Mereja media

Mereja  media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mereja media, Media/News Company, .

በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ አሰተዳደር በፋራ ቀበሌ መንገድ ከፈታ ስራ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥለዋል።የታቦር ክ/ከተማ መ/ኮሙኒኬሽን ጰጉሜ 01-2016 ዓ.ም         Mereja media
06/09/2024

በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ አሰተዳደር በፋራ ቀበሌ መንገድ ከፈታ ስራ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥለዋል።

የታቦር ክ/ከተማ መ/ኮሙኒኬሽን
ጰጉሜ 01-2016 ዓ.ም
Mereja media

በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ አሰተዳደር በፋራ ቀበሌ መንገድ ከፈታ ስራ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥለዋል።የታቦር ክ/ከተማ መ/ኮሙኒኬሽን ጰጉሜ 01-2016 ዓ.ም         Merja media
06/09/2024

በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ አሰተዳደር በፋራ ቀበሌ መንገድ ከፈታ ስራ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥለዋል።

የታቦር ክ/ከተማ መ/ኮሙኒኬሽን
ጰጉሜ 01-2016 ዓ.ም
Merja media

በታቦር ክ/ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ተካሄደ። ዛሬ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ የተካሄደ ሲሆን የክ/ከተማ አመራርሮች፣ የቀበሌ አመራር እና ነዋሪ...
23/08/2024

በታቦር ክ/ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ተካሄደ።

ዛሬ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ የተካሄደ ሲሆን የክ/ከተማ አመራርሮች፣ የቀበሌ አመራር እና ነዋሪዎች ፣ የሀገር የሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተው የአረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።

የታቦር ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ተስፋዬ አባይነህ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩን ሲያስጀምሩ እንደገለፁት የአረንጓዴ አሻራ የመተባበር እና የአንድነት ውጤት ማሳያ ነው ሲሉ ገልፀው በቀጣይም ህብረተሰቡ የተተከለውን ችግኞች የመንከባከብ ተግባር ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የታቦር ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ መስከረም ላሌ በበኩላቸው መርሀ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት እየተናወነ እንደሚገኝ ገልፀው ከነገው ዕለት ጀምሮም ነዋሪዎች በየቤታቸው ለፍራፍሬ የሚሆኑ ተክሎችን የመትከል ስራ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

ሀላፊዋ አክለውም ሁሉም ነዋሪ በየቤቱ ባለው ውስን ቦታ የከተማ ግብርናን የጓሮ አትክልቶችን በመጀመር ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ገልፀዋል።

Mereja media

በሀዋሳ የአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ በሚለው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል፡፡በደማቅ አሻራ ደማቅ ድል የምናስመዘግብበት፤ እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘመን ተሻጋ...
22/08/2024

በሀዋሳ የአንድ ጀንበር 600 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ በሚለው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል፡፡

በደማቅ አሻራ ደማቅ ድል የምናስመዘግብበት፤ እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ የምንጽፍበት በከተማችን ሀዋሳ የ75 ሺ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ የከፍታችን ንጋት ማብሰሪያ

አረንጓዴ አሻራ የመደመር ትውልድ ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ አሻራ፤ የነገ ትውልድ ውርስ ነው።

ይህንን ተከትሎ ነገ ነሐሴ 17/2016 ሀዋሳ በተባበረና በተናበበ ክንድ በህብር ደምቃ በአንድነት ትተክላለች።

ደማቁን የመደመር ትውልድ አሻራ በትጋት አሳርፈን ለነገዋ ኢትዮጵያ ውርስ እናኖራለን!

ነገ ከማለዳ ጀምሮ ከተለያየ የህበረተሰብ ክፍሎች የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች፣ የከተማና ክ/ከተማ አመራሮች፣ ሰራተኞች፣ የሀይማኖት አባቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በልዩ ትኩረት የሚሳተፉበት ደማቅ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ይካሄዳል።

በዚህም በሁሉም ክ/ከተሞች ደማቅ የህዝብ ተሳትፎ የሚደረግበት አሻራን በማስቀመጥ የትውልድ ውርስ የመትከል የአንድ ጀምበር መርሃግብር ለማድረግ ሁሉንም ክ/ከተሞች ባማከለ መልኩ በቂ የጉድጓድና የችግኝ ዝግጅት ተዘጋጅቷል።

ስንተባበርና በህብር ፀንተን በአንድነት ስንቆም ከዚህም በላይ እንችላለንና የነገው ሀገርዓቀፍ 600 ሚሊዮን የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃግብርን በስኬት ፈጽመን ሌላ ደማቅ ታሪክ እንጽፋለን።

Mereja media

የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ  ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው።ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ...
22/08/2024

የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው።

ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል።

የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ መጠለያ እንዳስቀመጡትና ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያሻዉ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማልኮ ገልጸው " በአሁኑ ወቅት የውሃው መጠን ከተለመደው ውጪ እየጨመረና ሰፊ ቦታ እየያዘ ከመምጣቱ የተነሳ ለኦሞራቴ ከተማ ማህበረሰብ እንደሚያሰጋ " ተናግረዋል ።

ችግሩ እየባሰ የመጣው የውሃውን አቅጣጫ የማስቀየርና የማፍሰስ ስራዎች በኢንቨስተሮች እርሻ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያስከተለ ነው በሚል በጅምር በመቆሙ መሆኑን የሚያነሱት የአካባቢዉ ነዋሪዎች በበኩላቸው ችግሩ በየአመቱ የሚፈጠር በመሆኑ ኑሯቸውን አስቸጋሪ እንዳደረገዉ ይገልጻሉ።

በመሆኑም አሁን ላይ ማህበረሰቡ ቤቱ እየተዋጠበት ከብቱ እየሞተበትና የሚቀምሰውም በመጥፋቱ ተስፋ በመቁረጥ አካባቢውን ጥሎ መሸሽ መጀመሩ ተሰምቷል።

ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ከኦሞ ወንዝ ሙላት ጋር ተያይዞ በአከባቢው በተደጋጋሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ ሲከሰት እንደነበር የገለጹት የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው አምና ከ79 ሺህ በላይ አርብቶ አደሮች በወንዙ ሙላት መጥለቅለቅ ከመኖሪያ ቀዬአቸው መፈናቀላቸውን ይናገራሉ።

እነዚህ አርብቶ አደሮች እስከ ዛሬ በጊዜያዊ ማቆያ ስፍራ እንዲቆዩ የተደረገ መሆኑን የሚገልጹት አቶ ታደለ ለእርሻ ስራ በሚል ወደ ቀድሞ ቀያቸው በተመለሱት ላይ አሁንም ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል ።

አሁን ላይ ወንዙ መደበኛ የፍሰት አቅጣጫውን በመልቀቅ የጉዳት መጠኑን አስፍቶና አርብቶ አደሩን አፈናቅሎ ለማህበራዊ ችግር እየዳረገ ሲሆን በኢፌዴሪ ውሃና ኢነሪጂ ሚኒስቴር አማካኝነት ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመረው የመከላከያ ፕሮጀክት መፍትሄ ያመጣል ቢባልም ሊጠናቀቅ አልቻለም።

በዚህ ምክኒያትም አሁን ላይ በ33 ቀበሌዎች የነበሩ መሠረተ ልማቶች ትምህርት ቤቶች ጤና ኬላዎችና መኖሪያ ቤቶች በውሃ ሊከበቡና ነዋሪው ለከፋ ችግር ይጋለጥ ዘንድ ምክኒያት ሆኗል።

mereja media

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ የሄቨን እናትን በማግኘት አጽናንተዋል::ልጇን በግፍ ተነጥቃ ባለፈው አንድ ዓመት ፍትህ ሳታገኝ ለቆየችው እህታችን የፍትህ ...
21/08/2024

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ የሄቨን እናትን በማግኘት አጽናንተዋል::

ልጇን በግፍ ተነጥቃ ባለፈው አንድ ዓመት ፍትህ ሳታገኝ ለቆየችው እህታችን የፍትህ ሂደቱን ለመከታተል ፣ ያለችበት ሁኔታ የተሻለ እንዲሆንላት እና ተጋላጭነቷን ለመቀነስ እንዲመች የከተማ አስተዳደሩ አንድ የመንግስት የመኖሪያ ቤት እንዲሁም በሙያዋ እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ እንድትሰራ መመቻቸቱን ከንቲባ አዳነች ተናግረዋል::

የህፃን ሄቨን ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ በመሆኑ ድርጊቱ ተገቢውን ፍትህ ማግኘቱ የሌሎች ህፃናት ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስተዋፅዖ ያለው ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች የዚህ አይነት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት እንዳይፈፀም የማህበረሰቡ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ እና ችግሩ የጋራ ጉዳይ በመሆኑ ሁላችንም ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባልም ብለዋል።

mereja media

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ልማት በአካባቢ ጥበቃና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው - የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ሚኒስትሮች  የኢትዮጵያ የአረንጓ...
21/08/2024

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ልማት በአካባቢ ጥበቃና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው - የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ሚኒስትሮች

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ ልማት በአከባቢ ጥበቃና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ሚኒስትሮች ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 17 በሚካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አሻራችንን እናኑር በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በእለቱ አዋቂዎች ከ20 በላይ፣ ታዳጊወች ደግሞ ከ10 በላይ ችግኞችን በመትከል ለሀገር ያለንን ፍቅር፣ ለትውልድ ያለንን ስጦታ በተገቢው ስፍራ እንግለጥ ብለዋል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አዲስ ታሪክ መስራቷን ተናግረዋል፡፡

በዚህ ዓመትም በሀገር አቀፍ ደረጃ ነሐሴ 17 ቀን ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር፤ በክልሉ አስፈላጊው ሁሉ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው በክልሉ ለአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ስኬት ሁላችንም ተዘጋጅተናል ብለዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፤ በድሬደዋ ከተማ አስተዳዳር በአንድ ጀምበር አንድ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል፡፡

በከተማዋ በአራት ክላስተሮችና በዘጠኝ ወረዳዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ነሐሴ 17 ቀን በነቂስ ወጥተው አሻራቸውን እንዲያሳርፉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ለነሐሴ 17 የአንድ ጀምበር የችግኝ የተከላ መርሃ ግብር ዜጎች በነቂስ ወጥተው አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በስኬት መቀጠሉን ገልጸዋል።

በአካባቢ ጥበቃ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በመሆኑም ነሐሴ 17 በሚከናወነው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሁሉም እንዲሳተፍ ጠይቀዋል።

በ2015 ዓ.ም በአንድ ጀምበር ከ566 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው ይታወሳል።

Mereja media

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድና ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ሀዋሳ ከተማ ገቡጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ሀዋሳ ከተማ ሲገቡ የሲዳ...
21/08/2024

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድና ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ሀዋሳ ከተማ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው ሀዋሳ ከተማ ሲገቡ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና የሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል አድገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚኖራቸው ቆይታ በሀዋሳ ታቦር ተራራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር፣ የከተማ ግብርና ስራዎች እንዲሁም በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ይመለከታሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Mereja media

ታምራት ቶላ በፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን ወርቅ አስገኘ!ታምራት 2:06:26 በሆነ ሰዓት የኦሎምፒክ ክብረወሰንን አሻሽሎ በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስ...
10/08/2024

ታምራት ቶላ በፓሪስ ኦሎምፒክ በማራቶን ወርቅ አስገኘ!

ታምራት 2:06:26 በሆነ ሰዓት የኦሎምፒክ ክብረወሰንን አሻሽሎ በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል።

የቤልጂየምና የኬንያ አትሌቶች ሁለተኛና ሦስተኛ ሲሆኑ ደሬሳ ገለታ አምስተኛ ቀነኒሳ በቀለ ደግሞ 39ኛ ሆነው አጠናቀዋል።

Merja media

በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ በጥልቴ ቀበሌ አስተዳደር  የውስጥ ለውስጥ መንገድ ከፈታ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።Merja media ነሐሴ 4/2016 ዓ.ም        ታቦር-ሀዋሳየታቦ...
10/08/2024

በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ በጥልቴ ቀበሌ አስተዳደር የውስጥ ለውስጥ መንገድ ከፈታ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።

Merja media
ነሐሴ 4/2016 ዓ.ም
ታቦር-ሀዋሳ

የታቦር ክፍለ ከተማ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማቲዎስ ማናዬ በጥልቴ ቀበሌ አስተዳደር የመንገድ ከፈታ መርሃ ግብር እየተሠራ ሲሆን የነዋሪዎችን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት እየተሰራ መሆኑንም ኃላፊው ገልጸዋል።

ሀላፊው አክለው የሚከፈቱ መንገዶች የመልካም አስተዳደር ችግር ሆነው የሠነበቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ለሥራው ስኬታማነት ከሚመለከታቸው አካላት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር እየተሠራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

የሐዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ በኑሮ ደረጃቸው ዝቅተኛ ለሆኑ አረጋዊያን ያሰራውን ቤት አስረከበ።ነሐሴ 4/2015 ዓ/ምሐዋሳበስፍራው ተገኝተው ርክክብ ያደረጉት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/...
11/08/2023

የሐዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ በኑሮ ደረጃቸው ዝቅተኛ ለሆኑ አረጋዊያን ያሰራውን ቤት አስረከበ።

ነሐሴ 4/2015 ዓ/ም
ሐዋሳ

በስፍራው ተገኝተው ርክክብ ያደረጉት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ኘ/ ጸጋዬ ቱኬ ናቸው።

ረ/ኘሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ በአስተዳደሩ ስር ለሚገኙ መምሪያዎች መሰል ተግባራትን እንዲተገብሩ በገለጹት መሰረት ዛሬ በሰላምና ጸጥታ መምሪያ ተሰርቶ የተጠናቀቀ ቤት ለርክክብ መብቃቱን ተናግረዋል።

ይህ ቤት በጥሬ ገንዘብ ብቻ ከ3 መቶ ሺህ ብር በላይ እንደፈጀ ገልጸው በከተማዋ ባለሀብቶችና ወጣቶች የተጀመሩ በጎ ተግባራት በሁሉም አካባቢ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመትም ከ2መቶ በላይ ቤቶችን ለመጠገን በዕቅድ መያዙን ነው ከንቲባ ጸጋዬ የገለጹት።

የሐዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ መኩሪያ መኒሳ በመምሪው ኮሚቴ በማወቀርና 38 ሰራተኞች 120 ሽህ ብር በማዋጣት በባህል አዳራሽ ክ/ከተማ ተለይቶ የተሰጣቸውን ቤት በሁለት ወር ውስጥ ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቅ እንደተቻለ ገልጸዋል።

ለዚህ ተግባር በርካታ ሰዎች በአይነትና በቁሳቁስ ድጋፍና ትብብር ማድጋቸውን አቶ መኩሪያ በማመስገን ጭምር ገልጸዋል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ፍሬህይወት ወ/ጻዲቅ በክረምት ከታቀዱ 17 ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የአረጋዊያን ቤት ጥገና በተለያዩ ክ/ከተማ ከ20 ቤት በላይ ለመጠገን ታቅዷል ብለዋል።

ወ/ሮ ፍሬህይወት አልቀው ያስረከብናቸው እየተጠናቀቁና በመሰራት ላይ ያሉ ቤቶች መኖራቸውን ገልጸዋል።

ቅን ልቦችን ፈጣሪ ይባርክ ያሉት ወ/ሮ ፍሬህይወት እነዚህ አረጋዊያን ሲደሰቱ ከማየት በላይ ትልቅ ደስታ የለም ብለዋል።

የቤት ርክክብ የተደረገላቸው አረጋዊያን አቶ ክብረት አሻግሬ እና ወ/ሮ አስናቀች ሀይሉ የ6 ልጆች ወላጅ ሲሆኑ ከዚህ ቀደም ባሉ ዓመታት በሚያፈስ፣ጎርፍ በሚገባበትና በፈራረሰ ቤት ውስጥ በችግር እየኖሩ እንደነበረ ገልጸው ይህንን ቤት ሰርተው ለሰጡን ሁሉ ፈጣሪ ይባርካቸው ሲሉ መርቀዋል አመስግነዋልም።

የመምው ም/ሀላፊና የወጣቶች ዘርፍ ሀላፊ አቶ አደራ ሀርቃ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 130 ሺህ ወጣቶች ተሳትፈው ለ270 ማህበረሰብ በመድረስ 110 ሚሊየን የመንግስት ወጪን የማስቀረት እቅድ መያዙን ገልጸዋል።

ከዚህም አንዱ በሆነው ቤት ጥገና ተግባር ዛሬ በአዲስ መልክ በመገንባት ርክክብ መደረጉን ገልጸው ሌሎችም ይህንን ተግባር እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።

Mereja media

ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በባሌና በምስራቅ ባሌ ዞኖች የስንዴ ልማትን እየጎበኙ ነው ታኅሣሥ 20፣ 2015  የግብርና ሚኒስትሩ ኡመር ሁሴን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊ...
29/12/2022

ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በባሌና በምስራቅ ባሌ ዞኖች የስንዴ ልማትን እየጎበኙ ነው

ታኅሣሥ 20፣ 2015 የግብርና ሚኒስትሩ ኡመር ሁሴን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በባሌና በምስራቅ ባሌ ዞኖች በክላስተር የለማ የስንዴ ልማትን እየጎበኙ ነው።

ሚኒስትሩ የልማት እንቅስቃሴን ከጎበኙ በኋላ በስራ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና ሊሰሩ በሚገቡ ተግባራት ላይ ከአርሶ አደሮች፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰማሩ ባለሀብቶች ጋር እንደሚመክሩ ተጠቅሷል፡፡

በምስራቅ ባሌ ብቻ በመኸሩ ወቅት ከ144 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Mereja media

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዳሴ ግድብ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገለጹነሐሴ 6፣ 2014  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል...
12/08/2022

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የህዳሴ ግድብ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገለጹ

ነሐሴ 6፣ 2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ሦስተኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠናቀቅን ከስፍራው ባበሰሩበት ንግግራቸው÷ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ እንዲሁም ለአፍሪካ እና ለዓለም የተሰጠ የተፈጥሮ ፀጋ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የአፍሪካ አገራት የኢኮኖሚክ ትስስርን ካፀደቁ ዓመታት ተቆጥሯል ያሉት ጠቅላይ ሚነስትሩ የኢኮኖሚክ ትስስሩ አንዱ መንገድ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለጎረቤት አገራት መሸጥ ነው ብለዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይሉ ሙሉ ለሙሉ ሲመነጭ ከጎረቤት አገራት ተሻግሮ ሊጠቅም የሚችል እንደሆነም ጠቅላይሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
የህዳሴ ግድቡ ሲጠናቀቅ በጋራ የመልማት እና የማደግ እድልንም በሰፊው እንደሚሰጥ ገልፀዋል።

አያይዘውም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያረፈበት አካባቢ ተራራማና አረንጓዴ መሆኑን ገልጸው፥ይህም ለቱሪዝምና ለተለያዩ የመዝናኛ አማራጮች እንዲሁም ለዓሣ እርባታ እንደሚውል አመላክተዋል፡፡

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የዓለም ሕዝብ መጥቶ ለመዝናናት የሚያስችለው ትልቅ ስጦታ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የዓለም ሕዝቦች አስፈላጊ ነው ብለው በሚያምኑበት በማንኛውም ጊዜ በዚህ ሥፍራ መጥተው ሊዝናኑ ፣ ሊያዩ፣ ጊዜአቸውን በደስታ ሊያሳልፉ የሚያስችል ከፍተኛ ብቃት እንዳለውም ነው ያስረዱት፡፡

በግድቡ ምክንያት 70 ገደማ ደሴቶች እንደሚፈጠሩ ገልጸው፥ከ40 በላይ ደሴቶች እያንዳንዳቸው ከ10 ሔክታር በላይ ቦታ እንደሚይዙን እና አንዳንዶቹ ከ800 እስከ ከ2 ሺህ ሔክታር በላይ እንደሚሸፍኑም ጠቀመዋል።

ዝቅተኛው ደሴት 5 ሔክታር የሚይዝ ነው ብለዋል፡፡

ደሴቶቹ ከፍተኛ የመዝናኛ ሥፍራና በውኃ ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎችን ሊያስተናግዱ እንደሚችሉና ከፍተኛ የሆነ የዓሣ ምርት ማምረት እንደሚያስችሉም ነው የጠቀሱት።

Mereja media

14/07/2022
አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ  ሐምሌ 7፣ 2014  በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቀድሞው ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ...
14/07/2022

አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሐምሌ 7፣ 2014 በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቀድሞው ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡

አቶ ምትኩ ካሳ እና ኢያሱ ምትኩ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

ፖሊሰ በተጠርጣሪዎቹ ላይ እስካሁን ያሰባሰባቸውን መረጃዎች እና ማስረጃዎች ለፍርድ ቤት አቅርቧል፡፡

የ10 ምስክሮችን ቃል ለመቀበል እንዲሁም በፌደራል እና በክልሎች በሚገኙ የኮሚሽኑ ቅርንጫፎች ያሉ ሰነዶች ኦዲት ለማድረግ እንዲሁም በብርበራ የተገኙ ሰነዶች እና ምንጩ ያልታወቀ የውጭ ሀገር ገንዘብን ለማጣራት እና ምርመራ ለማድረግ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡

ተጠርጣሪዎች በጠበቆቻቸው አማካኝነት በጉዳዩ ላይ የቀድሞ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና ፖሊስ የምርመራ ጊዜ ከአንድ ዓመት በፊት ያለቀ በመሆኑ ለፖሊስ እንዳይሰጥ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

ግራ ቀኙን የተመለከተው ችሎቱ ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜን የፈቀደ ሲሆን፥ ተጠርጣሪዎች ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄን ውድቅ አድርጓል።

Mereja media

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ጉዳይ ላይ ውሳኔ አሳለፈ ሐምሌ 5 ፣ 2014  የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከሰሞኑ አነጋጋሪ ሆኖ በሰነበተው የአዲስ አበባ ዩ...
12/07/2022

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ጉዳይ ላይ ውሳኔ አሳለፈ

ሐምሌ 5 ፣ 2014 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከሰሞኑ አነጋጋሪ ሆኖ በሰነበተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ5ኛ ዓመት ተማሪ ከሆነው ቢኒያም ኢሳያስ ጋር በተያያዘ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ዩኒቨርሲቲው ተማሪ ኢሳያስ የአራተኛ ዓመት ተማሪ እያለ የግራ እጁ ላይ በተፈጥሮ የአካል ጉዳት ያለበት መሆኑ በመምህራን ከተለየ በኋላ ይህ ጉዳት በህክምና ትምህርቱ ላይ ያለው ተፅዕኖ እንዲታይ ወደ ዲን ጽህፈት ቤት መርቶት እንደነበር አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጁ እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ላለፉት 8 ወራት ጉዳዩን ሲመለከቱት መቆየታቸውም ተገልጿል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው እና የጤና ሳይንስ ኮሌጁ የተማሪ ቢኒያምን ጉዳይ እንደ ተማሪ፣ እንደ አካል ጉዳተኛ እና የህሙማንን ጉዳይ በየዘርፉ ለይተው ምክክር ማድረጋቸውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አንዱአለም ደነቀ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ከዩኒቨርሲቲው ውጪ ያሉ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላትን በማሳተፍ ውይይት መደረጉን ጠቅሰው፥ መሰረታዊ በሆኑ የህክምና ተቋማት ላይ ቴክኒካል የሆኑ አሰራሮችን መመልከት መቻሉንም አስረድተዋል።

ባገኘው አሰራርም አንድ የህክምና ባለሙያ በመሠረታዊነት መስጠት ያለበትን የህክምና እርዳታ የሚያሟላውን መስፈርት በተመለከተም፥ ተማሪ ቢኒያም በዩኒቨርሲቲው ከሚሰጡ ስምንት የቅድመ ምረቃ ትምህርቶች አምስቱን ለመማር እና ለወደፊት ሙያውን ለመተግበር እንደሚቸገር ከስምምነት ላይ መደረሱን አስረድተዋል።

ነገር ግን በሌሎች የትምህርት አይነቶች ትምህርቱን መቀጠል እንደሚችል አብራርተዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በተሰጠ ውሳኔም ዩኒቨርሲቲው ችግሩን በወቅቱ ለይቶ አማራጮችን ባለመውሰዱ እና በተማሪው ላይ ለደረሰው የሞራል ጉዳት ሃላፊነቱንይወስዳልም ነው ያሉት።

በቀጣይ ተማሪ ቢኒያም ትምህርቱን በሚከታተልበት ሂደት ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

mereja media

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰሞኑን በወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር መከሰቱን አስታወቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ሐምሌ 01 ቀን 2014 በወጣው የ20/80 እና ...
12/07/2022

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰሞኑን በወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር መከሰቱን አስታወቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 01 ቀን 2014 በወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ የዳታ ማጭበርበር ድርጊት በመከሰቱ ሁኔታውን እያጣራ እንደሚገኝ እና በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር እያዋለ መሆኑን አስታወቀ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው÷ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓቱ በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ሲጀመር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነት ተገኝቶበታል፡፡

በእስካሁኑ የማጠራት ስራም ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል ነው ያለው፡፡

በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑም በመግለጫው ተመላክቷል፡፡

ከዚህ በመነሳትም “የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል” ብሏል፡፡

ሒደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማዋ ነዋሪ እንደሚያሳውቅ የገለጸው አስተዳደሩ÷ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንዲጠባበቁም ጠይቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ሀምሌ 01/ 2014 የወጣውን የ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ይመለከታል

በከተማችን አዲስ አበባ ከሚስተዋሉ ችግሮች መካከል አንዱ የቤት አቅርቦት እጥረት ሲሆን ይህንኑ ደረጃ በደረጃ ለማቃለል አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮችን ነድፎ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የዚህ ሂደት አካል የሆነው የነባሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉበትን ወስብስብ ችግር ለይቶ በመፍታት ተመዝጋቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ እና የቤት እጥረት ጫና ለመቀነስ የተደረገው ሰፊ ጥረት ተጠቃሽ ነው፡፡

በዚህ ሂደት በግንባታ ላይ የነበሩ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል 25,491 ያህሉ በቅርቡ ለባለ እድለኞች የዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት መካሄዱ ይታወቃል፡፡

ይህ የቤት ማሰስተላለፍ ስራ እንደ ከዚህ በፊቱ በቆጣቢወች መካከል አድሎና ብልሹ አሰራር እንዳይኖር ለማድረግ ግልፅነት በሚያሰፍን አግባብ ለማስተላለፍ ሲባል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ በመስራት ሂደቱን ግልጽና አሳታፊ ለማድረግ የተደረገው ተነሳሽነትና ጥረት እንዲሁም የባልሙያዎችን ሙያዊ ነፃነት አክብረን አስፈላጊውን ሂደት ተከትለን ተዓማኒነቱን እንዲያረጋግጡልን አድርገን ነበር፡፡

በዚህ ሂደት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ አዲስ ሶፍትዌር እንዲበለፅግ እና ስለሶፍትዌሩ ታአማኒነት የኢኖቬንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር እንዲያረጋግጥልንም ተደርጓል፡፡

በቀጣይም ከሁለት ጊዜ በላይ ታዛቢወች እና ባለሙያወች ፊት ቀርቦ እንዲያረጋግጡልን ተደርጎ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡

ይህ ሁሉ ሂደት ከእለት ጉርሱ የቆጠበዉን እና በከፍተኛ ጉጉት የሚጠባበቀውን ሕዝብ በፍትሃዊነት ተደራሽ ለማድረግ ቀና ሃሳብ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል፡፡

ይሁን እንጂ ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል፡፡

በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡

ከዚህ በመነሳትም የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር በቁጥጥር ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ስለሆነም ሂደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቀን ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማችን ነዋሪ የምናሳውቅ መሆኑን ስንገለጽ ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው ስህተት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ይጠይቃል!

mereja media

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲና ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ5 ሺህ 800 በላይ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት አበረከቱ ሰኔ 17፣ 2014  ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ...
24/06/2022

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲና ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ5 ሺህ 800 በላይ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት አበረከቱ

ሰኔ 17፣ 2014 ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 5 ሺህ 865 መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ዛሬ አበርክተዋል፡፡

''ሚሊየን መጻሕፍት ለሚሊኒየሙ ትውልድ' በሚል መሪ ቃል ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በሚከናወነው የመጻሕፍት ማሰባሰብ ንቅናቄ የተለያዩ ተቋማትና ዜጎች ተሳትፎ እያደረጉ ነው።

በዚህ መሰረትም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያሰባሰቧቸውን መጻሕፍት በዛባ ዕለት አስረክበዋል፡፡

መጻሕፍቱን የዩኒቨርሲቲውና የኮሌጁ አመራሮች ለአዲስ አበባ የባህል ኪነጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ የፅህፈት ቤት ኃላፊ ፈይሳ ፈለቀ ማስረከባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የሐረማያ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል የሱፍ÷ 4 ሺህ 334 የተለያዩ የምርምር፣ የፍልስፍና እንዲሁም የታሪክ ይዘት ያላቸው መጻሕፍትን ለአብርሆት ማስረከባቸውን ተናግረዋል ።

በተመሳሳይ የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ግሩም ግርማ ÷ኮሌጁ ከተማሪዎች፣ ከሰራተኞች እና ከተቋሙ ወዳጆች ያሰባሰባቸውን 1 ሺህ 531 መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ማበርከቱን ገልጸዋል፡፡

mereja media

Address


Telephone

+251918997611

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mereja media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share