Hadiya zone Government Communication Affairs Department

Hadiya zone Government Communication Affairs Department This is Hadiya Zone Government Communication

የሀድያ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

This is the offical facebook home page of Hadiya Zone Communication

‹ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግሥትንና ሕዝብን ተጠቃሚ በማድረግ አንድ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማኀበረሰብን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ነው።

የከተራና ጥምቀት በዓል በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው  ቅድመ ዝግጅት  መደረጉን የሀድያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።  ህብረተሰቡም ...
17/01/2025

የከተራና ጥምቀት በዓል በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሀድያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ህብረተሰቡም በዓሉን ሲያከብርም የራሱን እና የአከባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ጥሪውን አስተላልፏል።

።።።።።።።።።ሆሳዕና፣ ጥር 9/2017 ዓ.ም።።።።።።።

የሀድያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ተሾመ ባቲሶ የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።

አዛዡ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት በአለም አቀፍ ቅርስነት የተመዘገበዉ የከተራና የጥምቀት በዓል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ኃይማኖታዊ ትውፊቱ ተጠብቆ ባማረና በደመቀ ሁኔታ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች እንደሚከበር አስታውሰው።

በዓሉ በዘንድሮ ዓመትም በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጎ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመዋል።

የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ተሾመ ባቲሶ አያይዘውም እንዳብራሩት ታቦታቱ ካሉበት ወደ ጥምቀተ ባህሩ ከሚወርዱበት ከከተራ ዕለት ጀምሮ ተገቢውን እጀባ ከማድረግ ባለፈም በማደሪያቸው ተገቢው ጥበቃ ተደርጎ ወደ ደብራቸው እስኪመለሱ ድረስ ፖሊስ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ተገቢውን ጥበቃ ማድረግ እንዲቻል በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የፖሊስ መዋቅሮች አባላት መመደባቸውንም ተናግረዋል።

ዋና አዛዡ አያይዘውም በዓሉ በሰላም እንዲከበር የፀጥታ ኃይሉ፣ የፓትሮል ቅኝት ከማድረግ ባለፈም የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም በዕለቱ ሊፈጸሙ የሚችሉ ወንጀሎችን ለመከላከል የፀጥታ ኃይሉ ዝግጅቱን አጠናቆ በስምሪት ላይ ይገኛል ብለው፤

ህብረተሰቡም በዓሉን ሲያከብር የራሱን እና የአከባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል በማሳሰብ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ተሾመ ባቲሶ ለመላዉ የእምነቱ ተከታዮች ለ 2017 ዓ.ም እንኳን ለከተራ እና ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል ።

የከተራና ጥምቀት በዓል በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው  ቅድመ ዝግጅት  መደረጉን የሀድያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።  ህብረተሰቡም ...
17/01/2025

የከተራና ጥምቀት በዓል በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሀድያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ህብረተሰቡም በዓሉን ሲያከብርም የራሱን እና የአከባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥልም የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ጥሪውን አስተላልፏል።

።።።።።።።።።ሆሳዕና፣ ጥር 8/2017 ዓ.ም።።።።።።።

የሀድያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር ተሾመ ባቲሶ የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።

አዛዡ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት በአለም አቀፍ ቅርስነት የተመዘገበዉ የከተራና የጥምቀት በዓል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ኃይማኖታዊ ትውፊቱ ተጠብቆ ባማረና በደመቀ ሁኔታ በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች እንደሚከበር አስታውሰው።

በዓሉ በዘንድሮ ዓመትም በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጎ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመዋል።

የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ተሾመ ባቲሶ አያይዘውም እንዳብራሩት ታቦታቱ ካሉበት ወደ ጥምቀተ ባህሩ ከሚወርዱበት ከከተራ ዕለት ጀምሮ ተገቢውን እጀባ ከማድረግ ባለፈም በማደሪያቸው ተገቢው ጥበቃ ተደርጎ ወደ ደብራቸው እስኪመለሱ ድረስ ፖሊስ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ተገቢውን ጥበቃ ማድረግ እንዲቻል በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የፖሊስ መዋቅሮች አባላት መመደባቸውንም ተናግረዋል።

አዛዡ አያይዘውም በዓሉ በሰላም እንዲከበር የፀጥታ ኃይሉ፣ የፓትሮል ቅኝት ከማድረግ ባለፈም የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም በዕለቱ ሊፈጸሙ የሚችሉ ወንጀሎችን ለመከላከል የፀጥታ ኃይሉ ዝግጅቱን አጠናቆ በስምሪት ላይ ይገኛል ብለው፤
ህብረተሰቡም በዓሉን ሲያከብር የራሱን እና የአከባቢውን ሰላም በማስጠበቅ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል በማሳሰብ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ተሾመ ባቲሶ ለመላዉ የእምነቱ ተከታዮች ለ 2017 ዓ.ም እንኳን ለከተራ እና ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል ።

የመደመር ዕሳቤን መሰረት ያደረገ ሀገራዊና ክልላዊ የጋራ ትርክትን ማስረፅ የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ (ሆሳዕና፣ ጥር 9/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵ...
17/01/2025

የመደመር ዕሳቤን መሰረት ያደረገ ሀገራዊና ክልላዊ የጋራ ትርክትን ማስረፅ የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

(ሆሳዕና፣ ጥር 9/2017) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ እንደገለጹት የመደመር ዕሳቤን መሰረት ያደረገ ሀገራዊና ክልላዊ የጋራ ትርክት በህብረተሰቡ ውስጥ በማስረፅ በመንግሥትና በህዝብ መካከል የተጠናከረ ግንኙነት እንዲኖር በትኩረት እየተሰራ ነው።

በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት የሚያጋጥሙ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎችን ለመከለል የሚያስችል የቀውስ ጊዜ ዕቅድ በተገቢው በማቀድ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የተደራጀ የሚዲያ ሰራዊት በመገንባት ሁሉንም የሚዲያ አውታሮች በመጠቀም ብቃት ያለው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ በመስራት የጋራ ትርክት የበላይነትን ለማረጋገጥ በትኩረት መሰራቱንም አቶ ዘሪሁን አመላክተዋል።

ክልሉ ያሉትን ዕምቅ ፀጋዎችንና አቅሞችን በማስተዋወቅ ክልሉን ከአፍራሽ ኃይሎች በመታደግ የሰላም፣ የልማት እና የብልጽግና ማዕከል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ኃላፊው ተናግረዋል።

በየጊዜው የሚሰጡትን የህዝብ አስተያየቶች ወደ ውጤት በመቀየር የተቀናጀ የሚዲያ ዳሰሳ ስራ በመስራት አሉታዊ የሚዲያ ዘገባዎችን የማጋላጥና የመከላከል ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝም አቶ ዘሪሁን ጠቁመዋል።

በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀምን በተገቢው በመገምገም የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን አጠናክሮ ማስቀጠልና በጉድለት የተለዩትን ፈጥኖ ለማረም የሚያግዝ ምክክር እንደሚደረግም አመላክተዋል።

በመድረኩ የመጀሪያው ግማሽ አመት ዕቅድ የአፈፃፀም እና የድጋፋዊ ክትትል ግብረ መልስ ሪፖርት እየቀረበ ነው።

በመርሐ ግብሩ በክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግዛቸው ዋሌራ፣ የርዕሰ መስተዳደሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ እና የክልሉ ክላስተሮች የኮሙኒኬሽን አስተባባሪዎች፣ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#የክልሉ ኮሙኒኬሽን

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የሀዲያ ዞን መሰረታዊ ድርጅት የብልጽግና ፓርቲ የ2ኛ መደበኛ ቅድመ-ጉባኤ ኮንፍራንስ ተካሄደ።በኮንፍራንሱ የብልጽግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ላይ የተደ...
16/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የሀዲያ ዞን መሰረታዊ ድርጅት የብልጽግና ፓርቲ የ2ኛ መደበኛ ቅድመ-ጉባኤ ኮንፍራንስ ተካሄደ።

በኮንፍራንሱ የብልጽግና ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች የቀረቡ ሲሆን ለ2ኛ የፓርቲ ጉባኤ የሚሳተፉ አባላት ምርጫም ተካሂዷል።

።።።።።።።። ቀን 08/05/2017 ዓ/ም ።።።።።።።።

የአመለካከት ጥራት፣የአመራርነት ኃላፊነትን በብቃት መወጣት፣ስብዕናና ሥነ-ምግባር ከመላበስ አኳያ እና በሌሎች የፓርቲ አባልነት ግዴታዎችን መወጣት በሚሉ ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች ከአባላቱ ጋር ውይይት ሲደረግ የቆየ ሲሆን በመጨረሻ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ መሻሻል ያለባቸው አንቀጾች እና ቃላት መሻሻላቸውን ለጉባኤው ቀርቧል።

በኮንፈረንሱ ከጉባኤ እስከ ጉባኤ በተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ የተደረገ ሲሆን የዞኑ የኢንስፔክሽንና ስነ- ምግባር ኮሚሽን የአፈፃፀም ሪፖርትና የተሻሻለው የፓርቲዉ መተዳደሪያ ደንብ ቀርቧል።

አባላትም በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የሚያሳይ ሰነድ ላይ ያላቸውን ሀሳብ አስተያየት እንዲሁም የግንዛቤ ጥያቄዎችን በተመለከተ ለመድረኩ አቅርበዋል።

የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ እና መድረኩን የመሩት አካላት ከቤቱ ለቀረቡት የግንዛቤ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተው በ2ኛ ጉባኤ መቅረብ ያለባቸውን ጥያቄዎችን በተመለከተ ጉባኤውን ለመሳተፍ የሚመረጡ አካላት ይዘውት የሚሄዱት ጉዳይ ይሆናል በማለት ተናግረዋል።

የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ አባላት የሚመረጡበትን የምርጫ መስፈርት ለመደንገግ የወጣው መመሪያና ደንብ ቁጥር13/2017 ሰነድ ለተሳታፊው ቀርቦ ምርጫው ተካሂዷል።

በመድረኩ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣የሀዲያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣ የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ሰዴቦን ጨምሮ የዞኑ አመራር እና ፐብሊክ ሰርቫንት ተገኝተዋል።
በታከለ አጋፋሪ

14/01/2025
14/01/2025
በሀድያ ዞን ለ2017/2018 ምርት ዘመን ለበልግና  መኸር ወቅት የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ አስቀድሞ  ለማድረስ  አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብ...
14/01/2025

በሀድያ ዞን ለ2017/2018 ምርት ዘመን ለበልግና መኸር ወቅት የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ አስቀድሞ ለማድረስ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በዞኑ ለበልግና መኸር ወቅት የሚውል ከ 3 መቶ ሺህ 9 መቶ 60 ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ የማቅረብ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤

እስካሁን ከ 40 ሺህ ኩንታል በላይ ዳፕና ዩሪያ የአፈር ማዳበሪያ ዞን ማዕከል ደርሶ ወደ 120 የማሰራጫ ማዕከላት ተደራሽ የማድረግ ስራ በይፋ ተጀምሯል።

።።።።ሆሳዕና፣ ታህሳስ 06/2017 ዓ.ም።።።።።።

የሀድያ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ታደሰ እንደገለፁት በዞኑ ለ2017/18 ምርት ዘመን ለአርሶ አደሩ ለበልግና መኸር ወቅት የሚያስፈለግውን የአፈር ማዳበሪያ አስቀድሞ ለማድረስ ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ትግበራ መግባቱን ጠቅሰው ሲያብራሩ፤

በምርት ዘመኑ ለመስኖ፣ ለበልግና ለቀጣይ መኸር ወቅት የግብርና ልማት ግቦችን ለማሳካት በግብዓት አቅርቦት ላይ ትኩረት በመስጠት በተለይም የአፈር ማዳበሪያ የአርሶ አደሩን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ዕቅድ በማቀድ አቅርቦቱን ለማሳካት በቂ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር መገባቱን ተናግረዋል ።

በዚሁም መሰረት ለበልግ፣ ለመስኖ እና ለመኸር እርሻ ወቅት የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ዓይነትና መጠን በመለየት ከማዕከል ተጓጉዞ ዞን የደረሰውን ለሁሉም መዋቅሮች እንዲሰራጭ በማድረግ አርሶ አደሩ በወቅቱ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አያይዘውም የስርጭቱን ሂደት ሲገልፁ የበልግ አምራች ወደሆኑ ወረዳዎች ቅድሚያ ተሰጥቶ እስከ ስርጭት ጣቢያዎች ድረስ ሟሟጓዝ ተጀምሯል።

ከዚሁ ጎን ለጎን ባለፉት ዓመታት የአፈር ማደበሪያ ለአርሶ አደሩ በየአካባቢው የማሰራጫ ማዕከል ለማድረስ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አንዳንድ አካባቢዎች መንገዶች ጭቃ በመሆናቸው የተነሳ የትራንፖርት መኪናዎች ሊገቡ ባለመቻላቸው አርሶ አደሩ ለዕንግልት መዳረጉን አስታውሰዋል።

አያይዘውም በተያዘው ዓመት የዚህ አይነት ችግር እንዳይከሰት የዞኑ ግብረ ኃይልና ቴክኒክ ኮሚቴ ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው በመነጋገር የአርሶ አሩን ፍላጎት ለማርካት ለመኸር ወቅት የሚውለውን የአፈር ማዳበሪያ ወደ ማሰራጫ ጣቢያዎች ከወዲሁ የማድረሱ ተግባር መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ተናግረዋል።

የዚህ ዓመት የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት በተሻለ ሂደት ላይ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ሀብታሙ በየደረጃው ካለው አመራር ጋር በመቀናጀት ለአርሶ አደሩ የአፈር ማዳበሪያ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

አርሶ አደሩ ከበልግ ስራ ጎን ለጎን የመኸር እርሻ ዝግጀት ስራዎችን በስፋትና በተጠናከረ መንገድ ወደ ተግባር ገብተው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።

አርሶአደሩ የማሳ ዝግጅት በማድረግ ለማሳው የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ በዓይነትና በመጠን መውሰድ እንደሚችል የመምሪያው ኃላፊ ዶ/ር ሀብታሙ አሳስበዋል።

የሀድያ ዞን ህብረት ስራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ኢቴቦ በበኩላቸው እንዳብራሩት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የአርሶ አደሩን ፍላጎት ለማሳካት በየዓመቱ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቁመው የዞኑ አብይ ኮሚቴ በተያዘው ዓመትም የተጀመረው ጥረትን አጠናክሮ በማስቀጠል ለበልግ፣ ለመስኖ እና ለመኸር ወቅት የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተው፤

በዘንድሮ ዓመት ለመስኖ፣ ለበልግና መኸር ወቅት የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦት የአርሶ አደሩን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ትግበራ የተገባው አጠቃላይ ዕቅድ ከ 3 መቶ 96 ሺህ በላይ ሲሆን እስካሁን ዳፕ 19 ሺህ 6 መቶ 20 ኩንታል ፣ ዩሪያ 20 ሺህ 6 መቶ 93 ኩንታል በድምሩ 40 ሺህ 66 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ዞን ማዕከል ደርሶ በዞኑ ወደ ሚገኙ 120 የማሰራጫ ማዕከላት ተደራሽ የማድረግ ስራ በይፋ የተጀመረ ሲሆን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በተያዘው ዓመት በዞኑ የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ የታቀደው ዕቅድ ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ መጨመሩን አቶ ታደለ ጠቁመዋል።

ሂደቱ ቀድሞ መጀመሩ አርሶ አደሩ በአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት ይደርስበት የነበረውን መጉላላት በማስቀረት ሰብሉን በአግባቡ እንዲዘራ በማድረግ ውጤታማ እንዲሆን እንደሚያደርገውም አመልክተዋል።

ሊቻ የሀድያ ገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ደስታ ገብረ ወልድ ከጉዳዩ ጋር አያይዘው እንደገለፁት እንደሚታወቀው ከዚህ በፊት እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ዞናችን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ከአርሶ አደሩ ፍላጎት ጋር ባለመጣጣሙ እጥረት መፈጠሩን አስታውሰው ፤

ይኽንን መነሻ በማድረግ መንግስት የዞኑ አስተዳደር ከመቼውም ጊዜ በላይ ችግሩን ለመቅረፍ ትኩረት ሰጥቶ በማቀድ የተገዛውን የአፈር ማዳበሪያ ከአገር አቀፍ ማዕከል የ ወደ ዞኑ ማዕከል እንዲሁም ወደማሰራጫ መጋዘኖች አያጓጓዙ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

የዘንድሮው ዓመት የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በአቅርቦትና ስርጭቱ በጣም ጥሩ የሚባል ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የአፈር ማደበሪያ ለአርሶ አደሩ በየአካባቢው በሚገኙ መጋዘኖች በወቅቱ ተደራሽ አድርጎ ማሰራጨት እንዲቻል ከባለፈው አመት አፈፃጸም የተስተዋሉ ጠንካራ ጎኖችና እጥረቶችን በመገምገም ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ሊቻ የሀድያ ገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒዬን ከዞኑ ግብርና መምሪያ እና ህብረት ስራ ጽ/ቤት ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አቶ ደስታ አያይዘውም ከዞን እስከ ቀበሌ በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ ጠንከራ ክትትል በማድረግ በፍትሐዊነት እየተሰራጨ እንደሚገኝ ገልፀው አርሶ አደሩ በተገቢው መንገድ ተደራሽ እንዲሆን ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በካሳሁን አባይነህ

የበጋ ስንዴ እርሻችን በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር)
14/01/2025

የበጋ ስንዴ እርሻችን በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር)

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዱባይ ማራቶን በሁለቱም ጾታዎች በማሸነፍ በበላይነት አጠናቀቁ ዛሬ ማለዳ በተደረገው 24ኛው የዱባይ ማራቶን አትሌት ቡቴ ገመቹ በወንዶች እና አትሌት በዳቱ ሂርጳ በሴ...
12/01/2025

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዱባይ ማራቶን በሁለቱም ጾታዎች በማሸነፍ በበላይነት አጠናቀቁ

ዛሬ ማለዳ በተደረገው 24ኛው የዱባይ ማራቶን አትሌት ቡቴ ገመቹ በወንዶች እና አትሌት በዳቱ ሂርጳ በሴቶች አሸንፈዋል።

በወንዶች ውድድር ኢትዮጵያውን አትሌቶች ከ1 እስከ 10 ያለውን ደረጃ ይዘዋል።

አትሌት ቡቴ ገመቹ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ50 ሴኮንድ በርቀቱ የዓመቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል።

አትሌት ብርሃኑ ፀጉና አትሌት ሽፈራው ታምሩ ሁለተኛና ሶስተኛ ወጥተዋል።

በተመሳሳይ በሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 10 በመውጣት በበላይነት አጠናቀዋል።

አትሌት በዳቱ ሂርጳ 2 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ27 ሴኮንድ በመግባት አሸንፋለች።

አትሌት ደራ ዲዳ እና አትሌት ትዕግስት ግርማ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

በውድድሩ የማሸነፍ ግምት ተሰጥቷቸው ከነበሩት አትሌቶች አንዷ የሆነችው ዘይነባ ይመር አራተኛ ወጥታለች።

በሁለቱም ጾታዎች አንደኛ ለወጡ አትሌቶች የ80 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በአጠቃላይ የውድድሩ አዘጋጅ አካል የ504 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ሽልማት ለአትሌቶች አበርክቷል።

ከእ.አ.አ 1998 አንስቶ እየተካሄደ ያለው የዱባይ ማራቶን በዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ የተሰጠው የጎዳና ላይ ውድድር ነው።(ኢዜአ)

የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ ****************************የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ...
11/01/2025

የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
****************************

የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፕሬዝዳንቱ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው ፤ “የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ እንኳን ወደ ኢትዮጵያ መጡ እላለሁ” ብለዋል፡፡EBC

በደቡብ ኢትዮጵያ  ክፍል ሰማይ ላይ የታየው ክስተት በሰው ሰራሽ የስፔስ ቁስ ምክንያት የተከሰተ ሊሆን ይችላል፦ የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦፓሻል ኢኒስቲትዩት*************በትናንትናው ምሽ...
10/01/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክፍል ሰማይ ላይ የታየው ክስተት በሰው ሰራሽ የስፔስ ቁስ ምክንያት የተከሰተ ሊሆን ይችላል፦ የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦፓሻል ኢኒስቲትዩት
*************

በትናንትናው ምሽት በደቡብ ኢትዮጵያ ክፍል ሰማይ ላይ እየተቃጠለ ተቆራርጦ ወደ ምድር ሲጓዝ የታየው ቁስ በሰው ሰራሽ የስፔስ ቁስ ምክንያት የተከሰተ ሊሆን እንደሚችል የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦፓሻል ኢኒስቲትዩት ገለፀ፡፡

በስፔስ ሳይንስ እና ጂኦፓሻል ኢኒስቲትዩት የከባቢ አየር ሳይንስ ተመራማሪ የሆኑት ገመቹ ፋንታ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ዶት ስትሪም ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ጊዜ ያበቃላቸው ሳተላይት እንዲሁም ሳተላይቶችን የመጠቁባቸው የሮኬት ቁርጥራጮች ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡

በማንኛውም ሰው ሰራሽ መንገድ ህዋ ላይ የሚንቀሳቀሱ ነገሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ወደ ከባቢ አየር ውስጥ ሲገቡ የመቃጠል እና ተሰባብሮ የመውረድ ምልክቶችን እንደሚያሳዩ ገልጸዋል፡፡

ክስተቱ የተፈጠረው በተፈጥሮአዊ የህዋ አካላት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ጠቅሰዋል፡፡

ከመሬት እና ከሶላር ሲስተም አፈጣጠር አንጻር አለቶች በመኖራቸው በማንኛውም ጊዜ እየተቆራረጡ ሊወርዱ እንደሚችሉ ነው ያነሱት፡፡

በዓለም ላይ እንደዚህ ያለ ሁነት እንደሚከሰቱ የሚናገሩት ተመራማሪው፤ አልፎ አልፎ ቁጥራቸው በርከት ያሉት ወደ ምድር እንደሚወርዱም ገልፀዋል፡፡

ሰው የሚኖርበት ቦታ ከ 4 እስከ 5 በመቶ እንደማይበልጥ የሚናገሩት ተመራማሪው፤ ተቆራርጠው የሚወርዱ ነገሮች ከሰው ዕይታ ውጪ የሚከሰቱበት ሁኔታው ስለመኖሩም ጠቅሰዋል። አልፎ አልፎ ግን ለሰው ዕይታ እንደሚጋለጡም ነው አያይዘው የገለጹት፡፡

ጥናቶች እንደሚያሳዩት በዓመት እስከ 6 ሺህ ድረስ ተቆራርጠው ምድር የሚደርሱ እና አለፍ ሲልም የአሸዋ ቅንጣት በመሆን ወደ ምድር የሚወርዱ ስለመኖራቸው ነው ተመራማሪው የተናገሩት፡፡

የሚቃጠሉበት ምክንያት ደግሞ ወደ ከባቢ አየር ሲገቡ ከከባቢ አየር ጋር በሚያደርጉት ፍትጊያ የሚፈጠር ስለመሆኑም አያይዘዋል፡፡

"አሁን እንዳለን መረጃ በደቡባዊ ክፍል የታየው ምስል ሰማይ ላይ እየተቃጠለ ነው የሄደው፤ አርፏል አላረፈም የሚለውን እስካሁን ማወቅ አልቻልንም" ብለዋል፡፡

ምድር ሦስት አራተኛዋ ውኃ በመሆኑ በአብዛኛው ውኃ ውስጥ እንደሚወድቅ የሚናገሩት ተመራማሪው፤ ሰዎች የሚኖሩበት አካባቢ ካልወደቀ በስተቀር ጉዳት እንደሌለው ነው የተናገሩት፡፡
EBC

ትናንት ምሽት በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ የታየው ክስተት...የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢት...
10/01/2025

ትናንት ምሽት በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ የታየው ክስተት...

የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸውን አስታውቋል።

ተቋሙ በታዩት ተንቀሳቃሽ ምስሎች ለመመልከት እንደቻለውም የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አሊያም የሚቲዮር አለቶች እንደሚመስሉ ይፋ አድርጓል።

ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ነው የተመላከተው።

የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ያስችል ዘንድ ሁኔታውን በቅርበት እያጣራ እንደሚገኝ ተቋሙ ገልጿል።

የተጣራ መረጃ ሲደርስ ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚደረግም ተጠቁሟል።

የማጣራት ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ ተቋሙ አሳስቧል።FBC

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የሀዲያ ዞን የብልጽግና ፓርቲ አመራር የግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።።።።።።።።።።።ጥር 1/2017ዓ.ም።።።።።በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ...
09/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የሀዲያ ዞን የብልጽግና ፓርቲ አመራር የግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

።።።።።።።።።።ጥር 1/2017ዓ.ም።።።።።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን በሚካሄደው የአመራሮች የግምገማ መድረክ የአመራሩን ጉድለቶች በመቅረፍ፣ የተጀመሩ የለውጥ ትሩፋቶች ማጽናትና የኢትዮጵያን ህልም እውን ማድረግ እንዲሁም ብልጽግና ፓርቲ እስካሁን ያስመዘገባቸውን ድሎች የሚያጸናበትን ምህዳር ለመፍጠርና አመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በመፍጠር በአፈፃፀም ውጤታማ ሆኖ ለቀጣይ ተልዕኮ ትክክለኛ ቁመና ያለው አመራር ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

በመድረኩም የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣የሀዲያ ዞን ብ/ፓ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሀንዲሶ፣የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ክብርት ወይዘሮ እቴነሽ ሙሉጌታን ጨምሮ የዞን ፑል አመራሮች፣የወረዳና የከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አካለት ተገኝተዋል።

በምህረተአብ ዘለቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ዛሬ ያካሂዳል(ሆሳዕና፣ጥር 1/2017)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔው የተለያዩ...
09/01/2025

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ዛሬ ያካሂዳል

(ሆሳዕና፣ጥር 1/2017)

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔው የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ምክር ቤቱ በጉባዔው፤ የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት ለመደንገግ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በሕግና ፍትሕና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል።

በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ተቋማት ጋር የመረጃ ግንኙነት በማጠናከር  በሁሉም  ዘርፎች የህብረተሰቡን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ል...
08/01/2025

በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ተቋማት ጋር የመረጃ ግንኙነት በማጠናከር በሁሉም ዘርፎች የህብረተሰቡን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ

ሆሳዕና ፣ታህሳስ 30/2017 በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ተቋማት ጋር የመረጃ ግንኙነት በማጠናከር በሁሉም ዘርፎች የህብረተሰቡን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ገለፀ።

ከተሞች መዘመን እንዲችሉ በከተሞች የሚገነቡ ግንባታዎች ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑና የኮሪደር ልማቶችን ጥራት ለማስጠበቅ ተገቢ ክትትል እየተደረገ መሆኑም ተገልጿል::

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ባዩሽ ተስፋዬ፤ የክልሉ መንግስት ለሰላም መስፈን በሰጠው ልዩ ትኩረት የተገኘውን አስተማማኝ ሰላም በሁሉም የልማት ዘርፎች ለመድገም የጠራ መረጃ ማሰባሰብና ማሰራጨት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ጥራት ያለውን ትምህርትን፣ መከላከልን መሰረተ ያደረገ የጤና ሽፋን በማሳደግ፣ በምግብ ዋስትና፣ በመሰረተ ልማት አውታሮችና በሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡን ውጤታማና ፍትሃዊ ተጠቃሚ ለማድረግ ትክክለኛ መረጃን ማሰባሰብ እና ማሰራጨት የሚችል የመረጃ ዌብ ሳይት በማበልጸግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ተቋማት ጋር የመረጃ ግንኙነት በማጠናከር በሁሉም ዘርፎች የህብረተሰቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ዶክተር ባዩሽ አመላክተዋል::

ከኢኮኖሚ ዕድገት የተመጣጠነ፣ አምራች እና የበለጸገ ህብረተሰብ ለመፍጠር በስነ-ህዝብ ምጣኔ ላይ ልዩ ትኩረት መደረጉንም ዶክተር ባዩሽ ጠቁመዋል።

ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የኑሮ ውድነትን ለመከላከልና ገበያን ለማረጋጋት በተሰራው ስራ በክልሉ 104 የሰንበት ገበያ በማቋቋም አበረታች ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል።

ክልሉ የብዝሃ ማዕከላት በመሆኑ የሚገነቡ ግንባታዎች ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የኮሪደር ልማቶች ጥራታቸውን ለማስጠበቅ ተገቢ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ዶክተር ባዩሽ መግለጻቸውን ደሬቴድ ዘግቧል።

07/01/2025

በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እንደሚከተለው ሆኖ ተወስኗል።

1 አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር፣
2 አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር፣
3 አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር፣
4 አንድ ሊትር የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር፣
5 አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር እንዲሁም
6 አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ እንዲሸጥ ሚኒስቴሩ ወስኗል።

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉሆሳዕና፣ ታሕሣሥ 28፣ 2017  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገና በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረ...
06/01/2025

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ሆሳዕና፣ ታሕሣሥ 28፣ 2017 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የገና በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ

ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን ሕግ ጥሶ ከእግዚአብሔር ጋር የተጣላው ራሱ የሰው ልጅ ነበረ፡፡ ዕርቅን አውርዶ ሰላምን ለማስፈን በረት ድረስ የመጣው ግን እግዚአብሔር ነው፡፡ እንደ ቅዱሳት መጻሕፍት አስተምህሮ እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ፣ አሸናፊ፣ የሚሳነው አንዳች የሌለ ነው፡፡ ነገር ግን ለዕርቅ እና ለሰላም ሲል ወደ ማይገባው ሥፍራ መጣ፡፡ አሸናፊ ቢሆንም እንደ ተሸናፊ ሆነ፡፡ ዐቅም ቢኖረው እንደ ዐቅመ ቢስ ሆኖ ታየ፡፡ በሁሉ ሀብታም ሲሆን፣ ራሱን ታናሽ አደረገ፡፡ ይህ ሁሉ ለዕርቅና ለሰላም የተከፈለ የታላቅነት ዋጋ ነው፡፡

እግዚአብሔር ለዕርቅ እና ለሰላም ሲል በደካማዋ ከተማ በቤተልሔም፣ በተናቀችው ሥፍራ በበረት መገኘቱ የገባቸውም ያልገባቸውም ነበሩ፡፡ የገባቸው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርደው “ሰላም እና ዕርቅ በምድር ይሁን” ብለው ዘመሩ፡፡ የገባቸው፤ ከምሥራቅ ኮከቡን አይተው፣ እጅ መንሻውን ይዘው መጡ፡፡ የገባቸው፤ በረታቸውን ለቅቀው ለድንግል ማርያም እና ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰጡ፡፡ የገባቸው፤ የሰማይ መላእክቱን ተከትለው ወደ በረት ሄደው እርቅና ሰላምን አመሰገኑ፡፡

ያልገባቸው ሰዎች፣ የዕርቅ እና የሰላሙ ዐዋጅ እየታወጀ እነርሱ ግን ተኝተው ነበር፡፡ የመንደር ጌቶች እነ ሄሮድስ፣ የሰው ልጅ ሰላም ማግኘት ሳይሆን ከጠላት ያገኙት ሥልጣን ያስጨንቃቸው ነበር፡፡ የይሁዳ ሰዎች፤ ዓለም በማይመለስበት ሁኔታ እየተቀየረ፣ እነርሱ ግን እየሆነ ያለውን ለውጥ አያዩም አይሰሙም ነበር፡፡ ከሰማይ መላእክት ወርደው፣ ከምድር እረኞች ነቅተው ተአምር ሲሠራ፤ እነርሱ ግን በዕንቅልፍ ደንዝዘው ነበር፡፡እ ነርሱ እያንቀላፉ ከተማቸው ቤተልሔም ተቀይራለች፡፡ የእንጀራ ቤት ሆናለች፡፡ ታሪኳ ተቀይሯል፡፡ ታናሽ ከተማነቷ ተቀይሯል፡፡

ያልገባቸው፣ ሰላምና ዕርቅ ሲባሉ የድካምና የዐቅመ ቢስነት ምልክት አድርገው ተመለከቱት፡፡ ሰይፍና ጎራዴ የለመዱ፤ መግደልና ማጥፋት ጀግንነት የሚመስላቸው ነበሩና፡፡ ሰላም ድካም፣ ዕርቅም ሽንፈት ይመስላቸው ነበር፡፡ ስለዚህም በእኩለ ሌሊት ከመሸ፣ በከብቶች በረት ለሁሉ የመጣውን ሰላም አቅለው አንቀበልም አሉ፡፡ እነ ሄሮድስ ሰይፍ መዘዙ፡፡ ሰላምን አሳደዱ፤ ሰላማዊ ሕጻናትንም ፈጁ፡፡ ሄሮድስ የገዛ ሕዝቡን ለመጨፍጨፍና ለመግዛት በጠላት የተሾመ ሰው ነበር፡፡ የሚያስፈጽመው የእሥራኤል ጠላቶችን ዓላማ ነበረ፡፡

ይሄንን በዓል የምናከብር፤ ወይ ሰላምና ዕርቅን ከሚወዱት ወገን ነን፡፡ አለያም ሰላምንና ዕርቅን ከሚያሳድዱት ወገን ነን፡፡ መንግሥት ሰላምና ዕርቅን ደጋግሞ የሚያውጀው ዐቅም ከማጣት፣ ጉልበቱ ከመድከም የተነሣ አይደለም፡፡ ሁሉም ዓይነት መንግሥታዊ ዐቅሞች በእጁና በደጁ አሉ፡፡ ሰላምና ዕርቅ ግን ከሁሉ በበለጠ፤ ዘመን አሻጋሪ፣ ታሪክ ቀያሪ፣ የችግርና መከራ ዘመን ማብቂያ መፍትሔዎች በመሆናቸው ነው፡፡ ሁሉን አሸናፊ፣ ሁሉን አሻጋሪ ያደርጋሉ፡፡ ጠባሳ ሳይተዉ ቁስልን ያሽራሉ፤ ለልጅ ልጅ ቂምን ሳይሆን ሐሴትን ያወርሳሉ፤ ከመጠፋፋት ይታደጋሉ፡፡ የሰላምና የዕርቅ መንገድ የሚመረጠውም ለዚህ ነው፡፡

ሰላምና ዕርቅን መምረጥ፤ የኃያል ባለ-ራዕይ፣ የፍጹማዊ-አሸናፊና ባለታላቅ-ዐቅም በውዴታ የሚሸከመው የከፍታ ግዳጅ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ ይችል ነበር፡፡ ሰላምን እያወጀ ወደ ከብቶች በረት የመጣው ግን እርሱ ኃያሉ ነው፡፡ የአዳም ልጆች በሠገነት ሲወለዱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው በበረት የተወለደው፡፡ እግዚአብሔር ነው ለሰላምና ለዕርቅ ሲባል ከቤተልሔም እስከ ቀራንዮ መከራን የተቀበለው፡፡

መንግሥት ዛሬም ለሰላም እና ለዕርቅ እጁ እንደተዘረጋ ነው፡፡ ለሁሉ የሚሆን ሰላም በኃይል ሳይሆን በፍቅር መንገድ እንደሚመጣ ያውቃል፡፡ ለሰላምና ለዕርቅ በመሸነፍ ውስጥ ፍጹማዊ ማሸነፍ እንዳለ ያምናል፡፡ ጥቂቶች እንጂ ብዙኃኑ ከሰላም የሚገኘውን ክፍያ የሚሹ እንደሆነ ይረዳል፡፡

የጠላት መሣሪያ የነበረውን የሄሮድስን መጨረሻ ማየት ነው፡፡ ለሰላምና ለዕርቅ ጀርባቸውን የሰጡ የቤተልሔም ከተማ ሰዎችን ፍጻሜ ማሰብ ነው፡፡ እግዚአብሔር በረት ድረስ ሲፈልጋቸው አሻፈረኝ ብለው ነበር፡፡ ከዓመታት በኋላ በኃይልና በጉልበት ሲጎበኛቸው ግን፣ ፈልገው ሊያገኙት አልቻሉም፡፡ ቤታቸው የተፈታ ሆኖ ቀረ፡፡ ከዚያ በኋላ ፍለጋቸው መባከንና መቅበዝበዝ ሆነ ፡፡ ዕርቅና ሰላምን የሚገፋ ሁሉ መጨረሻው እንደዚህ ነው፡፡

ሁሉም ጊዜ አለው፡፡ በጊዜው መጠቀም የጠቢባን ድርሻ ነው፡፡ ለሰላም የተዘረጉ እጆች እንደተዘረጉ አይቀሩም፡፡ ለሰላም ሲባል ወደ ምድር የወረዱ ሁሉ እንደ ወረዱ አይቀሩም፡፡ ለሰላም ሲባል ደካሞች መስለው የታዩ ሁሉ፣ ኃይላቸው በጊዜው ይገልጣሉ፡፡ የግድግዳው ጽሑፍ ይመጣል፡፡ የተዘረጋው ብራና ይጠቀለላል፡፡

ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ሦስቱ ሰላማውያን ቦታ አላገኙም ነበር፡፡ የጥበብ ሰዎች፣ እረኞች እና መላእክት፡፡ ሦስቱም ብዙዎቹ ያደረጉትን ለማድረግ የመጡ አልነበሩም፡፡ ትክለኛውን ነገር ለማድረግ እንጂ፡፡ ሦስቱም ዘመን የወለደውን ጊዜ የወደደውን አልተከተሉም፡፡ የሚጠቅመውን ነገር እንጂ፡፡ ታሪክ እንደሚያስተምረን ግን የእነዚህ የሦስቱ እውነት በጊዜው ተገልጧል፡፡ ዓለምም በየዓመቱ የክርስቶስን ልደት ሲያከብር እነዚህን ሦስቱን ሰላማውያን ያስታውሳል፡፡

ለሰላም ስትሉ ዋጋ የምትከፍሉ፣ የምትዋረዱና የምትቃለሉ ሁሉ ከሦስቱ ሰላማውያን መማር አለባችሁ፡፡ የጠላት መሣሪያዎች የሆኑት ሄሮድሳውያን ቢገድሉም፤ የቤተልሔም ሰዎች እምቢ ቢሉም፣ የተማሩ የተባሉት የአይሁድ ሊቃውንት ቢቀልዱም፣ ለሰላም ዋጋ መክፈል ያዋጣል፡፡ ቢያንስ ሰማያዊና ታሪካዊ ዋጋ ያስገኛል፡፡

ይሄንን በዓል ስናከብር ከሦስቱ ሰላማውያን ጋር ሆነን ሰላምና ዕርቅ በሀገራችን እንዲሰፍን የበኩላችንን በማድረግ እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡ እርስ በርስ ከመሸናነፍ ስለሰላም ሁላችንም ብንሸነፍ ሁላችንንም አሸናፊ ያደርገናል፡፡ መንግሥት ለሰላማዊ መንገዶች ቅድሚያ ይሰጣል፡፡ ለሰላም ከሚሠሩት ጋር ሁሉ አብሮ ይሠራል፡፡ ሰላማውያን ለሚከፍሉት መሥዋዕትነት ክብርና ዋጋ ይሰጣል፡፡
በድጋሜ መልካም በዓል ይሁን፡፡

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ታህሳስ 28፣ 2017 ዓ.ም
#(ኤፍ ኤም ሲ)

በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ማተኮር አለብን  - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ሆሳዕና፣ታህሳስ 28/2017 )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ...
06/01/2025

በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ማተኮር አለብን - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው

(ሆሳዕና፣ታህሳስ 28/2017 )የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻዉ ጣሰዉ የ2017 ዓም የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል

ርዕሰ መስተዳድሩ በመልካም ምኞት መልዕክታቸው እንደገለጹት በሁሉም መስክ በሚከናወኑ ስራዎች የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ለማድረግ መሆን አለበት ብለዋል።

የተያዘው በጀት አመት በሁሉም ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።

በክልሉ በቂ ዝናብ የተገኘበት፣አዝመራው ለውጤት የበቃበት፣ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት በማምራት ትምህርታቸውን የተከታተሉበት፣የአካባቢን ሰላም ለማረጋገጥ በርካታ ስራ መስራት የተቻለበት ዓመት መሆኑን ነው ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው የጠቀሱት።

የክልሉ እና የሀገራችን ሰላም በላቀ ሁኔታ የሚረጋገጥበት ፣መሪዎቻችን ተጠናክረው ህዝብ የሚያገለግሉበት፣ህዝቦች በልማት ስራ ላይ የሚሳተፉበት፣ተማሪዎች ውጤት የሚያስመዘግቡበት፣አርሶ አደሮች ለበለጠ ስራ የሚዘጋጁበት፣የመንግስት ሰራተኞች የህዝብ አገልጋይነት መንፈሳቸው የሚጨምርበት ጊዜ እንዲሆንም ርዕሰ መስተዳድሩ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በጸጥታ ዘርፍ ለተሰማሩ አካላት፣ለመምህራን፣ለአርሶ አደሮች፣ለእናቶች፣ለህጻናት ለወጣቶች፣ በአጠቃላይ ለመላው ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት ቀን በዓል ገና በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ብለዋል።

የሰላም፣የፍቅር፣የአንድነት እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆን ርዕሰ መስተዳድሩ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251465551908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya zone Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hadiya zone Government Communication Affairs Department:

Videos

Share