ብቻም ሳይሆን ሃብቱን ߹ ባህላዊ ߹ ሃይማኖታዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስሮሹን ߹ ታሪክና ትዝታውን ጭምር በመሆኑ ነው ፡፡ የሚሄደው ወደ አዲስ ሕይወት ፤ ኑሮና ትግል ነውና የመሄዱን ምክንያት ሊያምንበት ዋጋ የሚከፍለው ለሕዝብ ጥቅም ሲባል እንደሆነ አምኖ መቀበል ይኖርበታል ፡፡ ለመቀበል አእምሮን ለማዘጋጀት ደግሞ ቢያንስ ከስድስት ወራት ያላነሰ ጊዜ እንደሚያስፈልገው ሕጉ አምኖ ሰጥቶታል፡፡ አሁን እየሆነ ያለውንና ጥድፊያውን ለተመለከተ ግን እየሆነ ያለው ሁሉ አሁን በጠቀስኳቸውና በሌሎችም በሕጉ የተቀመጡ ሁኔታዎች መሰረት ስለመሆኑ ጥያቄን ያጭራል።

ትዝታ ዘ-ፒያሳ    ሰሞኑን አዲስ አበባ በከፍተኛ ደረጃ ተዋክባለች። ከተማዋን መልሶ ለማልማት እና አለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ውብ አዲስ አበባን ለመፍጠር በሚል በከተማዋ የንግድና የመኖሪያ...
20/03/2024

ትዝታ ዘ-ፒያሳ

ሰሞኑን አዲስ አበባ በከፍተኛ ደረጃ ተዋክባለች። ከተማዋን መልሶ ለማልማት እና አለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ውብ አዲስ አበባን ለመፍጠር በሚል በከተማዋ የንግድና የመኖሪያ ቤቶች በየአቅጣጫው እየፈረሰ ነው። እየፈረሰ ነው ከማለት እየወደመ ነው ማለቱ ይቀላል ። በፒያሳ ፣ በአራት ኪሎ፣ በመገናኛ ፣ በጎተራ፤ በሳሪስ፣ በቄራ፣ በቦሌ...ወዘተ ፈረሳ በየቦታው እየተካሄደባት ይገኛል ። ከዚህ በፊት አዲስ አበባን የሚያውቃት እና ወደ ሌላ ስፍራ የሄደ ሰው ተመልሶ ከተማዋን ቢያያት አዲስ አበባ ሳይሆን ሌላ ከተማ የገባ እስኪመስለው ቢደናገር አይገርምም ። በመዲናዋ ወትሮ ከሚርመሰመሱት መኪኖች ባልተናነሰ ሎደርና ዶዘር ጎልተው ይስተዋላሉ። ሎደርና ስካቫተር ቤቶችን ሲያፈራርሱ ህንፃዎችን ሲያወድሙ መንገዶችን ሲንዱ የ130 ዕድሜ ባለፀጋዋ አዲስ አበባ ቆማ ትታዘባለች። ብዙ ሰዎችን ቤቶች ለምን እንደሚፈርሱ እንኳን ስትጠይቋቸው "እኔ አላውቅም!" በሚል ቁጭት ነው የሚሏችሁ። ማንም የተሟላ መረጃ ይሰጠኛል ብለው አይጠብቁም ። በእርግጥ መንግስት ከተማዋን ለማሳመርና መንገድ ለማስፋት መሆኑን ውስጦ ቢያውቅም ይሄ በመዲናዋ እየተካሄደ ያለው በዘመቻ ማፍረስ፣ በዘመቻ ማውደም የእርሶንም ናላ አዙሮታል። በቃ ዝም ብሎ የሚሆነውን መቀበል።
በተለይም በፒያሳ ዶሮ ማነቂያ፣ እሪ በከንቱ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ጊዮርስ አካባቢ ፣ ሰራተኛ ሰፈር ፣አገር ፍቅር፣ ደሀብ ሆቴል፣ መኮንን ባቅላባ፣ አያሌው ሙዚቃ ቤት እና ሌሎቹንም ከዚህ በኋላ ታሪክ ብቻ ሆነው ቀርተዋል።

ከሰፈሮች ሁሉ የስልጣኔ ቅድምና ያላት የልዑል ራስ መኮንን ግዛት ፣ የደጃች ውቤ መቅደስ፣ የነክቡር ይድነቃቸው ተሰማ ሰፈር ፣ የነአለማየሁ እሸቴ መንሸራሸሪያ ጎዳና ፣ የደራሲ ነፍሶች ሁሉ የሚዘጉባት ዋሻ፣ ድምጻዊያን፣ ተዋኒያን እና በአጠቃላይ የኪነጥበብ ሰዎች መገኛ እና መነኻሪያ ነበረች ፒያሳ።

የድሮ አራዳዎች መማጸኛ ከተማ ፣ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር ለፍቅሯ ተንበርክኮ በእቅፏ የተሸሸገባት ፣ እነ መሃመድ ሰልማን የተቀኙላት፣ እነ ፍቅሩ ኪዳኔ የተራቀቁባት ።

የእድሜ ገደብ ሳይወስናት ፣ የኢኮኖሚ መደብ ሳያጥራት ሁሉን እንደ ፍላጎቱ የምታስተናግድ ። ሽማግሌዎች በትዝታ ፈረስ የሚነጉዱባት ፣ ጎልማሶች የቅርብ ትዝታቸውን እያዋዙ በመስፋቅሯ የታሰሩባት ፣ ወጣቶች ሰርክ አዲስ ያለመሰልቸት የሚመላለሱባት ሁሉን አስማምታ ሁሉን አስተባብራ የያዘች የፍቅር ሐገር ። አዎ ፒያሳ ብቻዋን ሐገር ናት (ነበረች 😭) ።

የአራዳው ጊዮርጊስ ጸሎትና ቅዳሴ ፣ የአቡነ ጴጥሮስ የታማኝነት እና የምስክር ሃውልት ፣ የቤኒን መስጂድ አዛን፣ የአድዋው ምኒልክ የጀብድ ስራና ገድል ፣ የደጎል አደባባይ ትዕይንት፣ የእነ ሐጎስ ገ/ ህይወት እና ተክሌ ወርቅ ቤት አክሱም እና ላሊበላ ወርቅ ቤት ፤ ዘመን አስቆጣሪው የአንበሳ ጫማ፤ የአርበኛ አባቶች ክስተት! ናት ፒያሳ። ዛሬ ግን ትዝታዋን ብቻ ትታ አልፋለች ፒያሳ።

የጣይቱ ሆቴል ጣፋጭ አገልግል ፣ የአዲስ አበባ ሬስቶራንት ጠጅ ፣ የደሐብ ሆቴል ምላስ ሰንበር ፣ የዶሮ ማነቂያ ስጋ ቤቶች ጥብስ ፣ የመኮንን ባቅላባ (😭) ፣ የአያሌው ሙዚቃ ቤት አጠገብ ያለው ጁስ ቤት...ወዘተ ነበር በፒያሳ። ቀደምት አዲስ አበቤዎች ሆኑ አሁን ያለው ትውልድ "እንሂድ ፒያሳ እንብላ ባቅላባ" ይባባሉባት ነበር። ፍቅረኞች የፍቅርን ሀሁ የሚጀምሩበት መቼም አይረሳም የባቅላባው ቤት ትውስታ። ማን ጎራ ያላለ አለ መኮንን ባቅላባ ደርሶ ከፒያሳ ።

የመሲ ገበታ ማህበራዊ ፣ የትሬን ሃውስ አፍላ ፍቅር ፣ የቢግትሪ ጨዋታ ፣ የሸዋ ሆቴል ድራፍት ፣ የዶክተሩ ቤት አፕሬቲቭና ጂን ፣ የሐምዛ ድራፍት ፣ የጃምቦ ሃውስ ድራፍት ፣ የእህትማማቾች ፍርፍር ትዝታው ብቻ ቀሪ ሆኗል።

የኮፊ ፕላስ ፈጢራ ፣ የአለም ቡና ማኪያቶና ሳምቡሳ ፣ የናሽናል ሆቴል ቡላ ፣ የካስቴሌ ዝና ፣ የአራዳ ጨብሲ ቤት ግርግር ፣ የሳምራዊት ሆቴል ሽሮ ፣ የአረጋሽ ቡና በቃ የለም ከዚህ በኋላ

የትሪያኖን ማኪያቶ ፣ የ ቃዋ ፈጢራና ቡና ፣ የኪያብ ሳምቡሳ ፣ የ ጉድታይምስ ወይንና ካፕል ፣ የዞብል ሽሮ ፣ የ ኤንሪኮና ጎጆ ጣፋጭ ኬኮች ፣ የቲሩም ቦክሰኛ ፣ የሜሪ ምግብ ቤት ጣፋጭ ምግቦች።

ብራንድ ለባሾች ዘናጭ ቡቲክ የሚገዙበት ፣ መደበኛው ሰው እንደኔ በ 50 እና መቶ ብር ቆንጆ መነጽር ገዝቶ የሚምነሸነሽበት ፣ ውብ የእጅ ሰዓቶችን የሚያስርበት ፣ የጣሊያን ቤት ከፋይ ጫማ ገዝቶ የሚነጥርበት ያለው ደሞ ማያሚ ጎራ ብሎ በዳላር የሚሸምትበት።

ሽማግሌው ቀዝቅዞ ትዝታው የሚቀሰቀስበት ፣ ወጣቱ የወደዳትን እያማለለ የሚገማሸርበት ፣ አርበኞች መለስ ቀለስ የሚሉበት ፣ ራስታዎች ውጥማ በርካሽ ዶርም የሚያደርጉባትት። መዝናናት ቢፈልጉ አማርጠው የሚዝናኑበት ሰው ተስፋ ቆርጦ ሞትን ሲመኝ ውሳኔውን እንዲቃኝ የምታስደርግ ምትሃታዊ ከተማ!

ፒያሳ ሰፈር ወይም መንደር አይደለችም ፒያሳ ሐገር ናት ። ፒያሳ ብሔራዊ ጀግንነት የሚወደስባት ከተማ ናት ። ፒያሳ ጨዋ ፣ ዱርዬ ፣ ምሁር ፣ መሃይም ፣ ሌባ ፣ ሰራተኛ ፣ ጤነኛ ፣ በሽተኛ ብላ ሳትለይ ሁሉን እንደ አመሉ ሸክፋ የኖረች የእናት ጓዳ ናት(ነበረች)።

አፈረሱት አሉ መሃል አራዳን ያለ እናት ያለ አባት ያሳደገንን ብለው እነ ከተማ መኮንን ትንቢት የተናገሩላት ከተማ ናት

# ዘላለም የተባሉ ፀሀፊ ላይ ጭማሪ አድርጌ የጻፍኩት

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ አውጥተዋል የተባሉ ተማሪዎች ስማቸው ይፋ ተደርጓል።  በአዲስ አበባ እና ከጂማ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ወስደዋል የተባለው አጠቃላይ ገንዘብ ም...
17/03/2024

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ አውጥተዋል የተባሉ ተማሪዎች ስማቸው ይፋ ተደርጓል። በአዲስ አበባ እና ከጂማ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ወስደዋል የተባለው አጠቃላይ ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ ባይታወቅም አንዳንድ ምንጮች እስከ 1.2ቢሊዮን መመዝበሩ እየተነገረ ይገኛል ።

ስም ዝርዝር መለቀቅ ተጀምሯል

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ራሳችሁን ከችግር ታደጉ የተባለ ሲሆን

አሁን ላይ ስም ዝርዝር መለቀቅ መጀመሩ ሸገር ተመልክቷል።

16/03/2024

አንድም ተማሪ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ዛሬ ምሳ አልበላም 😂

እድሜ ለንግድ ባንክ Platinum ደረጃ Sponsor ‼️

ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ለበርካቶች የተሰጠው  African Leadership Magazine Award ምንድን ነው?                             ምንጭ፦ ኤሊያስ መሰረ...
16/03/2024

ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ለበርካቶች የተሰጠው African Leadership Magazine Award ምንድን ነው?

ምንጭ፦ ኤሊያስ መሰረት

አዩሬ አታፎሪ የተባለ ጋናዊ ጋዜጠኛ ሰሞኑን ያዘጋጀው የ African Governance Award ለኢንደስትሪ ሚኒስትራችን መበርከቱንና ከጀርባው ያሉ አንዳንድ መረጃዎችን አካፍዬ ነበር።

እስቲ የትናንት ምሽቱን ሽልማት ትንሽ እንፈትሸው።

የ African Leadership Magazine Award የሚዘጋጀው ደግሞ በናይጄርያዊው ጋዜጠኛ ኬን ጊአሚ ነው። ኬን ከዚህ በፊት 11 ግዜ ሽልማቶችን አዘጋጅቶ ሸልሟል፣ የዚህ አመት ሽልማቱም እንደ ሁል ግዜው ግርታን የሚፈጥር ሆኗል።

እንዴት?

1. ድርጅቱ በፌስቡክ ገፁ ላይ የዘንድሮ የሽልማቱ አሸናፊዎች ብሎ የዘረዘራቸው የኬንያው ፕሬዝደንት ዊልያም ሩቶ፣ የቀድሞው የላይቤርያው መሪ ጆርጅ ዊሀ፣ የታንዛኒያዋ ፕሬዝደንት ሳሚያ ሱሁሉ... ወዘተ ነበሩ (ማስረጃ: ስክሪንሾት ይመልከቱ)። ተሸላሚዎቹ በዛሬው እለት በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝተው ሽልማት እንደሚወስዱ በስፋት አስተዋውቆ የመግቢያ ትኬት የሸጠ ቢሆንም በስፍራው አልተገኙም።

2. የቀድሞው ጠ/ሚር አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ ተሸላሚ እንደሆኑ በሰበር ዜና ገልፆ ነበር (ማስረጃ: https://www.facebook.com/share/p/pwqFJvcY4eFx4TjM/?mibextid=Nif5oz) እርሳቸው ግን መገኘት እንደማይችሉ ሲገልፁ ከሽልማት ዝርዝር ውስጥ እንዳልተካተቱ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። መገኘት ያልተመቸው ባይሆን በተወካይ ይወስዳል እንጂ እንዴት ከዝርዝር ይወጣል የሚለው ሌላው ጥያቄ ነው።

3. ልክ እንደ አቶ ሐይለማርያም ሁሉ የቦትስዋናው 'ሉካራ' ድርጅት ዳይሬክተር የሆኑት ናሲም ላህሪ የዘንድሮው 'ምርጥ የሴት መሪ/አመራር' ተብለው ይፋ ከተደረጉ በኋላ ማምሻውን ሽልማቱ ለከንቲባ አዳነች አቤቤ ተበርክቷል (ማስረጃ: ስክሪንሾች ተያይዟል)።

4. የትናንት ምሽቱን ፕሮግራም ወጪ የሸፈነው የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ነበር። እንደገና ይሄው መፅሄት የኮሚሽኑን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ "በመንግስት አገልግሎት ላበረከቱት አስተዋፅዖ" በሚል ሽልማት ሰጥቷል። የፕሮግራም ስፖንሰርን መልሶ መሸለም የጥቅም ግጭት መፍጠሩ የማይቀር መሆኑ ብቻ ሳይሆን እርስ በርስ መሸላለም መሆኑ ግልፅ ነው። አቶ ደበሌ ከዚሁ ተቋም የዛሬ አመት ሌላ ሽልማት ወስደው ነበር (ማስረጃ: https://www.facebook.com/share/p/cvKWKss1tzg9g66u/?mibextid=Nif5oz)

ማሳረጊያ:

አሁን አሁን እየተለመደ የመጣ ነገር ቢኖር የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅቶች "ሽልማት አገኘን" የሚል ዜና መስማት ነው። እርግጥ ነው ትክክለኛ አለም አቀፍ እውቅና የሚያገኙ እንደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይነት ተቋማት አሉ፣ ግን ሌላ ጨዋታም አለ።

ታድያ ለእንዲህ አይነት ዜና ያለውን ከፍተኛ ጥማት የተረዱት በተለይ ናይጄርያውያን እና ጋናውያን ጋዜጠኞች ተፍ ተፍ እያሉ ይገኛሉ፣ ሽልማቶችን በገፍ ያከፋፍላሉ። ከዛም ለሚድያቸው የሚሆን ለማስታወቂያ በሚል ዳጎስ ያለ ክፍያ ይቀበላሉ፣ የሽልማት ስነ-ስርዐት አዘጋጅተው አንደኛ-ሁለተኛ-ሶስተኛ ደረጃ ስፖንሰር ብለው ከፋፍለው ገቢያቸውን ያጦፋሉ።

"Breaking News! Excitement builds for the African Leadership Magazine Persons of the Year Award 2024, as His Excellency, Hailemariam Desalegn Boshe, Former Prime Minister of Ethiopia, Will be present at the 12th edition of the Annual African Leadership Persons of the year Awards themed 'Building Resilient African Economies.' Mark your calendars - March 14-15, 2024, as we illuminate the path to a dynamic future!

For registration, please visit: https://www.eventbrite.co.uk/e/the-african-leadership-magazine-persons-of-the-year-awards-ceremony-2024-tickets-764571141867

"

የሐሰት ዜና ወይም ፌክ ኒውስ ምንድነው?  የሐሰት ዜናን ማሰራጨት ከሚዲያ ጋር በተያያዘ የረጅም ጊዜ ታሪክ አለው።  እንደ ጋዜጣ መጽሔት ወይም ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ባሉ ትራዲሽናል ሚዲያዎች ትክ...
15/03/2024

የሐሰት ዜና ወይም ፌክ ኒውስ ምንድነው?

የሐሰት ዜናን ማሰራጨት ከሚዲያ ጋር በተያያዘ የረጅም ጊዜ ታሪክ አለው። እንደ ጋዜጣ መጽሔት ወይም ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ባሉ ትራዲሽናል ሚዲያዎች ትክክለኛ መረጃ የመተላለፋቸውን ያህል ሀሰተኛ መረጃዎችም በብዛት የተሠራጩባቸው በርካታ አጋጣሚዎችን መጥቀስ ይቻላል። ነገር ግን የሐሰት መረጃዎች የበለጠ መስፋፋት የጀመሩት የማህበራዊ ሚዲያው ወይም ሶሻል ሚዲያው በስፋት መሠራጨት ከጀመረበት ጊዜ ወዲህ ነው። ለመሆኑ የሐሰት መረጃ ወይም ፌክ ኒውስ እንዴት ይሰራጫል?

የሐሰት ዜና fake news ለአንባቢያንን/ ለተከታዮቻቸው የሚያሳስት ዜናን ወይም መረጃን ሆን ብሎ (intentional) የማሰራጨት ተግባር ነው።

የተሳሳተ መረጃ misinformation ስንል ግን ትክክል ወዳልሆነ ወይም ወደተሳሳተ አቅጣጫ ሊመራ የሚችል መረጃ ማለት ሲሆን፤ በታማኝ ዘጋቢዎች ስህተት ወይም ትክክለኛ ትርጉሙን ካለመረዳት ሳይታሰብበት (unintentionally) የሚሰራጭ መረጃ ነው።

የሐሰት ዜና ወይም የተሳሳተ ይዘት ያለው ኢንፎርሜሽን በንግግር፣ በጽሁፍ፣ በህትመት፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በዲጂታል ሚዲያዎች ቅርጽ ይዞ በዜና እና በተግባቦት መልኩ ሲቀርብ ነው። በተጨማሪም የሐሰት ዜና ዘገባዎች፣ ዘገባው በራሱ ፈጠራ፣ እውነታዎችን፣ የመረጃ ምንጮች ለማረጋገጥ የማይችሉ ይዘት ያለው ነው።
ሀገራችን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ የሐሰት ዜና/ወሬዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች አማካይነት በቀላሉ እና በፍጥነት ማጋራት ስለሚቻል የብዙዎችን ህይወት አደጋ ውስጥ የሚጥሉ መረጃዎች ሲሰራጩ ይስተዋላል፡፡

የሐሰት ዜናዎች እንዴት_ይፈጠራሉ?

ለምን_ይታመናሉ? ለሚለዉ ጥያቄ የሚከተሉት ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸዉ፡፡

ህዝብ ተቸገርኩበት ስለሚለው ጉዳይ ትኩረት የሚሰጥ ሲጠፋ፤ አዛኝ በመምሰልና ሰለጉዳዩ በማጋነን ደጋፊዎችን ያገኛሉ፡፡ በዚህም ማስተላለፍ የፈለጉትን መልዕክት ያስተላልፋሉ፡፡

መንግስትና የሚመለከታቸዉ አካላት ሀላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት ሳይችሉ ሲቀር፤ ክፍተቱን በመጠቀም የበለጠ ሊያራግቡት ይችላሉ፡፡

የህብረተሰቡን ክፍተት በመጠቀም፤ ይህ ምናልባት እዉነተኛን መረጃ በመያዝና የህብረተሰቡን ድክመት እንደ ክፍተት በመጠቀም እንዲሁም እዉነተኛውን መረጃ በመጠምዘዝ እነሱ የፈለጉትን ሃሳብ ሊያስተላልፉ ይችላሉ፡፡

የመረጃ ድግግሞሽ፤ አንድ መረጃ ተደጋግሞ የሚፃፍ ወይም የሚነገር ከሆነ የመታመን እድሉን እያሰፋ ይሄዳል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ብዙም ባይሆንም ጥቂት ሰዎች የሐሰት መረጃዎች ሲደጋገሙ ለማጣራት እድል ይሰጣቸዋል፡፡

ሀሰተኛ መረጃዎችን በምን መልኩ መለየት_እንችላለን?

መረጃዉን ያሰራጨዉ አካል ማን እንደሆነ እና ታማኝ መሆኑን ከቀደሙ ታሪኮቹ ማረጋገጥ፤

መረጃዉን በጥልቀት መመርመር፣ ሁሌም እጅግ በጣም መልካም ወይም እጅግ መጥፎ የሚመስሉ ጉዳዮች ተአማኒነታቸው ዝቅተኛ መሆኑን መገንዘብ፤

መረጃው የተገኘበትን ገጽ ትክክለኛነት ማረጋገጥ፣ በተሰረቀ ማንነት በመጠቀም የተሰራጨ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ፣

ዜናዉን ያቀረበዉ ገፅ መረጃዉን ከየትኛዉ የመረጃ ምንጭ እንዳገኘው እና በምን ማስረጃ እንዳቀረበዉ ማጤን፤

የተጠቀሰዉን መረጃ በአንክሮ መመልከትና የፅሁፍ መረጃ ከሆነ የአገባብ ወይም የቃላት ስህተት ያለባቸዉ ዜናዎች በአብዛኛዉ ሀሰተኛ እንደሆኑ ይታመናል፣

በመሆኑም ይህን ልብ ማለት እንዲሁም የምስል አሊያም የተንቀሳቃሽ ምስል መረጃዎችን ካሉ ደግሞ መረጃዉ የተደገፈበት ምስል ትክክለኛ መሆኑን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነዉ፤

መረጃዉ ከሚገኝበት ቦታ ወይም ከመረጃዉ ጋር ቅርብ ግንኙነት ያለዉን አካል ስለመረጃዉ ትክክለኛነት በመጠየቅ መረዳት፤

ሀሰተኛ መረጃዎች መሆናቸዉ የተረጋገጡ መረጃዎችን ለገፆች ሪፖርት ማድረግና እንዲሰረዙ/እንዲወገዱ ማድረግ ተገቢ ነዉ፡፡

Address


Telephone

+251911538731

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ነፃው ፕሬስ - Free Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ነፃው ፕሬስ - Free Press:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share