የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Shone
  • የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ይህ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የማህበራዊ ሚዲያ ድህረ ገጽ ነው።

ቀን 09/11/2016 ዓ.ምየሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት  የ2016 ዓ.ም አፈፃፀምና ወቅታዊ የወባ ወረርሽኝ ሥራዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፤ሾኔ፤ ሐምሌ 0...
16/07/2024

ቀን 09/11/2016 ዓ.ም
የሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም አፈፃፀምና ወቅታዊ የወባ ወረርሽኝ ሥራዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፤

ሾኔ፤ ሐምሌ 09/2016 ዓ.ም ( የሾኔ የከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም አፈፃፀምና ወቅታዊ የወባ ወረርሽኝ ሥራዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩም የተዘጋጀው ሰነድ በጤና ልማት ዕቅድ ተወካይ በአቶ አሸናፍ ዮሴፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

መድረኩን የመሩት የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት እና የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ ሲሆኑ ከንቲባው ቤቱ በስፋት እንዲወያይ ትኩረት ከሰጡአቸው ጉዳዮች በተለይ በጉድለት የተገመገሙት ነጥቦች ዙሪያ ልዩ ትኩረት በመስጠት ሃሳብ መነሳት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በውይይቱም ላይ የከተማ አስተባባሪ፣ የጤና ጽ/ቤት ማኔጅመንት፣ የሆስፒታል ማኔጅመንት፣ የቀበሌ ደጋፊ አመራሮች፣ የቀበሌ የፊት አመራሮች፣ የማዞሪያ ጤና ጣቢያ ማኔጅሜንት እና የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የተገኙ ስሆን በሰነዱ ላይ አስተያየት ከሰጡ በኋላ በጉድለት በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ በቀጣይ ጊዜ ኃላፊነት ወስደው የየድርሻቸውን ለመወጣት ቃል ገብተዋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ዳንኤል አየለ እንደተናገሩት በጤናው ዘርፍ በርካታ ተግባራት የተከናወነና ውጤትም እያስመዘገብን የመጣን እንደሆነ ሁሉም ሰው ሊገነዘብ ይገባል ካሉ በኃላ በጉድለት ተለይቶ የቀረቡ ተግባራት፣ ወደ ኋላ የቀሩ ተቋማትና እንዲሁም ቀበሌያት የተለየ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል በማለት የማጠቃለያ ሃሳብ ሰጥተዋል።

አቶ ኤልያስ ዳዊት በተለይ ወቅቱ የወባ ወረረሽኝ ያለበት ወቅት በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት ልሰሩ እንደሚገባ በማስገንዘብ በየቀበሌው ያለው ፈጣን ምላሽ ሰጪ ኮሚቴ ከመቼውም ጊዜ በላዬ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበው ከስርዓተ ምግብ ፕሮግራም ጋር ተያይዞ የአልሚ ምግብ ከታለመው ውጪ ማዋል ይቅርታ እነደማያሰጥ አሳስበው እንደተቋም ግን በታዩት ክፍተቶች ዙሪያ ኃላፊነት ወስደዉ ለመሥራትና ድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር የማድረግ ሥራ ከመቸውም ጊዜ በላይ አጠናክረን እንሰራለን ብለዋል።

አቶ አበራ በዶሬ የማጠቃለያ ሃሳብ ስሰጡና ቀጣይ አቅጣጫ ባስቀመጡበት ወቅት የማዐጤመ አገልግሎት አሰጣጥ እና የወባ ወረረሽኝ ዙሪያ ላይ ትኩረት ሰጥተን ለህዝባችን አገልግሎት መስጠት ባለብን ልክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሁላችንም ቅንጅት ፈጥረን መስራት አለብን በማለት አቅጣጫ ካስቀመጡ በኋላ የውይይት መድረኩ ተጠናቋል።

ሐምሌ 09/2016 ዓ.ም
ሾኔ

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የ11 ወር አፈፃፀም ሪፖርት ገመገመ ::ሰኔ 18/2016 ዓም ::በማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ከሾኔ የመጀመሪያጠደረ...
25/06/2024

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የ11 ወር አፈፃፀም ሪፖርት ገመገመ ::

ሰኔ 18/2016 ዓም ::
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ከሾኔ የመጀመሪያጠደረጃቨሆስፒታል፣ ከማዞሪያ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ እንዲሁም የጽ/ቤቱ የማናጅመንት አካላት በተገኙበት በጤና ጽ/ቤቱ ኃላፊ መሪነት የ11 ወር አፈፃፀም ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን በግምገማውም ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገ በኃላ በውስንነት በታዩ ነጥቦች:-
- የረዥም ጊዜ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ተከታትሎ በየበጀት አመቱ ሪፖርት ከማድረግ አንፃር ውስንነት መኖር
- የክትባት አገልግሎት የመረጃ ጥራት ችግር
- የቲቢ ታካሚዎች የመረጃ ጥራት ችግር
- ከ2 ዓመት በታች ሕፃናት የእድገት ክትትልና ማጎልበት አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን
- በዘመቻ የተሰሩ ስራዎች በDHIS -2 system እየገባ አለመሆን ለምሳሌ ቫይታሚን ኤ ፣ ፀረ የአንጀት ጥገኛ ትላትል መድኃኒት የወሰዱ ሕፃናትን ሪፖርት አለማድረግ እንዲሁም የሚዝል 1 እና ሚዝል 2 ሪፖርት ያለማድረግ እና ሌሎችም በርካታ ተግባራት በአመቱ ማጠቃለያ ሪፖርት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሰራ አቅጣጫ በመያዝ እና የዓመቱን ማጠቃለያ በ25/10/2016 ዓ/ም እንደሚገመገም ቀጠሮ በመያዝ የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

ሾኔ ከተማ አስ/ር ጤና ጽ/ቤት

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ *********************የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር...
07/06/2024

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
*********************

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ ሁሉን ዓቀፍ የጤና አገልግሎትን ለማረጋገጥ እና በቀጣይም የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤን ለማጠናከር ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር እንደምትሰራ የጤና ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ በበኩላቸው ድርጅቱ በኢትዮጵያ የጤና ዘርፉ በሰው ኃይል እና በፋይናንሲንግ እንዲጠናከር፣ የክትባት ተደራሽነት እንዲሰፋ እንዲሁም የወባ እና የኮሌራ በሽታ ወረርሽኞችን ለመቆጣጠር ድጋፉን እንደሚያጠናክር አስታውቀዋል፡፡

ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ኢትዮጵያ የዓለም የጤና ደንብ ማሻሻያዎች ውስጥ ላሳየችው የነቃ ተሳትፎ አድናቆታቸውን መግለጻቸውንም ከጤና ሚኒስቴር የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ምንጭ የኢትዮጲያ ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬት

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የማዞሪያ ቀበሌን በጤና ሞዴል አድሮጎ ለማስመቅ የንቅናቄ መድረክ ፈጠረግንቦት 21/09/2016 ዓ/ምበውይቱ ላይ የተሳተፋት የሾኔ ጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች ...
29/05/2024

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የማዞሪያ ቀበሌን በጤና ሞዴል አድሮጎ ለማስመቅ የንቅናቄ መድረክ ፈጠረ

ግንቦት 21/09/2016 ዓ/ም
በውይቱ ላይ የተሳተፋት የሾኔ ጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች የማዞሪያ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ባለሙያዎች የቀበሌ የፊት አመራሮች በተገኙበት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት አጀንዳ ሲያሲዙ በቀጣይ 1 ወር የማዞሪያ ቀበሌን በጤና ሞዴል ማድረግ መሆኑን በመግለጽ በመግቢያ ንግግራቸው ቀበሌን በጤና ሞዴል ለማድረግ ሞዴል ቤተሰብ መፍጠር፣ ሞዴል ት/ቤት መፍጠር፣ ቀበሌውን ቤት ውስጥ ከመውለድ ነፃ ማድረግና በቤተሰብ ደረጃ የተሻሻለ መፀዳጃ ቤት እንዲኖር ከማድረግ ጋር ተያይዞ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚገባና ይህንን ባለማድረግ ብቻ ማህበረሰባችን ለተላላፊ በሽታ ከመዳረጉም በላይ ለህመምና ሞት እየተዳረገ መሆኑን በመግለጽ ለዚህም ቀበሌን በጤና ሞዴል ማድረግ ዋናው መብትሄ መሆኑን በመግለጽ ይህም እንዲሳካ ሁሉም ተልዕኮ የተሰጠው ባለድርሻ አካል ርብርብ በማድረግ የበኩሉን እንዲወጣ በማሳሰብ የዕለቱን መድረክ የከፈቱ ሲሆን የበሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዋና ስራ ሄደት አስተባባሪ ወሮ አዱኛ ለገሰ የግንዛቤ ማስጨበጫ በመስት እንዲሁም ከቀበሌ ስራ አስኪያጅ ጀምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካል ሊያሳካ እንደሚችል በአስተያየታቸው በማረጋገጥ የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

ምንጭ የሾኔ ከተማ አስተ/ር ጤና ጽ/ቤ

በማዕከላዊ ኢትዮዺያ  የሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ በ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር አፈፃፀም ሪፓርት መገምገሙን ገለፀ።ሾኔ፣ግንቦ...
14/05/2024

በማዕከላዊ ኢትዮዺያ የሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ በ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር አፈፃፀም ሪፓርት መገምገሙን ገለፀ።

ሾኔ፣ግንቦት 06/09/2016 ዓ/ም የሾኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የሀድያ ዞን የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ላማጆ ፣ አቶ ታከለ ኦልበሞ የሀድያ ዞን ጤና ምሪያ ኃላፊ፣ አቶ አበራ በዶሬ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና ሙሉ የቦርድ አባላት በተገኙበት በሆስፒታሉ ተዘዋውረው ምልከታ ካደረጉ በኃላ የቦርዱ ሰብሳቢ የሀድያ ዞን የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ላማጆ አጀንዳ በማስያዝ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፓርት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር በዶ/ር መሀመድ አህመድ ከቀረበ በኃላ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

የስራ አመራር ቦርዱ በቀረበው አፈፃፀም እና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደረገ ሲሆን በውይቱም በስፋት ከተነሱ ነጥቦች አንዱ የሆስፒታል የውሀ ችግር ከሁለት ዓመት በላይ ሳይፈታ የቆየ ችግር ሲሆን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበራ በዶሬ በቀጣይ ሁለት ሳምንት ሙሉ ሀላፊነት በመውሰድ ለማሰራት ቃል ገብተዋል በሌላ ጎኑ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሩን ከማሻል ረገድ የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎችን ችግር ከመቅረፍ ረገድ በፍጥነት ሁሉንም ባከድርሻ አካላት በማሳተፍ ሀብት ማሰባሰብ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚገባ የቦርዱ ሰብሳቢ አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት
ሾኔ

የስቅለትና ትንሳኤን በዓል በጤና!በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤ/ጽቤት ሃላፊ  የስቅለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፋ...
04/05/2024

የስቅለትና ትንሳኤን በዓል በጤና!

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በሀድያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤ/ጽቤት ሃላፊ የስቅለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፋ።

በመልዕክታቸውም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ስቅለቱና ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ በማለት!!

በዓሉ የሰላም፣የጤና ከፈጣሪ ዘንድ ምህረትን አግኝተን ድህነትን የምናገኝበት ትንሳኤ እንዲሆን ተመኝተዋል።

አያይዘውም ይህ በዓል ከፍተኛ የሆነ የንግድ ስርዓት የሚከናወንበት በዓል በመሆኑ ከንግድ ስርዓቱ ጋር ተያይዞ ያሉ ምግብን ለጤና ጠንቅ ከሆኑ ባዕድ ነገሮች በመቀላቀል በመሸጥ ለመክበር የሚፈልጉ ነጋዴዎች ስለሚኖሩ ማህበረሰቡ የቅቤ፣በርበሬ፣ዘይትና መሰል ለምግብነት የሚውሉ ከበዓሉ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ምርቶች በሚሸምትበት ወቅት አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ እንዲሸምት እንዲሁም አጠራጣሪ ሁኔታዎች በሚኖሩበት ወቅት በአካባቢው ለሚገኙ የጸጥታ አካላትና ለጤና ባለሙያዎች ጥቆማ እንድትሰጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ሲሉ ገልፀዋል።

ሃላፊው አክለውም በፆም ወቅት ከቅባት ነክ ምግቦች ታቅበን የምንቆይበት ወቅት በመሆኑ ፍስኩን መሰረት በማድረግ ከምንመገባቸው ምግቦች ጋር ተያይዞ የሚከሰት ማንኛውም የጤና እክል በሚኖርበት ወቅት ጤና ተቋም በመሄድ ተገቢውን ህክምና በማድረግ የሚታዘዙልንን መድሃኒቶች በአግባቡ ወስደን መጨረስ ይጠበቅብናል ሲሉም የገለጹ ሲሆን ያለ ሃኪም ትዕዛዝ የሚወሰዱ ማናቸውም መድሃኒቶች የጤና ጉዳት የሚኖራቸው መሆኑን አውቆ ህብረተሰቡ ያለ ሃኪም ትዕዛዝ ለህክምና የሚውሉ መድሃኒቶችን እንዳይጠቀም አሳስበዋል።

በበዓል ወቅት ሌላው የሚስተዋለው አንዱ ችግር ያልተገባ የአልኮል አጠቃቀም ነው ያሉት ሃላፊው አልኮል እድሜው 21 ዓመት ላልሞላው ሰው መሸጥም ሆነ እንዲሸጥ ማድረግ በህግ የተከለከለ ነው ሲሉም ገልፀዋል።

በመሆኑም ህብረተሰቡ ይህን በዓል በሚያከብርበት ወቅት አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ እራሱንና ቤተሰቡን መከላከል ከሚችለው የጤና ጉዳት እንዲጠብቅም አሳስበዋል።

የትንሳኤው ብርሃንና የጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ለሁላችን ይሁን በድጋሚ መልካም የስቅለትና የትንሳኤ በዓል እንዲሆን እንመኛለን።

የሾኔ ከተማ አስተ/ር ጤና ጽ/ቤት

"እመረመራለሁ ጤናዬን እጠብቃለሁ" - በሚል መሪ ሀሳብ በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ ከጤና ጽ/ቤትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የማህፀን ...
22/04/2024

"እመረመራለሁ ጤናዬን እጠብቃለሁ" - በሚል መሪ ሀሳብ በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ ከጤና ጽ/ቤትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በሽታን አስመልክቶ ለሴቶች ሊግ አባላትና መላ ሴቶች ግንዛቤ መፍጠሪያ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ፤

ሾኔ፡ ሚያዚያ 14/2016 ዓ.ም "እመረመራለሁ ጤናዬን እጠብቃለሁ" - በሚል መሪ ሀሳብ በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ሊግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የማህፀን በር ካንሰር በሽታን አስመልክቶ ለሴቶች ሊግ አባላትና መላ ሴቶች ግንዛቤ መፍጠሪያ ንቅናቄ መድረክ በሾኔ ከተማ አካሄዷል።

ሴቶች ቤት ከማስተዳደር ጀምሮ ለብልጽግና ጉዞ እና ለጠንካራ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ሚናቸው የላቀ በመሆኑ የሴቶች ጤናማ ሆኖ መገኘት ፋይዳው ፈርጀ ብዙ ስለሆነ የሴቶችን ጤና የሚጎዱ በሽታዎችን የመከላከል እና የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ ምንነትና ምልክቶችን በተመለከተ ግንዛቤ ተሰጥቷል።

ከመድረኩም ጎን ለጎን በጤናው ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች የመስክ ምልከታና ልምድ ልውውጥ በሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በማዋለጃ ክፍል፣በእናቶች ማቆያ የተከናወነ ሲሆን፤ የመድረኩ ተሳታፊዎች ለሆስፒታሉ የእናቶች ማቆያ የአልባሳት ድጋፍ ለግሰዋል።

ይህ ተመሳሳይ መድረክ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች ድረስ የሚወርድ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።

በውይይቱም በከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወርቁ ዮሐንስ፣ አቶ ተስፋሁን ማቲዎስ የሾኔ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ የፓለቲካ እና ሪዕዮተ- ዓለም ዘርፍ ኃላፊ ፣ክብርት ወ/ሮ ክብርነሽ አበበ የከተማ አስ/ር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ፣ የከተማ አስተዳደሩ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ ዳዊት፣ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ደሳለች ሄሊሶ እና ወ/ሮ ወርቅነሽ ሴታ የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይና ሴቶች ሊግ ጽ/ቤት ም/ኃላፊ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የቲቢ በሽታ ቅድመ ምርመራ /Catch up/ ዘመቻ ላይ ለሚሳተፉ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።****                 ...
15/04/2024

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የቲቢ በሽታ ቅድመ ምርመራ /Catch up/ ዘመቻ ላይ ለሚሳተፉ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።

****
ሚያዚያ 05- 2016 ዓ/ም

በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ አቶ አቶ ኤልያስ ዳዊት የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ሥልጠናውን ሲያስጀምሩ ያስተላለፋት መልዕክት እንደ ዓለም ጤና ጥበቃ መረጃ በተለምዶ የሳንባ በሽታ የምንለው (ትበርክሎሲስ/ቲቢ ) በሚልየን ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት ምክንያት ነው።�በ ዓለም ላይ ሞትን ከሚያስከትሉ ተላላፊ በሽታዎች ቁጥር 1 ገዳይ በሽታ ነው ።�ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ከፍተኛ የቲቢ ታማሚ እና በቲቢ ምክንያት ሰዎች ከሚሞቱባቸው 30 አገራት አንዷ ነች እንዲሁም እንደከተማ አስተዳደርም በሽታው በስፋት መኖሩን አውስተው ይህን የቲቢ በሽታ ቅድመ ምርመራ /Catch up/ ዘመቻ እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ�የበሽታው ዋና ምልክቶች ምንድናቸው?�የቲቢ በሽታ በምን አይነት ምርመራ ይረጋገጣል?�ሕክምናው ምን ይመስላል ?�ሕክምናው ለምን ያህል ጊዜ ይቆያል?�ቤት ውስጥ የታመመ ሰው ካለ ምን አይነት ጥንቃቄ ነው ማድረግ ያለበት ? የሚለውን ጥያቄ ማህበረሰባችን እንዲያውቅ ከማድረግ አንፃር በደንብ ግንዛቤ መፍጠር እንዳለባቸው በመግለጽ በስልጠናው መሰረት መመርመር ያለባቸውን የማህብረተሰብ ክፍሎች በሚገባ በመመርመር፣ ህክምና እንዲጀምሩ በማድረግ እንዲሁም ከ15 ዓመት በታች ኮንታክት ኬዞችን IPT በማስጀመር� ይህንን ለተከታታይ 10 ቀናት በዘመቻ መልክ የሚሰራውን የቲቢ በሽታ ቅድመ ምርመራ /Catch up/ ዘመቻ ስኬታማ ማድረግ ከእያንዳንዱ ባለሙያ የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን በማስታወቅ የዕለቱን የስልጠና መድረክ የከፈቱ ሲሆን ስልጠናውንም የጽ/ቤቱ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ስራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ አዱኛ ለገሰ ስልጠናውን በመስጠት ሰፊ ውይይት በማድረግ የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም ቀበሌያት እየተሰጠ ያለው የዚትሮማክስ መድሀኒት ዕድልና የቤት ለቤት የኩፍኝ ወረርሽኝ አሳሰ ቅኝት እንድሁም በተመረጡ የክትባት መስጫ ማዕከላት እየተሰጠ ያለው ክትባ...
27/01/2024

በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም ቀበሌያት እየተሰጠ ያለው የዚትሮማክስ መድሀኒት ዕድልና የቤት ለቤት የኩፍኝ ወረርሽኝ አሳሰ ቅኝት እንድሁም በተመረጡ የክትባት መስጫ ማዕከላት እየተሰጠ ያለው ክትባት በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ገለፀ።

ጥር 17/5/2016 ዓ.ም
በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር የዚትሮመክስ ዘመቻና የኩፍኝ ወረርሽኝ መከላከያ ተግባራት እንድሁም የክትባት አሰጣጥ በተቀናጀ መንገድ እየተሰራ እንደሆነ የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ገለፀ።

የዘመቻውን አጠቃላይ ሂደትን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በኃይሉ ዳዊት የዘመቻው አስተባባሪዎች በተለየዩ ቀጠናዎች በማዘዋወር ተመልክቷል።
ሾኔ

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር በሚቀጥሉት ቀናት ለሚካሄደው የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሀኒት ዕደላ ለማስጀመር ለጤና ባለሙያዎች፤ጤና ኤክስቴንሽኖችና ለዘመቻ አስተባባሪዎች ስልጠና እየተ...
22/01/2024

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር በሚቀጥሉት ቀናት ለሚካሄደው የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሀኒት ዕደላ ለማስጀመር ለጤና ባለሙያዎች፤ጤና ኤክስቴንሽኖችና ለዘመቻ አስተባባሪዎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አስተወቀ።

ጥር 13/2016 ዓ.ም
በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የትራኮማ በሽታ መከላከያ መድሀኒት ዕደላ ለማካሄድ የባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አስታወቀ።

21/01/2024
በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ኢስትሪንግ ኮሚቴ በወቅታዊ የኩፍኝ ወረርሽኝና ሌሎች በወረርሽኝ መልክ ልከሰት የሚችሉ በሽታዎችን ቀድሞ ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር የተከናወኑ ተግባራት...
19/01/2024

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ኢስትሪንግ ኮሚቴ በወቅታዊ የኩፍኝ ወረርሽኝና ሌሎች በወረርሽኝ መልክ ልከሰት የሚችሉ በሽታዎችን ቀድሞ ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር የተከናወኑ ተግባራትን በጥልቀት በመገምገም በቀጣይ መከናወን በልባቸው ጉዳዮች አቅጣጫ ማስቀመጡን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት አስታወቀ።

ጥር 10/2016 ዓ.ም

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ኢስትሪንግ ኮሚቴ በወቅታዊ የኩፍኝ ወረርሽኝና ሌሎች በወረርሽኝ መልክ ልካሰት የሚችሉ በሽታዎችን ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር የተከናወኑ ተግባራትን በጥልቀት በመገምገም ቀጣይ መከናውን በልባቸው ጉዳዮች ተወያይቶ አቅጣጫ ማስቀመጡን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ገለፀ።

የግምገማ መድረኩን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ባንጡራ የመሩት ስሆን በመድረኩም በላፉት 60 ቀናት የኩፍኝና ሌሎች በወረርሽኝ መልክ ልከሰት የሚችለውን እንድሁም በስነምግብ እጥረት ብሎም የወባ በሽታ በማህበረሰቡ ጤና ላይ ልያሰድረው የሚችለውን ተፅዕኖ ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር የተከናወኑ ተግባራት በሾ/ከ/አስ/ር ጤና ጽ/ቤት የበሽታ መከላከል ደይሬክቶሬት ቡዱን መሪና የPHEM ተወካይ በሆኑት ወ/ሮ አዱኛ ለገሠ አማካኝነት በዝርዝር ቀርበው ወይይት ተደርጎአል።

ከሰነዱ መነሻ የከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ባንጡራ የኩፍኝ ወረርሽኝና ሌሎች በወረርሽኝ መልክ ልከሰት የሚችለውን በሽታ በተቋም ደረጃ ታቅዳ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች በመሆኑ በቀጣይነት የተጠናከረና የተቀናጀ ተግባር መከናወን እንዳለበት በመግለጽ በዋናነት የተጀመረውን ያላየቶ ማከሚያ ማዕከል በሆስፒታልና በጤና ጠቢያ መጠናከር እንድሁም በሁሉም ቀበሌያት የቅኝትና አሳሰ ሥራዎችን በትኩረት መሠረትና የመረጃ ልውውጥ ሂደቱን ወጥ ማድረግ ላይ ትኩረት ከመስጠት በተጨማሪ የጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጠፍ በማድረግ የተገልጋይ ማህበረሰብ ፍላጎት ቅድሚያ መስጠት ላይ ማትኮር አስፈላጊ መሆን በማስገንዘብ አቅጣጫ አስቀምጧል።

ከቀረበው ረፖርት ማነሽ የኮሚቴው አባለት እስካሁን የተከናወኑ ተግባራት አበረታች በመሆናቸው በሂደቱም በቀጣይ መሰረት ባለባቸው ጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየት እንድሁም በቀጣይ በሚከናውነው ተግባራት ዙሪያ የጋራ ኃላፊነት ለወጣት በመግባባት የዕለቱ መድረክ መጠናቀቁን የጽ/ቤቱ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ አስታወቀ።

የሴቶች ህብረት መጠናከርና የጤና ልማት ሰራዊት መገንባት የሴቶች ድህነት በመርገጥ ጠንካራና የበለፀገ ማህበረሰብ ከመገንባት በሸገር በሴቶች ለይ የሚደርሰውን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ለመከላከል ወ...
18/01/2024

የሴቶች ህብረት መጠናከርና የጤና ልማት ሰራዊት መገንባት የሴቶች ድህነት በመርገጥ ጠንካራና የበለፀገ ማህበረሰብ ከመገንባት በሸገር በሴቶች ለይ የሚደርሰውን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ለመከላከል ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ።

ጥር 9/2016 ዓ.ም

በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ከከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ በጋራ በመሆን አድሱን የሴቶች ህብረት አደረጃጀት የንቅናቄ መድረክ መካሄዳቸውን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ገለፀ።

በንቅናቄ መድረክ የተገኙት የሾኔ ከተማ አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና ሪዮታዓለም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወርቁ ዮሐንስ የሴቶች ህብረት በአድስ መልኩ መደራጀት የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚ በሁሉም መስክ ለመርገጥ ሚናው የጎላ በመሆኑ አደረጃጀቱ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ በፍጥነት ተጠናቆ ወደ ሥራ እንድገባ ለባለድርሻ አካለት ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በኃይሉ ዳዊት በንቅናቄው መድረክ በመገኘት ስለ ሴቶች ህብረትና የጤና ልማት ሰራዊት ግንባታ እንድሁም በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት መከላከል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንፃር ስለሚኖረው ሚና ለባለድርሻ አካለት ገለፀ አድረገዋል።
አቶ በኃይሉ በማብራሪያቸው የለ ሴቶች ተሳትፎ ጠንካራና የበለፀገ ማህበረሰብ መገንባት እንደማይችል በመግለፅ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ለመከላከል የሴቶች ህብረት መደራጀትና መጠናከር ወሳኝ መሆንን ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለው በጤናው ሴክተር ባለፉት አመታት የሴቶች የጤና ልማት ሰራዊት አደረጃጀት በመጠናከር በእናቶችና ህፃናት ላይ ልደርስ የሚችለውን ሞት ከመስቀራት በሸገር የጤና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ለማሳከት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ እንዳለ በማስገንዘብ ተቋሙ የንቅናቄ አጋጣሚ በመጠቀም ጠንካራ አደረጃጀት በማስቀጠል ውስንነት በሚታይባቸው ቦታዎች የአቅም ግንቦታ ሥራዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ሰራዊት የሆነ ህብረት እንደምሆን አረጋግጠዋል።
በመድረኩም የሴቶች ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሜሮን ተደሰ የሴቶች ህብረት በአድስ መልኩ መደራጀት የሴቶችን ተሳትፎ ብቻ ስይሆን ተጠቃሚነታቸውንም ለመርገጥ የምጫወተው አስተዋጽኦ ከፈተኛ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በንቅናቄው መድረክ የቀበሌ አመራሮች የሴቶች ሊግ ኃላፊዎች የየቀበሌ የሴት አደረጀጀት የተለያዩ ሴክተር የሴቶች ተወካዮች እንድሁም የተለየዩ ባለድርሻ አካለት መገኘታቸውን የጽ/ቤቱ ሚድያና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ አስታወቀ።

ሾኔ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት EOC እና የተቋሙ PMT አባለት ወቅታዊ የኩፍኝ ወረርሽኝና በታህሳስ ወር የተከናወኑ ተግባራትን በጋራ ገምግሞ ቀጣ...
17/01/2024

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት EOC እና የተቋሙ PMT አባለት ወቅታዊ የኩፍኝ ወረርሽኝና በታህሳስ ወር የተከናወኑ ተግባራትን በጋራ ገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጡን አስታወቀ።

ጥር 8/2016 ዓ.ም

ጥር8/2016 ዓ.ም (የሾ/ከ/አስ/ጤ/ጽ/ቤት) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ወቅታዊ የኩፍኝ ወረርሽኝ ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችንና በታህሳስ ወር የተከናወኑ ተግባራትን በEOC እና በPMT በጥልቀት በጋራ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጡን የከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ገለፀ።

በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በኃይሉ ዳዊት የኩፍኝ ወረርሽኝ አጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች ከተከሰተ ጀምሮ የከተማ ማህበረሰብ ከለው ማህበራዊ መስተጋብር አንፃር በከፈተኛ ደረጀ ስጋት በመሆኑ ተግባራት በቅንጅት በልዩ ትኩረት በከተማ አስተዳደር ሥር ያሉ ተቋማትን በማስተባበር እንድሁም በዬ ጤና ተቋማት የተቋቋሙ የፈጣን ምላሽ ሰጭ ኮሚቴ በመቀናጀት በረካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ኃላፊው አክለው እስከአሁን የተከናወኑ ተግባራትን በመጠናከር በዋናነት በመከለከሉና በመቆጣጠሩ ሂደት በተቀመጠው ተቋማዊ አሰራር ሁሉንም የጤና ተቋማት መንቀሳቀስና በፍጥነት ስጋት እንዳይሆን መስረት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም በታህሳስ ወር የተከናወኑ ተግባራት አበረታች በመሆኑ የተሻለ አፈጻጸም የታየባቸውን ተግባራት መጠናከርና በውስንነት የተለዩ ተግባራት ላይ ፈጥኖ ወጤት ማስመዝገብ በሚቻልበት ሁኔታ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በመጨረሻም የተቋሙ የEOCና የPMT አባለት በተሰጠው የሥራ አቅጣጫ የተሻለ ተግባር ለመፈጸም የጋራ ማግባባት በመፈጠሩ የዕለቱ ስብሰባ መጠናቀቁን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የሚድያና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
ሾኔ

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በኃይሉ ዳዊት በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረውን የገና በዓል በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት፦          ...
06/01/2024

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በኃይሉ ዳዊት በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረውን የገና በዓል በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት፦

ታህሳስ 27 ቀን 2016 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለ2016 ዓ.ም ለጌታችን ለመድህንታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አያይዘውም በዓሉን በሚናከብረበት ጊዜ ለጤና ልዩ ትኩረት በመስጠትና አመጋገበችንን በማስተካከል በተለይም ቅበት የበዛባቸውን ምግቦች ጥንቃቄ በማድረግ እንድሁም የአካባቢውን ንፅህና በመጠበቅ ከበዓሉ ጋር ተያይዞ የሚደረገውን ዕርድ ቄራ በማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካለት ለከተማው ውበት የበኩላቸውን እንድትወጡ ስሉ ጠይቀዋል።

በመጨረሻም በዓሉ የሠላም፤የጤና፤የወንድማማችነት የብልግና የመትረፈረፍ እንድሆን ተመኝተዋል።
በተጨማሪም በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን ወገኖች የመጠየቅ የመርዳትና የማገዝ ኢትዮጵያዊ ባህላችንን በጠበቀ መልኩ ይሆን ዘንድ ያለቸውን እምነት ገልጸዋል።

የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት የተቀናጀ የተቋማት ድጋፋዊ ክትትል ሥራ በከተማ አስተዳደር ሥራ ባሉት በሁሉም የጤና ተቋማት እያከናወነ መሆኑን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤ/ጽ/ቤት ገለፀ። ...
03/01/2024

የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት የተቀናጀ የተቋማት ድጋፋዊ ክትትል ሥራ በከተማ አስተዳደር ሥራ ባሉት በሁሉም የጤና ተቋማት እያከናወነ መሆኑን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤ/ጽ/ቤት ገለፀ።

ታህሳስ 24/2016 ዓ.ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት የተቀናጀ ተቋማዊ ድጋፍ ክትትል በሁሉም ተቋማት እየተከናወነ መሆኑን ገለፀ።

የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል የኮማንዶ ፖስት ሰብሰብ ወ/ሮ አዱኛ ለገሠ የሁለተኛ ሩብ ዓመት የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል ሥራ በመዋቅሩ በሁሉም ጤና ተቋማት ከ22/4/2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ እንደሆነ ለጽ/ቤቱ የሚድያና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ አስታውቋል።
ወ/ሮ አዱኛ የድጋፍ ቡድኖች ከሁሉም የሥራ ሂደት የተዋቀሩና ባለፉት 3 ወረት በሁሉም ተቋማት የተከናወኑ ተግባራት በመረጃ ደረጃ የተነበቡ ስለመሆናቸው በማረጋገጥ በቀጣይ ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ ለማስቀጠልና በተለያዩ መድረኮች በውስንናት የተገመገሙ ነገሮች በፍጥነት ማረም በሚቻልበት ሁኔታ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ እንድየደረጉ ኦሬንተሽን መሰጠቱን ገልጸዋል።

ለ5 ቀናት በሚቆየው ድጋፋዊ ክትትል ሥራ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፤የዌራ ጤና አጠበበቅ ጠቢያ፤በ6ቱም ቀበሌ የሚገኙ ጤና ኬላዎች እንድሁም የተመረጡ የግል ጤና ተቋማት እንደተካተቱ በማብራሪያ አስረድተዋል።

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት
ሾኔ

"የኩፍኝ በሽታ የኩፍኝ ሻይረስ በሚባል ረቂቅ ተህዋስ የሚከሰትና በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው የሚዘመት የበሽታ ዓይነት ነው።
02/01/2024

"የኩፍኝ በሽታ የኩፍኝ ሻይረስ በሚባል ረቂቅ ተህዋስ የሚከሰትና በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው የሚዘመት የበሽታ ዓይነት ነው።

"ከወባ በሽታ የፀዳች ኢትዮጵያን ለማየት የአመራሩንና እና የህበረተሰቡ ተሳትፎ ጉልህ ሚና አለው!!
02/01/2024

"ከወባ በሽታ የፀዳች ኢትዮጵያን ለማየት የአመራሩንና እና የህበረተሰቡ ተሳትፎ ጉልህ ሚና አለው!!

Address

On The Way Of Addis Abeba To Arbaminch Main Street
Shone
GIRMAAYELEBUILDING

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251911666511

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የሾኔ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት:

Videos

Share