Mereja media

Mereja  media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mereja media, Media/News Company, .

የሐዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ በኑሮ ደረጃቸው ዝቅተኛ ለሆኑ አረጋዊያን ያሰራውን ቤት አስረከበ።ነሐሴ 4/2015 ዓ/ምሐዋሳበስፍራው ተገኝተው ርክክብ ያደረጉት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/...
11/08/2023

የሐዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ በኑሮ ደረጃቸው ዝቅተኛ ለሆኑ አረጋዊያን ያሰራውን ቤት አስረከበ።

ነሐሴ 4/2015 ዓ/ም
ሐዋሳ

በስፍራው ተገኝተው ርክክብ ያደረጉት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ኘ/ ጸጋዬ ቱኬ ናቸው።

ረ/ኘሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ በአስተዳደሩ ስር ለሚገኙ መምሪያዎች መሰል ተግባራትን እንዲተገብሩ በገለጹት መሰረት ዛሬ በሰላምና ጸጥታ መምሪያ ተሰርቶ የተጠናቀቀ ቤት ለርክክብ መብቃቱን ተናግረዋል።

ይህ ቤት በጥሬ ገንዘብ ብቻ ከ3 መቶ ሺህ ብር በላይ እንደፈጀ ገልጸው በከተማዋ ባለሀብቶችና ወጣቶች የተጀመሩ በጎ ተግባራት በሁሉም አካባቢ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመትም ከ2መቶ በላይ ቤቶችን ለመጠገን በዕቅድ መያዙን ነው ከንቲባ ጸጋዬ የገለጹት።

የሐዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ መኩሪያ መኒሳ በመምሪው ኮሚቴ በማወቀርና 38 ሰራተኞች 120 ሽህ ብር በማዋጣት በባህል አዳራሽ ክ/ከተማ ተለይቶ የተሰጣቸውን ቤት በሁለት ወር ውስጥ ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቅ እንደተቻለ ገልጸዋል።

ለዚህ ተግባር በርካታ ሰዎች በአይነትና በቁሳቁስ ድጋፍና ትብብር ማድጋቸውን አቶ መኩሪያ በማመስገን ጭምር ገልጸዋል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ፍሬህይወት ወ/ጻዲቅ በክረምት ከታቀዱ 17 ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የአረጋዊያን ቤት ጥገና በተለያዩ ክ/ከተማ ከ20 ቤት በላይ ለመጠገን ታቅዷል ብለዋል።

ወ/ሮ ፍሬህይወት አልቀው ያስረከብናቸው እየተጠናቀቁና በመሰራት ላይ ያሉ ቤቶች መኖራቸውን ገልጸዋል።

ቅን ልቦችን ፈጣሪ ይባርክ ያሉት ወ/ሮ ፍሬህይወት እነዚህ አረጋዊያን ሲደሰቱ ከማየት በላይ ትልቅ ደስታ የለም ብለዋል።

የቤት ርክክብ የተደረገላቸው አረጋዊያን አቶ ክብረት አሻግሬ እና ወ/ሮ አስናቀች ሀይሉ የ6 ልጆች ወላጅ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ባሉ ዓመታት በሚያፈስ፣ጎርፍ በሚገባበትና በፈራረሰ ቤት ውስጥ በችግር እየኖሩ እንደነበረ ገልጸው ይህንን ቤት ሰርተው ለሰጡን ሁሉ ፈጣሪ ይባርካቸው ሲሉ መርቀዋል አመስግነዋልም።

የመምው ም/ሀላፊና የወጣቶች ዘርፍ ሀላፊ አቶ አደራ ሀርቃ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 130 ሺህ ወጣቶች ተሳትፈው ለ270 ማህበረሰብ በመድረስ 110 ሚሊየን የመንግስት ወጪን የማስቀረት እቅድ መያዙን ገልጸዋል።

ከዚህም አንዱ በሆነው ቤት ጥገና ተግባር ዛሬ በአዲስ መልክ በመገንባት ርክክብ መደረጉን ገልጸው ሌሎችም ይህንን ተግባር እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።

Mereja media

ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በባሌና በምስራቅ ባሌ ዞኖች የስንዴ ልማትን እየጎበኙ ነው ታኅሣሥ 20፣ 2015  የግብርና ሚኒስትሩ ኡመር ሁሴን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊ...
29/12/2022

ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በባሌና በምስራቅ ባሌ ዞኖች የስንዴ ልማትን እየጎበኙ ነው

ታኅሣሥ 20፣ 2015 የግብርና ሚኒስትሩ ኡመር ሁሴን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በባሌና በምስራቅ ባሌ ዞኖች በክላስተር የለማ የስንዴ ልማትን እየጎበኙ ነው።

ሚኒስትሩ የልማት እንቅስቃሴን ከጎበኙ በኋላ በስራ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና ሊሰሩ በሚገቡ ተግባራት ላይ ከአርሶ አደሮች፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰማሩ ባለሀብቶች ጋር እንደሚመክሩ ተጠቅሷል፡፡

በምስራቅ ባሌ ብቻ በመኸሩ ወቅት ከ144 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Mereja media

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዳሴ ግድብ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገለጹነሐሴ 6፣ 2014  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል...
12/08/2022

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዳሴ ግድብ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገለጹ

ነሐሴ 6፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ሦስተኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠናቀቅን ከስፍራው ባበሰሩበት ንግግራቸው÷ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ እንዲሁም ለአፍሪካ እና ለዓለም የተሰጠ የተፈጥሮ ፀጋ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የአፍሪካ አገራት የኢኮኖሚክ ትስስርን ካፀደቁ ዓመታት ተቆጥሯል ያሉት ጠቅላይ ሚነስትሩ የኢኮኖሚክ ትስስሩ አንዱ መንገድ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለጎረቤት አገራት መሸጥ ነው ብለዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይሉ ሙሉ ለሙሉ ሲመነጭ ከጎረቤት አገራት ተሻግሮ ሊጠቅም የሚችል እንደሆነም ጠቅላይሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የህዳሴ ግድቡ ሲጠናቀቅ በጋራ የመልማት እና የማደግ እድልንም በሰፊው እንደሚሰጥ ገልፀዋል።

አያይዘውም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያረፈበት አካባቢ ተራራማና አረንጓዴ መሆኑን ገልጸው፥ይህም ለቱሪዝምና ለተለያዩ የመዝናኛ አማራጮች እንዲሁም ለዓሣ እርባታ እንደሚውል አመላክተዋል፡፡

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የዓለም ሕዝብ መጥቶ ለመዝናናት የሚያስችለው ትልቅ ስጦታ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የዓለም ሕዝቦች አስፈላጊ ነው ብለው በሚያምኑበት በማንኛውም ጊዜ በዚህ ሥፍራ መጥተው ሊዝናኑ ፣ ሊያዩ፣ ጊዜአቸውን በደስታ ሊያሳልፉ የሚያስችል ከፍተኛ ብቃት እንዳለውም ነው ያስረዱት፡፡

በግድቡ ምክንያት 70 ገደማ ደሴቶች እንደሚፈጠሩ ገልጸው፥ከ40 በላይ ደሴቶች እያንዳንዳቸው ከ10 ሔክታር በላይ ቦታ እንደሚይዙን እና አንዳንዶቹ ከ800 እስከ ከ2 ሺህ ሔክታር በላይ እንደሚሸፍኑም ጠቀመዋል።

ዝቅተኛው ደሴት 5 ሔክታር የሚይዝ ነው ብለዋል፡፡

ደሴቶቹ ከፍተኛ የመዝናኛ ሥፍራና በውኃ ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎችን ሊያስተናግዱ እንደሚችሉና ከፍተኛ የሆነ የዓሣ ምርት ማምረት እንደሚያስችሉም ነው የጠቀሱት።

Mereja media

14/07/2022
አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ  ሐምሌ 7፣ 2014  በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቀድሞው ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ...
14/07/2022

አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሐምሌ 7፣ 2014 በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቀድሞው ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

አቶ ምትኩ ካሳ እና ኢያሱ ምትኩ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

ፖሊሰ በተጠርጣሪዎቹ ላይ እስካሁን ያሰባሰባቸውን መረጃዎች እና ማስረጃዎች ለፍርድ ቤት አቅርቧል፡፡

የ10 ምስክሮችን ቃል ለመቀበል እንዲሁም በፌደራል እና በክልሎች በሚገኙ የኮሚሽኑ ቅርንጫፎች ያሉ ሰነዶች ኦዲት ለማድረግ እንዲሁም በብርበራ የተገኙ ሰነዶች እና ምንጩ ያልታወቀ የውጭ ሀገር ገንዘብን ለማጣራት እና ምርመራ ለማድረግ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡

ተጠርጣሪዎች በጠበቆቻቸው አማካኝነት በጉዳዩ ላይ የቀድሞ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና ፖሊስ የምርመራ ጊዜ ከአንድ ዓመት በፊት ያለቀ በመሆኑ ለፖሊስ እንዳይሰጥ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

ግራ ቀኙን የተመለከተው ችሎቱ ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜን የፈቀደ ሲሆን፥ ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄን ውድቅ አድርጓል።

Mereja media

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ጉዳይ ላይ ውሳኔ አሳለፈ ሐምሌ 5 ፣ 2014  የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከሰሞኑ አነጋጋሪ ሆኖ በሰነበተው የአዲስ አበባ ዩ...
12/07/2022

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ጉዳይ ላይ ውሳኔ አሳለፈ

ሐምሌ 5 ፣ 2014 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከሰሞኑ አነጋጋሪ ሆኖ በሰነበተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ5ኛ ዓመት ተማሪ ከሆነው ቢኒያም ኢሳያስ ጋር በተያያዘ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው ተማሪ ኢሳያስ የአራተኛ ዓመት ተማሪ እያለ የግራ እጁ ላይ በተፈጥሮ የአካል ጉዳት ያለበት መሆኑ በመምህራን ከተለየ በኋላ ይህ ጉዳት በህክምና ትምህርቱ ላይ ያለው ተፅዕኖ እንዲታይ ወደ ዲን ጽህፈት ቤት መርቶት እንደነበር አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጁ እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ላለፉት 8 ወራት ጉዳዩን ሲመለከቱት መቆየታቸውም ተገልጿል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው እና የጤና ሳይንስ ኮሌጁ የተማሪ ቢኒያምን ጉዳይ እንደ ተማሪ፣ እንደ አካል ጉዳተኛ እና የህሙማንን ጉዳይ በየዘርፉ ለይተው ምክክር ማድረጋቸውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱአለም ደነቀ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ከዩኒቨርሲቲው ውጪ ያሉ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላትን በማሳተፍ ውይይት መደረጉን ጠቅሰው፥ መሰረታዊ በሆኑ የህክምና ተቋማት ላይ ቴክኒካል የሆኑ አሰራሮችን መመልከት መቻሉንም አስረድተዋል።

ባገኘው አሰራርም አንድ የህክምና ባለሙያ በመሠረታዊነት መስጠት ያለበትን የህክምና እርዳታ የሚያሟላውን መስፈርት በተመለከተም፥ ተማሪ ቢኒያም በዩኒቨርሲቲው ከሚሰጡ ስምንት የቅድመ ምረቃ ትምህርቶች አምስቱን ለመማር እና ለወደፊት ሙያውን ለመተግበር እንደሚቸገር ከስምምነት ላይ መደረሱን አስረድተዋል።

ነገር ግን በሌሎች የትምህርት አይነቶች ትምህርቱን መቀጠል እንደሚችል አብራርተዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በተሰጠ ውሳኔም ዩኒቨርሲቲው ችግሩን በወቅቱ ለይቶ አማራጮችን ባለመውሰዱ እና በተማሪው ላይ ለደረሰው የሞራል ጉዳት ሃላፊነቱንይወስዳልም ነው ያሉት።

በቀጣይ ተማሪ ቢኒያም ትምህርቱን በሚከታተልበት ሂደት ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

mereja media

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰሞኑን በወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር መከሰቱን አስታወቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ሐምሌ 01 ቀን 2014 በወጣው የ20/80 እና ...
12/07/2022

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰሞኑን በወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር መከሰቱን አስታወቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 01 ቀን 2014 በወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር ድርጊት በመከሰቱ ሁኔታውን እያጣራ እንደሚገኝ እና በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን አስታወቀ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው÷ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓቱ በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ሲጀመር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነት ተገኝቶበታል፡፡

በእስካሁኑ የማጠራት ስራም ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል ነው ያለው፡፡

በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑም በመግለጫው ተመላክቷል፡፡

ከዚህ በመነሳትም “የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል” ብሏል፡፡

ሒደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማዋ ነዋሪ እንደሚያሳውቅ የገለጸው አስተዳደሩ÷ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንዲጠባበቁም ጠይቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ሀምሌ 01/ 2014 የወጣውን የ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ይመለከታል

በከተማችን አዲስ አበባ ከሚስተዋሉ ችግሮች መካከል አንዱ የቤት አቅርቦት እጥረት ሲሆን ይህንኑ ደረጃ በደረጃ ለማቃለል አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮችን ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የዚህ ሂደት አካል የሆነው የነባሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉበትን ወስብስብ ችግር ለይቶ በመፍታት ተመዝጋቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ እና የቤት እጥረት ጫና ለመቀነስ የተደረገው ሰፊ ጥረት ተጠቃሽ ነው፡፡

በዚህ ሂደት በግንባታ ላይ የነበሩ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል 25,491 ያህሉ በቅርቡ ለባለ እድለኞች የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት መካሄዱ ይታወቃል፡፡

ይህ የቤት ማሰስተላለፍ ስራ እንደ ከዚህ በፊቱ በቆጣቢወች መካከል አድሎና ብልሹ አሰራር እንዳይኖር ለማድረግ ግልፅነት በሚያሰፍን አግባብ ለማስተላለፍ ሲባል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ በመስራት ሂደቱን ግልጽና አሳታፊ ለማድረግ የተደረገው ተነሳሽነትና ጥረት እንዲሁም የባልሙያዎችን ሙያዊ ነፃነት አክብረን አስፈላጊውን ሂደት ተከትለን ተዓማኒነቱን እንዲያረጋግጡልን አድርገን ነበር፡፡

በዚህ ሂደት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲስ ሶፍትዌር እንዲበለፅግ እና ስለሶፍትዌሩ ታአማኒነት የኢኖቬንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር እንዲያረጋግጥልንም ተደርጓል፡፡

በቀጣይም ከሁለት ጊዜ በላይ ታዛቢወች እና ባለሙያወች ፊት ቀርቦ እንዲያረጋግጡልን ተደርጎ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡

ይህ ሁሉ ሂደት ከእለት ጉርሱ የቆጠበዉን እና በከፍተኛ ጉጉት የሚጠባበቀውን ሕዝብ በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ቀና ሃሳብ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል፡፡

ይሁን እንጂ ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል፡፡

በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡

ከዚህ በመነሳትም የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ስለሆነም ሂደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቀን ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማችን ነዋሪ የምናሳውቅ መሆኑን ስንገለጽ ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው ስህተት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ይጠይቃል!

mereja media

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲና ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ5 ሺህ 800 በላይ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት አበረከቱ ሰኔ 17፣ 2014  ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ...
24/06/2022

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲና ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ5 ሺህ 800 በላይ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት አበረከቱ

ሰኔ 17፣ 2014 ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 5 ሺህ 865 መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ዛሬ አበርክተዋል፡፡

''ሚሊየን መጻሕፍት ለሚሊኒየሙ ትውልድ' በሚል መሪ ቃል ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በሚከናወነው የመጻሕፍት ማሰባሰብ ንቅናቄ የተለያዩ ተቋማትና ዜጎች ተሳትፎ እያደረጉ ነው።

በዚህ መሰረትም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያሰባሰቧቸውን መጻሕፍት በዛባ ዕለት አስረክበዋል፡፡

መጻሕፍቱን የዩኒቨርሲቲውና የኮሌጁ አመራሮች ለአዲስ አበባ የባህል ኪነጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ የፅህፈት ቤት ኃላፊ ፈይሳ ፈለቀ ማስረከባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የሐረማያ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል የሱፍ÷ 4 ሺህ 334 የተለያዩ የምርምር፣ የፍልስፍና እንዲሁም የታሪክ ይዘት ያላቸው መጻሕፍትን ለአብርሆት ማስረከባቸውን ተናግረዋል ።

በተመሳሳይ የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ግሩም ግርማ ÷ኮሌጁ ከተማሪዎች፣ ከሰራተኞች እና ከተቋሙ ወዳጆች ያሰባሰባቸውን 1 ሺህ 531 መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ማበርከቱን ገልጸዋል፡፡

mereja media

በታንዛኒያ በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር ተያይዞ በእስር ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያን የጋራ መፍትሄ ለማፈላለግ ሀገራቱ ከስምምነት ደረሱ ግንቦት 4፣ 2014 የታንዛኒያ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮችን ...
13/05/2022

በታንዛኒያ በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር ተያይዞ በእስር ላይ ላሉ ኢትዮጵያዊያን የጋራ መፍትሄ ለማፈላለግ ሀገራቱ ከስምምነት ደረሱ

ግንቦት 4፣ 2014 የታንዛኒያ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮችን ያካተተ የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የለውጥ ስራዎችን ጎበኘ፡፡

ከፍተኛ አመራሮቹ በውይይታቸው ወቅት ስለ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር በተለይ ኢትዮጵያዊ ወጣቶች በኬንያና በታንዛኒያ ሀገር አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲጓዙ የሚያጋጥማቸውን አደጋና እንግልት በጋራ ለመቅረፍ የሚያስችል ተግባር ለማከናወን ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የአደገኛ እፅ ዝውውርን በጋራ ለመግታት፣ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ከታንዛኒያ ፖሊስ አካዳሚ ጋር በአቅም ግንባታ ላይ አብሮ ለመስራትና ከአንጋፋው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የተሻለ ልምድ እንዲሁም የታንዛኒያን ልምድ ለማካፈል ተስማምተዋል፡፡

ከዚህም ባሻገር ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እየተካሄደ ያለው የለውጥ ስራ በወንጀል መከላከል፣ በምርመራና በቴክኖሎጂ ተቋሙ የደረሰበት ደረጃ ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡

የታንዛኒያ ፖሊስ ልዑክ መሪ ኢንስፔክተር ጄነራል ሲሞን ኞኮሮ ስሮ በጉብኝቱ ወቅት ስለተመለከቱት የለውጥ ስራዎች ያላቸውን አድናቆት ገልፀው ፥ ለተደረገላቸው አቀባበልም ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አንድ ቡድን ወደ ታንዛኒያ ሄዶ በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ጋር ተያይዞ በእስር ላይ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች በምን ዓይነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ ለመመልከትና ከእስር አስፈትቶ ወደ አገራቸው ለማስመለስ የሚያስችል የመፍትሄ ሀሳብ በጋራ ለማፈላለግ ስምምነት ላይ የተደረሰ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በመጨረሻም የሁለቱን ሀገራት የፖሊስ ግንኙነት ለማጠናከር የመግባቢያ ሰነድ በታንዛኒያ በመፈራረም የተጀመረውን ፖሊሳዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሁለቱ ሀገራት ፖሊስ ኃላፊዎች መስማማታቸውን ከፌዴራል ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Mereja media

ጠ/ሚ ዐቢይ በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹግንቦት 5 ፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ ካሊፋ ቢን ...
13/05/2022

ጠ/ሚ ዐቢይ በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

ግንቦት 5 ፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ ካሊፋ ቢን ዛይድ አል ናህያን ህልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ለተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች አልጋ ወራሽ ሼክ ሞሃመድ ቢንዛይድ አልናህያን እንዲሁም ለተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ህዝብ የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን እገልጻለሁ ብለዋል።

Mereja media

የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘግንቦት 4፣ 2014  የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ።የ...
12/05/2022

የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ

ግንቦት 4፣ 2014 የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ።

የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን ለዚህ ታሪካዊ ላሉት ስኬት እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

የቡና ምርት ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ ከምታቀርባቸው የግብርና ምርቶች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ ቀጥሏል።

ሀገሪቱ በተለይም ወደ ቻይና የምትልከው የቡና ምርት በከፍተኛ መጠን አድጓል።

በፈረንጆቹ 2021 ዓመተ ምህረት ላይ ቻይና ከኢትዮጵያ ያስገባቸው የቡና ምርት መጠን ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ አድጓል።

በቅርቡ የኢትዮጵያን የቡና ምርት በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ የሀገሪቱ የቡና ማህበር እንዳስታወቀው፥ በቻይና ከትላልቅ ከተሞች እስከ መለስተኛ ከተሞች የቡና ተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፥ ይህም ለኢትዮጵያ ቡና አምራቾች እና ላኪዎች ሰፊ የገበያ ዕድል መፈጠሩ ተመልክቷል።

ሚኒስትሩ ባለፉት የበጀት ዓመቱ ወራት የተገኘው የውጭ ምንዛሪ ምን ያህል የቡና መጠን ወደ ውጭ ተልኮ እንደሆነ አልጠቆሙም።

Mereja media

በሐረር በአንድ ሆቴል ውስጥ በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት ተጠርጣሪዎች ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው ነው - የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ሚያዝያ 18፣ 2014  በሐረር ከተማ ልዩ ስሙ ሸንኮር ቀ...
26/04/2022

በሐረር በአንድ ሆቴል ውስጥ በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት ተጠርጣሪዎች ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው ነው - የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን

ሚያዝያ 18፣ 2014 በሐረር ከተማ ልዩ ስሙ ሸንኮር ቀበሌ 09 በአንድ ሆቴል ውስጥ በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት አራት ተጠርጣሪዎች ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነስሪ ዘከሪያ ጥቃቱን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ÷ በትንሳኤ ዕለት እሁድ ከምሽቱ 2:45 ላይ በሸንኮር ወረዳ ቀበሌ 09 ዮድ ተብሎ በሚጠራው ሆቴል ላይ ማንነታቸው ለጊዜው ያልታወቀ ግለሰቦች በወረወሩት ቦምብ በስምንት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።

የጥቃቱ ሰላባ ከሆኑት ስምንት ግለሰቦች መካከል አራቱ መጠነኛ ሕክምና ተደርጎላቸው ወዲያው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ጠቁመው÷ ቀሪዎቹም በአስጊ ሁኔታ ላይ አለመሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም ጥቃቱን በተመለከተ ኃላፊነት የጎደላቸው አንዳንድ ግለሰቦች ከእውነታው በራቀ እና በምርመራ ላይ ያለን ጉዳይ÷ ባሻቸው መልኩ በማቅረብ ሀሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ እንደሚገኙ በመግለጫቸው አንስተዋል።

ጠብ አጫሪ በሆነ መልኩ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የሚያጋሩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰባቸውን የሐረሪ ክልል ብዙኃን መገናኛ ዘግቧል፡፡

ፖሊስ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን የጠቆሙት ኮሚሽነሩ÷ ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ አራት ግለሰቦች ተጠርጥረው ምርመራ እየተደረገባቸው ሲሆን የምርመራ ውጤቱ እንደተጠናቀቀ ለህብረተሰቡ ይፋ ይደረጋል ብለዋል።

mereja media

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ  ታላቅ የኢፍጣር መርሐ ግብር ተካሄደሚያዝያ 18፣ 2014  በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሺህዎች የሚቆጠሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ደማቅ  የጎዳና ላይ የኢፍጣር መርሐ ...
26/04/2022

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ታላቅ የኢፍጣር መርሐ ግብር ተካሄደ

ሚያዝያ 18፣ 2014 በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሺህዎች የሚቆጠሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ደማቅ የጎዳና ላይ የኢፍጣር መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

በመርሐ ግብሩ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር መሀመድ ኑርዬ እና የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃሩና አሕመድን ጨምሮ የዞን እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም በርካታ የእስልምና እና የክርስትና እምነት ተከታዮች ተሳትፈዋል።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር መሀመድ ኑርዬ በመርሐ ግብሩ ባደረጉት ንግግር÷ የረመዳን ወር የአንድነትና የመተሳሰብ ወር በመሆኑ አቅመ ደካሞችን መደገፍ አለብን ብለዋል።

የረመዳን ወር የመቻቻል፣ የመከባበርና የአንድነት ወር በመሆኑ÷ ሕዝበ ሙስሊሙ አንድነቱን ማጠናከር እንዳለበት እና ይህን በጎ ወር ለጥሩ ነገር መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃሩና አሕመድ÷ ይህን ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

Mereja media

በሐረር 10 ሺዎች የተሳተፋትበት የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሄደአዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረር ከተማ በ10ሺዎች የሚቆጠሩ የእስልምና ተከታዮች እና የሌሎች እምነቶች አባ...
17/04/2022

በሐረር 10 ሺዎች የተሳተፋትበት የጎዳና ላይ ኢፍጣር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረር ከተማ በ10ሺዎች የሚቆጠሩ የእስልምና ተከታዮች እና የሌሎች እምነቶች አባቶች የተገኙበት የጎዳ ላይ ኢፍጣር ተካሄደ ።

በኢፍጣር ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ የእስልምና እምነት አባቶች "ቅዱሱን የረመዳን ወር ስንፆም ሚስኪኖችን በማሰብ በመርዳት መሆን አለበት" ብለዋል።

የረመዳን ወርን በመተጋገዝና በመረዳዳት እያሳለፉ እንደሚገኙ የገለፁት ምእመናን በበኩላቸው፥ ቀሪውን የፆም ጊዜ ይህኑን የመተሳሰብ እሴት ሀይማኖቱ በሚፈቅደው ሁሉ አጠናክረው ለመቀጠል ገብተዋል።

የኢፍጣር መርሃ ግብሩ በከተማው ከሚገኘው ራስ ሆቴል እስከ እስከ ሀረር ከተማ ማዘጋጃ ቤት ድረስ ነው የተካሄደው።

mereja media

ገንዘብ እናባዛለን በሚል ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ለማጭበርበር የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉሚያዝያ 6፣ 2014  ገንዘብ እናባዛለን ብለው ከአንድ ግለሰብ ላይ ከ1 ነጥብ 5 ሚ...
14/04/2022

ገንዘብ እናባዛለን በሚል ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ለማጭበርበር የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ሚያዝያ 6፣ 2014 ገንዘብ እናባዛለን ብለው ከአንድ ግለሰብ ላይ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ለማጭበርበር የሞከሩ ግለሰቦችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ተጠርጣሪዎቹ ሚያዚያ 5 ቀን 2014 ዓ.ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ቦታው ቦሌ ሆምስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው በቁጥጥር የዋሉት፡፡

አንድ ግለሰብ በአጋጣሚ ለተዋወቁት ሰው ገንዘብ እንደቸገራቸው ከነገሩት እና ይህ ሰውም "ገንዘብ የሚያባዛ ሰው አውቃለሁ፤ ችግር የለም ያባዛሎታል" ካላቸው በኋላ ነበር የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው፡፡

ገንዘብ ቸግሮኛል ያሉት ግለሰብ እንዲባዛልኝ ብለው ለተጠርጣሪዎቹ 2 ሚሊየን ብር ስለመስጠታቸው በምርመራ ወቅት መግለፃቸውን ተመላክቷል፡፡

ገንዘብ እንዲባዛ አደርጋለሁ ያለው ተጠርጣሪ የናይጄሪያ ዜግነት ካለው ግብረአበሩ ጋር በመሆን የወንጀል ድርጊቱን ለመፈፀም በዝግጅት ላይ እያሉ ፖሊስ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ ገንዘብ ይባዛበታል በተባለው ቤት ውስጥ በህግ አግባብ ብርበራ መከናወኑን ፖሊስ ገልጿል፡፡

በተደረገው ብርበራም ግለሰቡ እንዲባዛላቸው ሰጥቻለሁ ካሉት 2 ሚሊየን ብር ውስጥ 1 ሚሊየን 555 ሺህ 8 00 ብር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

በተጨማሪም በብር መጠን የተቆራረጠ በርካታ ወረቀት፣ ኬሚካል እና ማተሚያ ማሽን መያዙን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራው የቀጠለ ሲሆን ÷ፖሊስ ገንዘብ ይባዛበታል ወደ ተባለው ቤት ለብርበራ በሄደበት ወቅት ተጠርጣሪዎቹ ማስረጃ ለማጥፋት በማሰብ በብር መጠን ተቆራርጦ የተቀመጠውን ወረቀት በእሳት ለማቃጠል እና የጣራ ቆርቆሮ ገንጥለው ለማምለጥ መሞከራቸው ታውቋል፡፡

የሀገርን ኢኮኖሚ ለመጉዳት የሚፈፀሙ ልዩ ልዩ ህገ-ወጥ ተግባራት በህብረተሰቡ እና በፀጥታ አካላት ትብብር እየከሸፉ እንደሚገኙ የጠቀሰው ፖሊስ÷በተለይም ከበዓላት መቃረብ ጋር ተያይዞ ሃሰተኛ ገንዘቦችን ወደ ገበያ ውስጥ ለማሰራጨት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በተቀናጀ መንገድ በቁጥጥር ስር ማዋል እንደሚገባ እና ህብረተሰቡም አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚጠበቅበት ጥሪ አቅርቧል፡፡

mereja media

የሰብዓዊ ዕርዳታ የጫኑ 47 የጭነት ተሸከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እየተጓዙ ነውሚያዝያ 6፣ 2014 በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ሥር የሚንቀሳቀሰው የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስተባባሪ...
14/04/2022

የሰብዓዊ ዕርዳታ የጫኑ 47 የጭነት ተሸከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እየተጓዙ ነው

ሚያዝያ 6፣ 2014 በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ሥር የሚንቀሳቀሰው የዓለም ምግብ ፕሮግራም አስተባባሪነት 47 የሰብዓዊ ዕርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እየተጓዙ መሆኑን ድርጅቱ ገለፀ፡፡

እየተጓጓዘ ያለው የሰብዓዊ ዕርዳታም ÷ ምግብ፣ ዓልሚ ምግቦችን እና ሌሎች ሕይወት አድን ቁሳቁሶችን እንዳካተተ ነው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ያስታወቀው።

ከምግብ እና መሰል አቅርቦቶች በተጨማሪ 3 የነዳጅ ቦቴዎች በማጓጓዝ ሂደቱ ለተሸከርካሪዎቹ ለጥቅም እንዲውሉ ታስቦ አብረው ወደ ትግራይ ክልል እየተንቀሳቀሱ እንደሆነም ነው ድርጅቱ በትዊተር ገጹ ያመላከተው፡፡

mereja media

የአዋሽ 2 -  አሰላ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ጥገና ተጠናቀቀሚያዝያ 2፣ 2014 በዘራፊዎች ተቆርጦ የወደቀው ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰ...
10/04/2022

የአዋሽ 2 - አሰላ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ጥገና ተጠናቀቀ

ሚያዝያ 2፣ 2014 በዘራፊዎች ተቆርጦ የወደቀው ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን በእንጨት ምሰሶ የመተካት ሥራ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም በዶዶታ ወረዳ እና ጌራ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው የምሰሶ አካላት ዝርፊያ ሁለት ምሰሶዎች የወደቁ ሲሆን ÷በአካባቢው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ መቆየቱ ይታወሳል።

ለቀናት ሲከናወን የቆየው ጥገና ዛሬ በመጠናቀቁም ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ እንደሚከናወን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

mereja media

10/04/2022

በጅማ ከተማ አዲስ ደረቅ ወደብና ተርሚናል ሊገነባ ነው

መጋቢት 30፣ 2014 የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ዘጠነኛ የደረቅ ወደብና ተርሚናል መዳረሻውን በጅማ ከተማ እንደሚገነባ አስታወቀ፡፡

በጅማ ከተማ የሚገነባው ደረቅ ወደብና ተርሚናል በምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል ለሚገኙ ተገልጋዮች በቅርበት አገልግሎት በመስጠት የወጪና ገቢ ንግዱን ለማሳለጥ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

በተለይ አካባቢው በቡናና በሌሎችም የግብርና ምርቶች በእጅጉ የሚታወቅ በመሆኑ እነዚህ የግብርና ምርቶች ቀልጣፋ የሎጂስቲክስ አገልግሎት አግኝተው ለውጭ ገበያ እንዲደርሱ በማስቻል ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡

የጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክና አየር መንገድን ማዕከል አድርጎ ከጅማ ወደ ቦንጋ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ ለደረቅ ወደቡ ግንባታ የሚሆን 20 ሄክታር መሬት መመረጡን ከባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ድርጅቱ ለመሬቱ የካሳ ክፍያና መሰል ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት ሂደት ላይ እንደሆነና የመሬት ርክክቡ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚከናወን መሆኑን በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የወደብና ፋሲሊቲ ልማት መምሪያ ኢንጂነር አሰፋ ወርቅነህ ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ስምንት ወደብና ተርሚናሎች ያሉት ሲሆን በጅማ ከተማ የሚገነባው ዘጠነኛው መሆኑ ታውቋል፡፡

mereja media

በቡራዩ ከተማ በሸኔ ሎጅስቲክስ አቅራቢነት በተጠረጠረች ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ከባድ መሳሪያና ጥይቶች ተያዙ መጋቢት 22፣ 2014  በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ ነ...
31/03/2022

በቡራዩ ከተማ በሸኔ ሎጅስቲክስ አቅራቢነት በተጠረጠረች ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ከባድ መሳሪያና ጥይቶች ተያዙ

መጋቢት 22፣ 2014 በኦሮሚያ ክልል ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ ነዋሪ በሆነች እና በሸኔ የሽብር ቡድን የሎጀስቲክስ አቅራቢነት በተጠረጠረች ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ከባድ መሳሪያና ጥይቶች ተያዙ።

የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ያካሄደውን ክትትልና ጥቆማ ለኦሮሚያ ፖሊስ በሰጠው መሰረት ተጠርጣሪዋ በቁጥጥር ስር እንድትውል መደረጓ ተገልጿል።

በተጠርጣሪዋ መኖሪያ ቤት ውስጥም በተደረገ ፍተሻ በምስራቅ ወለጋ ዞን ለሚንቀሳቀሰው የሸኔ የሽብር ቡድን ለማቀበል በዝግጅት ላይ የነበረ አንድ ብሬን ከ426 ጥይት እና 10 የብሬን ጥይት ማስቀመጫ ሰንሰለት ጋር እንዲሁም 179 የክላሽ ጥይት በቁጥጥር ስር እንዲውል መደረጉንም ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Mereja media

በሀገር ውስጥ የዘረ-መል ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር ተገለጸ መጋቢት 19፣ 2014  በሀገር ውስጥ የዘረ-መል (ዲ ኤን ኤ) ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ፌዴ...
28/03/2022

በሀገር ውስጥ የዘረ-መል ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር ተገለጸ

መጋቢት 19፣ 2014 በሀገር ውስጥ የዘረ-መል (ዲ ኤን ኤ) ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል እንደገለጹት ፥ አዳዲስ የፎረንሲክ ምርመራ ማሽኖችን ተቋሙ ወደ ሀገር አስገብቶ ጥቅም ላይ እያዋለ ነው።

በአስር ዓመቱ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ከአፍሪካ ምርጥ አምስት የፖሊስ ተቋማት አንዱ ሊሆን በለውጥ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሰራሮቹን በቴክኖሎጂ እያዘመነ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በዚህም ከዚህ ቀደም ወደ ሌላ ሀገራት ተልኮ ይደረግ የነበረው የዲ ኤንኤ ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ይደረጋል ብለዋል።

ከቴክኖሎጂ ባለፈ ፖሊስ ውጤታማ ስራ ለመስራት ያስችለው ዘንድ አዳዲስ አደረጃጀቶች ማዋቀሩን ኮሚሽነር ጄነራሉ ገልጸዋል።

አዳዲሶቹ አደረጃጀቶች እያደገ የመጣውን የአየር እና የየብስ ትራንስፖርት ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ናቸው ተብሎላቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ኢንዱስትሪዎችንና ዩኒቨርሲቲዎችን ትኩረት አድርገው መዋቀራቸውን አስታውቀዋል።

አዳዲሶቹ አደረጃጀቶች የአቪየሽን ፖሊስ፣ የምድር ባቡር ፖሊስ፣ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ እንዲሁም በኢንዱስትሪ እና ቱሪዝም ላይ ትኩረት አድርጎ የሚከታተል የፖሊስ ክፍሎች ናቸው።

mereja media

ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው ሰመራ ከተማ ለተጠለሉ  ዜጎች ድጋፍ ተደረገ መጋቢት 19፣ 2014  ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ለተጠለሉ ዜጎች ድጋፍ ተደረገ፡፡ድጋፉን ዓ...
28/03/2022

ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው ሰመራ ከተማ ለተጠለሉ ዜጎች ድጋፍ ተደረገ

መጋቢት 19፣ 2014 ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ለተጠለሉ ዜጎች ድጋፍ ተደረገ፡፡

ድጋፉን ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመሆን ለ9 ሺህ ዜጎች ነው ያደረገው፡፡

ድጋፉም የስንዴ ዱቄት፣ አተር ክክ፣ የማዕድ ጨው እና የምግብ ዘይትን ያካተተ መሆኑን ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

mereja media

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ መጋቢት 19 ፣ 2014  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ...
28/03/2022

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ

መጋቢት 19 ፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጂቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ።

የጂቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል።

ፕሬዚዳንቱ ዛሬ የኢትዮጵያ የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና መስሪያ ቤትን ጎብኝተዋል።

ከጉብኝቱ በኋላ የሁለቱ አገራት መሪዎች በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

በውይይታቸው ወቅትም የንግድ፣ የግብርና መዋዕለ ንዋይ ፍሰት፣ የጋራ መሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ ቱሪዝም፣ ኢነርጂ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ባማከለ መልኩ ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ መክረዋል።

Mereja media

"የአዲስ አበባ የእሁድ ገበያ ተጠናክሮ ቀጥሏል"  -ከንቲባ አዳነች አቤቤመጋቢት 18፣2014  የአዲስ አበባ ከተማ የእሁድ ገበያ ተጠናክሮ  መቀጠሉን የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡...
27/03/2022

"የአዲስ አበባ የእሁድ ገበያ ተጠናክሮ ቀጥሏል" -ከንቲባ አዳነች አቤቤ

መጋቢት 18፣2014 የአዲስ አበባ ከተማ የእሁድ ገበያ ተጠናክሮ መቀጠሉን የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡

ከተጀመረ ወራትን ያስቆጠረው የእሁድ ገበያ አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት በከተማዋ የኑሮ ውድነትን ለማቃለልና የግብይት ስርዓቱን ጤናማ ለማድረግ እንደሚያግዝ ከንቲባዋ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

የግብርና ምርቶች በተለይም አትክልት፣ ጥራጥሬ፥ የመኸር ሰብል እና የፋብሪካ ምርቶች በተሻለ አቅርቦትና በተመጣጣኝ የገበያ ዋጋ ለሸማቾች እየቀረበ እንደሚገኝም ገልፀው ነበር።

በዛሬው ዕለትም የአዲስ አበባ የእሁድ ገበያ ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ያሰፈሩት፡፡

የከተማው አስተዳደሩ በቀጣይም አምራቹ እና ሸማቹ በቀጥታ የሚገበያዩበትን ጤናማ የንግድ ስርዓት ለመፍጠር የጀመርናቸውን መሰል ተግባራት አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናልም ብለዋል ከንቲባዋ።

Mereja media

ማህበረሰቡ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናውን እየጠበቀ የእግርና ሳይክል ጉዞን እንዲያጎለብት ተጠየቀ መጋቢት 18፣ 2014 የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ማህበረሰቡ በአካ...
27/03/2022

ማህበረሰቡ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናውን እየጠበቀ የእግርና ሳይክል ጉዞን እንዲያጎለብት ተጠየቀ

መጋቢት 18፣ 2014 የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ማህበረሰቡ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናውን እየጠበቀ የእግርና የሳይክል ጉዞን እንዲያጎለብት ጠይቀዋል፡፡

በድሬደዋ አስተዳደር ሳምንታዊ ከተሽከርካሪ ነፃ የብስክሌተኞች እና የእግረኞች ቀን ማስጀመሪያ መርሀ ግብር የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ ሚንስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እና የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

በዚሁ ወቅት ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እንደገለጹት÷ እንደ ሀገር እየጨመረ የመጣውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል አማራጭ ስትራቴጂ ተወስዶ እየተተገበረ ያለውን የሞተር አልባ ትራንስፖርት ስትራቴጂን ማህበረሰቡ ውስጥ ለማስረፅ እየተሠራ ነው፡፡

በመላው ሀገሪቱ ወርሃዊ የንቅናቄ ስራዎችን በማከናወን የህብረተሰቡን በእግር እና በሳይክል የመጠቀም ባህል ለማጎልበት ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው÷ በዚህም አዎንታዊ ለውጥ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡

ድሬ ዳዋ ከተማም ለመጀመሪያ ጊዜ በመላው የአስተዳደሩ ክልል ሳምንታዊ የሞተር አልባ የእግረኞች እና ብስክሌተኞች ቀንን አውጃለች ብለዋል፡፡

የህብረተሰባችን ጤና ያሳስበናል ያሉት ከንቲባው፥ ለዚህም የእግር እና የሳይክል ጉዞ ባህል እንዲጎለብት እና የትራፊክ አደጋ እንዲገታ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ያለን ትብብርና ትስስር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

የድሬዳዋ ከተማ በየሳምንቱ እሁድ ከጥዋት 12 ሰዓት እስከ 6 ሰአት የከተማዋ ጎዳናዎች ከድንገተኛ አገልግሎት እና ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች ውጭ ከተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ነጻ በመሆን ለእግረኞች እና ብስክሌተኞች ብቻ ክፍት ይሆናል መባሉን ከትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የተገኝው መረጃ ያመላክታል፡፡

mereja media

በህልውና ዘመቻው በጀግንነት ለተሰዉ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የሚሊሻ አባላት እና ቤተሰቦቻቸው የእውቅና መርሀ ግብር ተካሄደመጋቢት 18፣2014 በህልውና ዘመቻው በጀግንነት ለተሰዉ እና...
27/03/2022

በህልውና ዘመቻው በጀግንነት ለተሰዉ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የሚሊሻ አባላት እና ቤተሰቦቻቸው የእውቅና መርሀ ግብር ተካሄደ

መጋቢት 18፣2014 በህልውና ዘመቻው በጀግንነት ለተሰዉ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው በምስራቅ አማራ ለሚገኙ የሚሊሻ አባላት እና ቤተሰቦቻቸው ከ27 ሚሊየን 600 ሺህ ብር በላይ የማበረታቻ ገንዘብ ሰጦታና የእውቅና መርሀ ግብር በሸዋሮቢት ከተማ ተካሄደ።

በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአማራ ክልል ሚሊሻ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኮሎኔል ባምላኩ አባይ÷ የሽብር ቡድኑ ህወሃት የተለያዩ አካባቢዎችን ሲወር በሰላሙ ገዜ የልማት አርበኛ የሆነው የሚሊሻ ኃይል ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ከፍተኛ መስዕዋትነት በመክፈል አሸባሪውን ቡድን አይቀጡ ቅጣት ቀጥቷል ነው ያሉት።

ለሀገርና ለወገናቸው ሲሉ መስዋትነት ለከፈሉ ለእዚህ የሚሊሻዎች እውቅና ለመስጠት በሸዋሮቢት ከተማ ከ12 ወረዳዎች ለተውጣጡ ከ220 በላይ የሚሊሻ ቤተሰቦችና አባላት ከ27 ሚሊየን 600 ሺህ ብር በላይ ተበርክቷል ብለዋል፡፡

የተሰጠው እውቅና ለከፈሉት የህይወት መሰዋትነትና ጀግንነት የሚተካ ሳይሆን መንግስት ውለታቸውን መቼም እደማይረሳ ለመግለፅ ነው ብለዋል።

ይህ የእውቅናና ምስጋና መርሀ ግብር ለነባሩና አሁን በአዲስ እየተቀላቀለ ላለው የሚሊሻ ኃይል በቀጣይ ለሀገራቸው ሰላምና ደህንነት የበለጠ እዲሰሩ የሚያበረታታ መሆኑንም ገልጸዋል።

እውቅናውን ያገኙት በጀግንነት የተሰዉ የሚሊሻ ቤተሰቦችና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሚሊሻዎችም መንግስት ለሀገርና ለወገን ሲሉ መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖችን በዚህ መልኩ ማገዙ የሚያሰመሰግነው እንደሆነ ተናግረዋል ።

mereja media

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ፈረስ ስፖርት ቻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አስመዘገበች መጋቢት 18: 2014 ኢትዮጵያ በአልጀሪያ ኦራን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ፈረስ ስፖርት ቻምፒ...
27/03/2022

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ፈረስ ስፖርት ቻምፒዮና የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አስመዘገበች

መጋቢት 18: 2014 ኢትዮጵያ በአልጀሪያ ኦራን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ፈረስ ስፖርት ቻምፒዮና በመጀመሪያ ጊዜ ተሳትፎዋ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አግኝታለች።

ከቤካ ፈርዳ የፈረስ ስፖርት ክለብ የተገኘው ታዳጊ ፈጠነ ተሾመ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፏል::

ሜዳሊያው የተመዘገበው ከ12-14 የዕድሜ ክልል በተካሄደው የመሰናክል ዝላይ ውድድር ሲሆን በውድድሩ አራት ታዳጊ አትሌቶችን ተሳታፊ ሆነዋል።

በቻምፒዮናው እድሜቻው ከ18 አመት በታች የሆኑ 7 ታዳጊዎች ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ላለፉት 2 አመታት በውድድሩ ለመሳተፍ የኢትዮጵያ ፈረስ ስፖርት አሶስዬሽን የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቷል።

Mereja media

አገር አቀፍ የሕፃናት ፓርላማ ተመሰረተመጋቢት 18፣ 2014 በኢትዮጵያ በአዲስ መልክ የተደራጀ አገር አቀፍ የሕፃናት ፓርላማ ተመሰረተ።ፓርላማው ከዚህ በፊት ሞዴል የሕፃናት ፓርላማ በሚል ተቋ...
27/03/2022

አገር አቀፍ የሕፃናት ፓርላማ ተመሰረተ

መጋቢት 18፣ 2014 በኢትዮጵያ በአዲስ መልክ የተደራጀ አገር አቀፍ የሕፃናት ፓርላማ ተመሰረተ።

ፓርላማው ከዚህ በፊት ሞዴል የሕፃናት ፓርላማ በሚል ተቋቁሞ የነበረ ሲሆን÷ ዛሬ ጠንካራ አደረጃጀት ፈጥሮ በአዲስ መልክ ተቋቁሟል ተብሏል፡

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደው የምስረታ ሂደት ከሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የተውጣጡ አባላት ተሳትፈዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንዲሁም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ሌሎች የሥራ ሃላፊዎችም ተገኝተዋል።

የሕፃናት ፓርላማው በተለይም የህጻናት መብቶችና ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚሰራ ይሆናል መባሉን ኢዜአ ዘግቧል።

ከሕፃናት መብቶች ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸውን ህጎችና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች በማስገንዘብ ረገድም የሕጻናት ፓርላማው ጉልህ ሚና ይኖረዋል ነው የተባለው።

mereja media

የፑቲን ስልጣን የሚወሰነው በመረጧቸው ሩሲያውያን እንጂ በባይደን አይደለም - የክሬምሊን ቃል አቀባይ መጋቢት 18፣ 2014 የፕሬዚዳንት ፑቲን ስልጣን የሚወሰነው በመረጧቸው ሩስያውያን እንጂ ...
27/03/2022

የፑቲን ስልጣን የሚወሰነው በመረጧቸው ሩሲያውያን እንጂ በባይደን አይደለም - የክሬምሊን ቃል አቀባይ

መጋቢት 18፣ 2014 የፕሬዚዳንት ፑቲን ስልጣን የሚወሰነው በመረጧቸው ሩስያውያን እንጂ በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አይደለም ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሜትሪ ፔስኮቭ ተናገሩ፡፡

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በፖላንድ ከዩክሬን ባለስልጣናት ጋር በነበራቸው ውይይት፥ ፑቲን በስልጣን ላይ መቆየት የለባቸውም ማለታቸውን ተከትሎ ነው ክሬምሊን ይህን ምላሽ የሰጠችው፡፡

የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሜትሪ ፔስኮቭ ከሮይተርስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፥ ፕሬዚዳንት ፑቲን በስልጣን የሚቆዩት ወይም የሚወርዱት በባይደን በጎ ፈቃድና አስተያየት ሳይሆን በመረጣቸው የሩስያ ሕዝብ ውሳኔ ብቻ ነው ብለዋል፡፡

“በዩክሬን ላይ ያካሄዱት ወረራ የፑቲን የመወሰን አቅም ደካማ መሆኑን የሚያሳይ ነው” ያሉት ፕሬዚዳንት ባይደን፥ በሩስያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ላይ የሚያደርጉትን ውረፋና የማጣጥል ዘመቻ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡

ቀደም ሲል ፕሬዚዳንት ባይደን “ፑቲን የጦር ወንጀለኛ ናቸው” ማለታቸውን ተከትሎ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሜትሪ ፔስኮቭ በሰጡት ምላሽ፥ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን የገደለች እና ሀገራትን የወረረች አሜሪካ ፑቲንን የጦር ወንጀለኛ የማለት ሞራል የላትም ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ወራትን ባስቆጠረው ሩስያ-ዩክሬን ጦርነት፥ ሩስያ ወታደራዊ ዘመቻዋን አጠናክራ የቀጠለች ሲሆን የምዕራብ ዩክሬኗን ከተማ ሊዩቭን በሮኬት መደብደቧ ተነግሯል፡፡

የሩስያ ኃይሎች የኒውክሌር ጣቢያ ሰራተኞች የሚኖሩባትን ስላቫቲች ከተማን እንደተቆጣጠሩ የሩስያ መከላከያ ሚኒስትር ሰርጌይ ሾይጉ ገልጸዋል፡፡

የዩክሬን ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው፥ ወረራውን ለመግታት ምዕራባውያን የወታደራዊ ጦር መሳሪያዎችን ብቻ ሳይሆን መገጣጠሚያዎችን ጭምር እንዲልኩላቸው ጠይቀዋል፡፡

ባሁኑ ወቅትም የዩክሬን ወታደሮች በዋና ከተማዋ ኪየቭ ዙሪያ ባሉ አካባቢዎች በሰፈሩ የሩስያ ወታደራዊ ኃይሎች ላይ የመልሶ ማጥቃት እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውን ነው የተናገሩት፡፡

የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትሬስ ደግሞ ሞስኮ ሙሉ በሙሉ የተኩስ አቁም ስምምነት ካደረገች እና ወታደሮቿን ጠቅልላ ከዩክሬን የምታስወጣ ከሆነ ዩናይትድ ኪንግደም በሩስያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ትችላለች ነው ያሉት፡፡

ከተጀመረ 32 ቀናትን ያስቆጠረው የሩስያ-ዩክሬን ጦርነት፥ 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ዜጎች ከዩክሬን እንዲሰደዱ ማድረጉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል፡፡

6 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ደግሞ አንፃራዊ ሰላም ወዳለባቸው የዩክሬን አካባቢዎች የፈለሱ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ 90 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች እና ሕፃናት መሆናቸው ነው የተገለፀው፡፡

Mereja media

ህገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪ ግለሰብ ከ25 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጦች ጋር በቁጥጥር ስር ዋለ መጋቢት 17፣ 2014 አንድ ህገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪ ግለሰብና ግብረ አበሩ ከ25 ቱርክ ሰ...
26/03/2022

ህገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪ ግለሰብ ከ25 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጦች ጋር በቁጥጥር ስር ዋለ

መጋቢት 17፣ 2014 አንድ ህገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪ ግለሰብና ግብረ አበሩ ከ25 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጦች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

መነሻቸውን ከአማራ ክልል ባሕርዳር ከተማ ያደረጉት ህገ ወጥ የጦር መሣሪያ አዘዋዋሪውና ግብረ አበሩ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ3 A03861 በሆነ አፍሪካ ባስ በተባለ የህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት በቁጥር 25 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጦች በመጫን እያሽከረከሩ መዳረሻቸውን አዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ በመጓዝ ላይ እያሉ በተደረገ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ግለሰቦቹ በአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተብሎ በሚጠራው ልዩ ቦታ ሲደርሱ ከነጦር መሣሪያቸው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል።

Mereja media

በ40 ቀናት ውስጥ በ10 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው ልዩ ትምህርት ቤት ተመረቀ  መጋቢት 17፣ 2014 በጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ በ40 ቀናት ውስጥ ግንባታው የተጠናቀቀው ልዩ ትምህርት ቤ...
26/03/2022

በ40 ቀናት ውስጥ በ10 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው ልዩ ትምህርት ቤት ተመረቀ

መጋቢት 17፣ 2014 በጅማ ዞን ሸቤ ሶምቦ ወረዳ በ40 ቀናት ውስጥ ግንባታው የተጠናቀቀው ልዩ ትምህርት ቤት ተመረቀ።

በኦሮሚያ ልማት ማህበር 10 ሚሊየን ብር በሆነ ወጪ ከ40 ቀናት በፊት ግንባታው የተጀመረው የሸቤ ልዩ ትምህርት ቤት በዛሬው ዕለት የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አባዱላ ገመዳ በተገኙበት ተመርቋል።

በጅማ ዞን የሸቤ ሶምቦ ወረዳ እንደ ክልል ብዙ ተማሪዎችን ወደ አዳሪ ትምህርት ቤት በማስገባት የላቀ አፈፃፀም ማስመዝገቡን ተከትሎ ተገንብቶ ለወረዳው ህዝብ የተበረከተ መሆኑን አቶ አባ ዱላ ገመዳ ገልፀዋል።

ትምህርት የሁሉም ነገር መሰረት መሆኑን የተናገሩት አቶ አባ ዱላ ፥ ትምህርትና ቴክኖሎጂ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ ነው ብለዋል።

ስንጀምር በ40ቀናት ውስጥ ሰርተን እናጠናቅቃለን ባልነው መሠረት ቃላችንን ጠብቀናል ፥ የኦሮሚያ ልማት ማህበር ትምህርት ቤቶችን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ግንባታዎችንም በ40 ቀን ውስጥ ሰርቶ አጠናቆ ለአገልግሎት እያበቃ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

የኦሮሚያ ልማት ማህበር ቀኝ እጃችን ነው ያሉት የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ፥ ትምህርት ቤት ከመገንባት በተጨማሪ የዞኑ ተማሪዎች ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትልቅ ስራ ተሰርቷል ነው ያሉት።

Mereja media

Address


Telephone

+251918997611

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mereja media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share