Hadiya zone Government Communication

Hadiya zone Government Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hadiya zone Government Communication, Hossana.

This is the offical facebook home page of Hadiya Zone Communication

‹ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግሥትንና ሕዝብን ተጠቃሚ በማድረግ አንድ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማኀበረሰብን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ነው።

በሀዲያ ዞን የወጣቶችን ሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ትኩረት  ተሰጥቶ እየተሠራ ነው።በዞኑ የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ (YNSD) Youth Network for Sus...
13/12/2025

በሀዲያ ዞን የወጣቶችን ሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው።

በዞኑ የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ (YNSD) Youth Network for Sustainable Development የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ አካሂዷል።

ሆሳዕና፣ታህሳስ 04/2018 ዓ.ም(ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን )

በሀዲያ ዞን ከሚገኙ መዋቅሮች በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር፣በሶሮ ፣ በሌሞ እና በሻሾጎ ወረዳዎች የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ (YNSD) Youth Network for Sustainable Developmet የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።

ድርጅቱም ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ፍቅር በሕይወት ከተሰኙ ማህበራዊ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በወጣቶች አመለካከት፣ ሥነምግባርና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ የምክክርና የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል።

በምክክር መድረኩም የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳደርን ወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሀዲያ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ የዕለቱ ክብር እንግዳ አቶ ታገሠ ዶባሞ በዚህ ወቅት እንደገለፁት ይህ (YNSD) Youth Network for Sustainable Developmet የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ፍቅር በሕይወት ከተሰኘው ማህበራዊ ድርጅት ጋር በመተባበር በዞኑ ከሚገኙ መዋቅሮች በሶስት ወረዳና ሆሳዕና ከተማ አስተዳደር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መቆየቱን አንስተዋል።

ድርጅቱ በወጣቶች መሪነት ፣ በሥራ ፈጠራ እና በአመለካከት ዙሪያ ለሴቶች ለወጣቶች እና ተጋላጭ በሆኑ አካላት ላይ አፅንኦት ሰጥቶ እየሰራ መቆየቱንም ገልጸዋል።

በዚህም ወጣቶቹ በማህበረሰብ ውስጥ ገብተው የአረጋውያን ቤት ከማደስና ድልድይና መንገድ ጥገናን ጨምሮ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን መከናቸውን አብራርተዋል ።

አቶ ታገሠ አክላውም ድርጅቱ በይበልጥ ሴቶችን(70%)፣ተጋላጭ ማህበረሰብ ክፍሎች/ የአካል ጉዳተኞች(10%) እና ወጣቶችን(20%) በድምሩ ለአንድ ሺህ 500 ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ አጽንኦት ሰጥቶ የሚሠራ ድርጅት መሆኑን አንስተው
ተግባሩም ይበልጥ ውጤታማ መሆን እንዲችል ዞኑ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

የሀዲያ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ምክትል ኃላፊ ሞርካ ሞግሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመራ ከመጣው አዳጊ የህዝብ ፍላጎቶች አንፃር መንግስት ብቻውን ማሟላት አዳጋች እንደሆነ አንስተው፣
መንግስታዊ ያልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች በመንግስት ያልተሸፈኑ የልማት ፍላጎቶችን በማሟላት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያላቸው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በዚህም (YNSD) Youth Network for Sustainable Development የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ፍቅር በሕይወት ከተሰኙ ማህበራዊ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በዞኑ አራት መዋቅሮች በወጣቶች ዙሪያ እየሠራ ያለው ጅምር ሥራ አበረታች መሆኑን አመላክተዋል።

በተሠራው ሥራም ውጤቶች መመዝገባቸውን የጠቆሙት ኃላፊው ድርጅቱ ያመቻቸውን የብድር አማራጮች በመጠቀም ወጣቶች ቀጣይነት ያለውን የሕይወት ለውጥ ለማምጣት በሚደረገው ርብርብ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የሥራ ዕድል ፈጠራ ተቋማት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል ።

የCommunity Service As a Pathway to work (CSPW) የግብረ ሰናይ ድርጂት ሶዶ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ኢያሱ ስዩም ለተሳተፊዎቹ ባደረጉት ገለፃ፣ፕሮጀክቱ የሶዶ ክላስተርን ማዕከል አድርጎ በደቡብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወጣቶች ዙሪያ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መቆየታቸውን አስገንዝበዋል።

በሀዲያ ዞንም ከሚገኙ መዋቅሮች ሆሳዕና ከተማ፣ ሌሞ ወረዳ፣ ሻሾጎ ወረዳ እንዲሁም የሶሮ ወረዳን ጨምሮ ዘርፈብዙ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል ።

አቶ ኢያሱ ስዩም አክላውም በባለፉት የሥራ ወቅቶች በሶስቱ ወረዳዎችና በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር በወጣቶች መሪነት ሚና ፣ በሥራ ፈጠራ እና በአመለካከት ዙሪያ ሰፊ ሥራዎች ተሰርተዋል።

ከተሳታፊዎቹ መካከል የሀዲያ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ዓለምፀሐይ ተሰማ እና የሻሾጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግርማ ሎቤ በየበኩላቸው በሰጡት አስተያየት ፣ድርጅቱ በዞኑ የጀመራቸው ሥራዎች ቀድሞውኑ በሰው ተኮር መንግስታችን ትኩረት የተሰጠባቸው ናቸው በማለት
ሁሉንም ወጣት በማሳተፍ ሥራውን ውጤተማ ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በመጨረሻም የምክክር መድረኩ በሀዲያ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተምሬ ኤርሚያስ ቀጣይ የሥራ መመሪያና ማጠቃለያ ሀሳብ ተሰጥቶ ተጠናቋል።

በንጉሤ ዶሌቦ

ሆሳዕና ከተማ የኢትዮጵያ ማንሰራራት አንዷ ማሳያ ናት-  ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ (ሆሳዕና፣ ታህሳስ 3/2018)፣ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ህዝባዊ የውይይ...
13/12/2025

ሆሳዕና ከተማ የኢትዮጵያ ማንሰራራት አንዷ ማሳያ ናት- ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ

(ሆሳዕና፣ ታህሳስ 3/2018)፣ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

የኤፌዴሪ ከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለፁት ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በወራት ውስጥ ግንብቶ በማጠናቀቅ ምሳሌ የሆነ ክልል ነው።

ክልሉ በልማትም ሆነ በሰላም ረገድ ለሌላ አካባቢ ተሞክሮ የሚሆኑ ተግባራትን ማከናወን የቻለ ክልል መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በሆሳዕና ከተማ የተሰሩ የልማት ስራዎች እጅግ የሚያስደምሙ መሆናቸውን ሚኒስትሯ ተናግረው፣ ከተማዋ የኢትዮጵያ ማንሰራራት አንዷ ማሳያ ናት ሲሉም ገልፀዋታል።

በከተማዋ በአጭር ጊዜ የተከናወኑ የኮሪደር ልማትና የትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ስራዎች አመራሩ ከህዝብ ጋር ያለውን ቅንጅት የሚያሳይ ነው ብለዋል።

የተጀመሩ የልማትና ሰላምን የማፅናት ተግባራትን አመራሩ ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ማስቀጠል ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወ/ሮ እናትአለም መለሰ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ለውጥ በተቀናጀና በተባበረ መንፈስ መስራትን ይፈልጋል።

ለውጥን ለማስቀጠል ህዝብን በማሳተፍ መስራት ይገባል ያሉት ሚኒስትሯ፣ ወጣቱን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማብቃት ተወዳዳሪና ብቁ ማድረግ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ህዝቡ ለልማት ያለውን ቁርጠኝነት በሆሳዕና ከተማ በተከናወኑ ተግባራት ማሳየት ችሏልም ብለዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ፣ የከተማና ኢንዱስትሪ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል፣ የህዝቡ የልማት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በሆሳዕና ከተማ የተሰሩ መሠረተ ልማቶችን ህዝቡ ማድነቁን አንስተው፣ የመሰረተ ልማቶቹን ህብረተሰቡ በባለቤትነት በአግባቡ መጠቀም ይኖርበታል ሲሉም አሳስበዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ ከከተማ ነዋሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት፣ የመሠረተ ልማት በተለይም የንፁህ መጠጥ ውሃ እና የመብራት ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ፍላጎትን ለመሟላትም በሚቀርቡ አማራጮች ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑንም አመላክተዋል።

የወጣቱን የልማት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ህገ ወጥ ስደትን በአካባቢው ለማስቀረት በመንግሥት የተጀመሩ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ሲሉም የውይይቱ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል።

በከተማው የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ከመንግሥት ጎን በመሆን እንደሚያስቀጥሉም ተናግረዋል።
#የክልሉ ኮሙኒኬሽን

ለህብረተሰቡ ገላጭ የሆነ የተቋማት መረጃ ተደራሽ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እየተከናወነ እንደሚገኝ ተጠቆመ።የሀዲያ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ከቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤቶች...
13/12/2025

ለህብረተሰቡ ገላጭ የሆነ የተቋማት መረጃ ተደራሽ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እየተከናወነ እንደሚገኝ ተጠቆመ።

የሀዲያ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ከቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤቶች ጋር በመተባበር የዞኑን ተቋማት ተልዕኮ ጠቋሚ የዌብሳይት ልማት ግምገማ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄዳል።

።።።።።።።።።።።።። 04/04/2018 ።።።።።።።።።።።።

በግምገማው ወቅት መምሪያው የዞን መምሪያዎችን አሰራር በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

የሀዲያ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሪት ገነት ሙሉጌታ በግምገማው ወቅት እንዳሉት መምሪያው ከተሰጠው ተልዕኮዎች መካከል ለተለያዩ ተቋማት ሶፍትዌሮችንና ዌብ-ሳይቶችን አልምቶ በመስጠት አሰራሮቻቸውን ማዘመን እንደሆነ ተናግረዋል።

መምሪያው በዛሬው ግምገማ በዞኑ ለሚገኙ ሶስት የተለያዩ የመንግስት ተቋማትን አሰራር ገላጭ የሆነ ዌብሳይት በማልማትና ግምገማ በማድረግ አመርቂ አፈፃፀም መመዝገቡን ኃላፊዋ ጠቁመዋል።

የተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ለህብረተሰቡ ገላጭ፣ ፈጣንና ጥራት ያለው እንዲሆን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ያሉት ኃላፊዋ ለዚህም ስራ ግብዓት እንዲሆን መምሪያዎች ለተቋማችን አጭርና ገላጭ የሆነ መረጃ በመስጠት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

በዘርፉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤት የሆኑና በተለያዩ የስራ ዓይነቶች ተሰማርተው የሚገኙ ግለሰቦች በተለይም ወጣቱ ከመምሪያው ጋር ቅርበት መፍጠር ይገባቸዋል ያሉት ኃላፊዋ ለዚህ ተቋማቸው በሩን ከፍቶ አብሮ ለመስራ ዝግጁ መሆኑን አውስተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትልና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከበደ ሻሜቦ በበኩላቸው ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስን በመገንባት፤በቴክኖሎጂ የተደገፈ ወጪ ቆጣቢና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት መሰል የቴክኖሎጂ ውጤቶች ሚናቸው የጎላ ነው ብለዋል።

በዚህም ረገድ በዛሬው ዕለት ለምተው የተገመገሙት የዌብሳይት የልማት ስራዎች አበራታች እና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ያስታወሱት አቶ ከበደ ለሌሎች አከባቢዎችም በምርጥ ተሞክሮነት ሊቀመር እንደሚችል ጠቁመዋል።

ምክትል ኃላፊው አያይዘውም በዘርፉ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤት ለሆኑና ክህሎቱ ላላቸው አካላት አስፈላጊውን ልዩ ድጋፍ በማድረግ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ቢሮው በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በሆሳዕና ከተማ የእዘዙኝ ዴሊቨሪ ድርጅት ባለቤትና ስራ አስኪያጅ እንዲሁም የፈጠራው ባለቤት የሆነው ወጣት ሳሙኤል ተሻለ የቴክኖሎጂ ውጤቱ ከዞኑ ሳይንስና ቴክኖሎጂ መምሪያ ጋር በመተባበር ተዘጋጅቶ በዛሬው ዕለት ለግምገማ መቅረቡን ጠቁመው፤

ስራውን በተመለከተ የተሰጡ አዎንታዊ ግብረ መልሶችን በመቀበል በቀጣይ ቀናት ለሚመለከተው አካል እንደሚያስረክቡ ገልፀዋል።

በፍላጎት ለማ

በሆሳዕና ከተማ ህዝባዊ ውይይት እንደቀጠለ ነውሆሳዕና 04/04/2018 (የሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን )"የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፈቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ነው ውይይት እየተካሄደ ያለ...
13/12/2025

በሆሳዕና ከተማ ህዝባዊ ውይይት እንደቀጠለ ነው

ሆሳዕና 04/04/2018 (የሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን )

"የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፈቶች" በሚል መሪ ሀሳብ ነው ውይይት እየተካሄደ ያለው።

የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ በዚህ ወቅት የህዝብ ውይይቱ 20ኛውን የኢትዮጲያ ብሔር ብሔረሰቦች በዓል ማግስት የሚደረግ በመሆኑ ለየት ያደርገዋል ብለዋል።

መንግስት ለከተማ ልማት ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው በሆሳዕና ከተማም በተሰሩ የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉንም አንስተዋል።

በውይይቱም በከተማው ከህዝብ የሚነሱ ችግሮች በመፍታት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰዋው።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በበኩላቸው የጉባ ብስራቶችን የመንግስት የመፈፀም አቅም የሚያሳዩ ድሎች ተመዝግበዋል ብለዋል

የሆሳዕና ከተማ በተሰራው የልማት ሥራዎች በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አሕመድ አድናቆት መቻሩንም አንስተዋል።

ለከተማው ልማት መቀላጠፍ አስተዋፅኦ ላበረከተ የመንግስት አካላት ፣ባለሀብቶች እና ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል ስል የሀድያ ቴሌቪዥን ዘግቧል ።

በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ (YNSD) Youth Network for Sustainable Development የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት በሆሳዕና ...
13/12/2025

በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ (YNSD) Youth Network for Sustainable Development የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት በሆሳዕና ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄ ነው።

ሆሳዕና፣ታህሳስ 04/2018 ዓ.ም(ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን )

በሀዲያ ዞን በሶስት ወረዳዎችና በሆሣዕና ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ (YNSD) Youth Network for Sustainable Developmet የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት በሆሳዕና ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄ ይገኛል።

ድርጅቱ ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እና ፍቅር በሕይወት ማህበራዊ ድርጅት ጋር በመተባበር በዜጎች ሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በወጣቶች ክህሎት ማሳደጊያ ዘዴዎችና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ እስካሁን በተሠሩ ሥራዎች የልምድ ልውውጥና የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።

በምክክርና የልምድ ልውውጥ መድረኩም የሀዲያ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊና የዕለቱ ክብር እንግዳ አቶ ታገሠ ዶባሞ፣የሀዲያ ዞን የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ምክትል ኃላፊ ሞርካ ሞግሶ(ዶ/ር)፣የሀዲያ ዞን ጉዳዩ የሚመለከታቸው መምሪያ ኃላፊዎች፣በፕሮጀክቱ የታቀፉ ወረዳዎች ሻሾጎ፣ሌሞ፣ሶሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና አደረጃጀቶች ፣የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣የባህል ሽማግሎዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በንጉሤ ዶሌቦ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ የህዝብ የውይይት መድረክ  እየተካሄደ ነው። (ሆሳዕና፣ ታህሳስ 3/2018)፣ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳ...
13/12/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ የህዝብ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

(ሆሳዕና፣ ታህሳስ 3/2018)፣ "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ በሆሳዕና ከተማ የህዝብ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወ/ሮ እናትአለም መለሰ መድረኩን ይመራሉ።

በውይይት መድረኩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማና ኢንዱስትሪ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል፣ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።

በመድረኩ ከሆሳዕና ከተማ ከሁሉም ማህበራዊ መሠረቶች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ይገኛል።
የክልሉ ኮሙኒኬሽን እንደዘገበው

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የፌዴራል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወ/ሮ እናትአለም መለሰ በሆሳዕና ከተማ የልማት ስራዎች ምልከታ አደረጉ(ሆሳዕና፣ ታህ...
12/12/2025

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የፌዴራል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወ/ሮ እናትአለም መለሰ በሆሳዕና ከተማ የልማት ስራዎች ምልከታ አደረጉ

(ሆሳዕና፣ ታህሳስ 3/2018)፣ ሚኒስትሮቹ በሆሳዕና ከተማ የአቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስቴዲየም፣ አዲሱን የርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት፣ ቤተ መንግስትና የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲሁም የሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ምልከታ አድርገዋል።

ሚኒስትሮቹ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማና ኢንዱስትሪ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል እና የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በተገኙበት ነው የመስክ ምልከታውን ያደረጉት።

12/12/2025

ከእንግዶች አንደበት..

በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ የታቀደውን 60 በመቶው በተያዘው ታህሳስ ወር ለማሳካት በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ (ሆሳዕና፣ታህሳስ 3/2018 )ቢሮው...
12/12/2025

በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ የታቀደውን 60 በመቶው በተያዘው ታህሳስ ወር ለማሳካት በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ

(ሆሳዕና፣ታህሳስ 3/2018 )ቢሮው ከወቅታዊ የገቢ አሰባሰብ ጋር ተያይዞ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቀመሪያ ረሻድ ከወቅታዊ የገቢ አሰባሰብ ጋር ተያይዞ በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት በክልሉ በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ የታቀደውን 23 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በሁሉም የገቢ አማራጮች ላይ በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል ።

በተለይም ክልሉ አሁን ላይ እያሳየ ያለውን ፈጣን የልማት እድገት ቀጣይነቱን ለማረጋገጥና አዳጊ የልማት ፍላጎቶችን ለማሟላት ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ሀብት በሚጠበቀው ፍጥነትና ቅልጥፍና ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አለመሆኑን ነው ኃላፊዋ በመግለጫቸው ያብራሩት።

በክልሉ እስከ ታህሳስ ወር መጨረሻ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ 60 በመቶ ገቢ ለመሰብሰብ እንዲቻል በተቋሙ ልዩ ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ስራ መገባቱን አመላክተዋል ።

በየደረጃው የገቢ አማራጮችን ከተለምዷዊ አሰራሮች በማላቀቅ ዘመናዊና ተዓማኒነት ያለው ሁሉን አቀፍ አሰራሮችን ለመዘርጋት በቢሮ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በቀሪ ጊዜያቶች ያልተሰበሰቡ የገቢ አማራጮችን በመለየት ሁሉም በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ሰራተኞች በቅንጂት በመስራት የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት መትጋት እንደሚጠበቅ ያመላከቱት ወ/ሮ ቀመሪያ የገቢ ስራ እንቅፋት የሆኑ ብልሹ አሰራሮችን ማረምና ማስተካከል ተገቢ ነው ሲሉም ገልፀዋል ።

በመደበኛ የገቢ ስራዎች በተለይም የደረሰኝ ክትትል፣የገጠር መሬት መጠቀሚያና የእርሻ ስራ ገቢ ግብር የኢንቨስትመንት መሬት ኪራይና የማዕድን ገቢ ትኩረት መስጠት ፣ የሊዝ ኪራይና የዴስክ ኦዲት እንዲሁም ሌሎችም የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የገቢ አማራጮቾን በመጠቀም በሙሉ አቅም ገቢ መሰብሰብ እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

በገቢ ስራ 40 በመቶውን ያህል ማሳካት የሚቻለው ከገቢ ደረሰኝ ጋር ተያይዞ ያሉ ስራዎች ናቸው ያሉት የቢሮ ኃላፊዋ በክልሉ የተጀመሩ ጥብቅ የቁጥጥር ስራዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል ።

እንደ ወ/ሮ ቀመሪያ ገለፃ ህብረተሰቡም ደረሰኝ ጠይቆ የመቀበል ባህልና ልምዱን ሊያጎለብት እንደሚገባና የንግዱ ማህበረሰብም የሚጠበቅበትን ተግባር በኃላፊነት ሊወጣ ይገባል ሲሉም ማሳሰባቸውን ከክልሉ ገቢዎች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ነው​​በሀዲያ ዞን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የሀዲያ ዞን መልካም አስተዳደርና የአካባቢያዊ ...
12/12/2025

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ነው

​በሀዲያ ዞን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የሀዲያ ዞን መልካም አስተዳደርና የአካባቢያዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የገለፀ ሲሆን

ከሚቀርቡት አቤቱታዎች ውስጥ አብዛኞቹ መሬት ነክና ተያያዠ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ እንደሆነም ተጠቁሟል።

ሆሳዕና፣ ታህሳስ 03/2018 (የሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)።።

​ የሀዲያ ዞን መልካም አስተዳደርና የአካባቢያዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተሾመ ኤርቲሮ እንደገለፁት በዞኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መፍቻ ዘዴዎች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት ተፈጥሮ ወደ ትግበራ መገባቱን ጠቁመው።

​በዚህም በዞኑ ሥር ከሚገኙ መዋቅሮች ያልተፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የአስተዳደር ችሎትና መሰል መድረኮችን በማመቻቸት፣ ከተገልጋዩ ማኅበረሰብ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በቂ ጊዜ ሰጥቶ በማድመጥ ምላሽ የመስጠት ሥራ ተሠርቷል ።

​አቶ ተሾመ አክለውም፣ በዞኑ እስከ አሁን ከቀረቡት ዘጠና ሦስት (93) አቤቱታዎች ውስጥ ዘጠና (90) የሚሆኑት ተፈትተው፣ ከዚህም ሰማንያ አንድ (81) ያህሉ እልባት አግኝተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ ሂደት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

​አብዛኞቹ አቤቱታዎች ከመሬትና ከመሬት ነክ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ እንደሆነ ያነሱት ኃላፊው፣ ይህም ከአካባቢ አካባቢ እንደሚለያይ ገልጸዋል። አቤቱታ ከሚበዛባቸው አካባቢዎች አመራሮችና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት በመሥራት እና ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ አመርቂ ውጤት መመዝገቡንና የተጠቃሚው ማኅበረሰብ እርካታ ከፍ ማለቱን አቶ ተሾመ አስረድተዋል።

​ይህንኑ ይበልጥ በማጠናከር የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተለይም በታችኛው መዋቅር የችግሮቹን ምንጭ የመለየትና የማክሰም ሥራ እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።

​በንጉሤ ዶሌቦ

የሀዲያ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ዜጎችን ከተረጂነት ተላቀው በራስ የመለወጥ አቅም እንዲኖራቸው ለማድረግ በትጋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።​ጽ/ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አ...
12/12/2025

የሀዲያ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ዜጎችን ከተረጂነት ተላቀው በራስ የመለወጥ አቅም እንዲኖራቸው ለማድረግ በትጋት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

​ጽ/ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም እና የ2018 በጀት ዓመት የንቅናቄ ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማ እንዲሁም የቀጣይ 6 ወራት ዕቅድ ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

​።።ሆሳዕና፣ታህሣሥ 03/2018 (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን ።።

​የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካና ርዕዮተ ዓለም ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ መሳይ ተስፋዬ፣ ተረጂነት አንገት የሚያስደፋ እና እኩልነትን የሚነፍግ በመሆኑ ከውስጣችን አውጥተን ማክሰም አለብን ብለዋል።

​ አንድ ዓመትን እንደ አምስት ዓመት በመቁጠር ተረጂነትን ለማስቀረት በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።

​ፎጮ የሀዲያ ህዝብ ምርጥ የመተጋገዝ ተሞክሮ መሆኑን ጠቅሰው፣ አርሶ አደሩ ይህን ባህል በማጎልበት የፎጮ የመሰብሰብና መጋዘን ላይ የማከማቸት ሥራ እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።

​አቶ መሳይ አክለውም፣ በተግባሩ የሪፖርት አቀራረብ ፍጥነት ከጥራት ጋር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸው፣ ምርጥ ተሞክሮዎችን መቀመር እና የድጋፍና ክትትል ሥራውን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተዋል።

​የሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሀብታሙ ታደሰ በበኩላቸው፣ ከዚህ በፊት በተሰራው ሥራ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ላይ ትልቅ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰዋል። ይሁን እንጂ፣ ካለው የመሬት ሀብት እና የሰው ኃይል አንጻር ብዙ የሚቀረው ሥራ እንዳለ አመልክተዋል።

​ሼድ ኔት ላይ የፍራፍሬ ልማትን በትኩረት መስራት እና ሶላር ፓምፕ ያለባቸው አካባቢዎች በመስኖ ስራ ሞዴል እንዲሆኑ ጠይቀዋል።

​በተጨማሪም ቅንጅታዊ ሥራ ላይ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበው፣ የሪፖርት አቀራረብ ከውሸት የጸዳ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።

​ቅድመ ማስጠንቀቂያን በተመለከተ ደግሞ፣ ምን እንደሚከሰት ስለማይታወቅ ቅድመ ዝግጅት የማድረግ ሥራ በትኩረት በመስራት ዞኑን ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

​የሀዲያ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለሙ አሕመድ የመግቢያ ሰነድ በማቅረብ፣ በ2017 እና በ2018 በ6 ወራት ውስጥ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠል ደካማ ጎኖችን ማረም እንደሚገባ ጠቁመዋል።

​አቶ አለሙ እንደገለጹት፣ ድንገት ለሚከሰቱ ችግሮች ፈጣን እና ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ከ2 በመቶ በላይ የሆነ 42 ሚሊዮን ብር የአስቸኳይ ጊዜ የመጠባበቂያ ፈንድ መሰብሰብ ያስፈልጋል ብለው።

​ለዚህም ከአርሶ አደር ከ12 እስከ 15 ኪሎ ግራም እህል እና 3 መቶ ብር መሰብሰብ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
​በዞኑ ያሉ 11 ሶላር ፓምፖች በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል፤ በአሁኑ ሰዓት በስራ ላይ ያሉት ውስን እንደሆኑም ጠቁመው፤

​የልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን በተመለከተ ደግሞ ከታህሣሥ 30/2018 ዓ.ም ጀምሮ እንደቆመ አንስተዋል።

​በመጨረሻም ተሳታፊዎች፣ ከተረጂነት ለመውጣት በዞኑ የታቀደውን ዕቅድ ለማሳካት በትኩረት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አንስተው ፤

​ከፎጮ አሰባሰብ ስርዓት ጋር ተያይዞ በ2017 የታዩ ጉድለቶችን በ2018 በማረም እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
​በመንግስት የለሙ ማሳዎች እንዳሉ ሁሉ ህብረተሰቡን በማስተባበር የሚሰሩ ስራዎችን ለመፈፀም አቋም ይዘው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

​በታከለ አጋፋሪ

በዞኑ በሚካሄደው የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበበሀዲያ ዞን ዕድሜያቸው 5 ዓመት እና ከዚያ በታች የሆኑ ከ 3 መቶ 64 ሺህ በላይ ሕፃናትን...
12/12/2025

በዞኑ በሚካሄደው የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ

በሀዲያ ዞን ዕድሜያቸው 5 ዓመት እና ከዚያ በታች የሆኑ ከ 3 መቶ 64 ሺህ በላይ ሕፃናትን ከፖሊዮ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል የተቀናጀ የክትባት ዘመቻ ተጀምሯል።

።።ሆሣዕና፣ታህሳስ 03/2018 (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)።።

​የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ ፖሊዮ የሕፃናትን አካል በተለይም የእጅና የእግር ጡንቻዎችን በማዳከም፣ ሽባነትን የሚያስከትልና አልፎ ተርፎም ለሞት የሚዳርግ ተላላፊ በሽታ መሆኑን ገልጸዋል።

​ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ፣ ይህ ለ4ኛ ዙር በዘመቻ የሚሰጠው የፖሊዮ ክትባት ሲሆን፣ ዘንድሮ ቤት ለቤት የሚሰጥ በመሆኑ ከዚህ በፊት ቢከተቡም ባይከተቡም እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ሁሉም ሕፃናት ክትባቱን ማግኘት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

​በዞኑ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻው ከታህሳስ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 4 ቀናት ቤት ለቤት በጤና ባለሙያዎች አማካይነት በአፍ የሚሰጥ ሲሆን፤ በዞኑ ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ከ 3 መቶ 64 ሺህ እና ከዚያ በላይ ሕፃናት ለመከተብ ታቅዷል።

​ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ ወላጆች ሕፃናትን የፖሊዮ ክትባት በማስከተብ ከልጅነት ልምሻ ለመከላከል ወላጆች ግዴታቸውን እንዲወጡ በብርቱ አሳስበዋል።

​የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ እናቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ሥርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሌጅሶ የበሽታውን አደገኛነት አጠናክረው ገልጸው ክትባቱን በመስጠት መከላከል እንደሚቻል አስገንዝበዋል።
ሁሉም ባለድርሻ አካላት እድሜው አምስት አመትና በታች የሆነ አንድም ሕፃን ሳይከተብ እንዳያልፍ በጋራ በመሥራት ዘመቻው በስኬት እንዲጠናቀቅ ሚናቸውን እንዲወጡ ዶ/ር ደሳለኝና አቶ ተስፋዬ መልዕክት አስተላልፈዋል።

​አክለውም በዘመቻው ወቅት ከፖሊዮ ክትባት ጎን ለጎን፣ ከንፈርና ላንቃ መሰንጠቅ ያለባቸው፣ እግራቸው ቆልማማ የሆኑ እና የምግብ እጥረት ያለባቸው ሕፃናት ልየታ እና ወደ አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች የመላክ ሥራ ጭምር እንደሚከናወን አቶ ተስፋዬ ገልጸዋል።

​በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የአንሌሞ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ብርሃኑ ዱኔ በበኩላቸው በወረዳው ተግባሩን የተሳካ ለማድረግ ወላጆች ሕፃናትን እንዲያስከትቡ የቅስቀሳ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

​በአንሌሞ ወረዳ የክትባት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው መንግሥት ጤናማ ዜጋን ለመፍጠር በጤናው ዘርፍ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያበረታቱ በመሆናቸው ለውጤታማነት የበኩላቸውን ሚና እንሚወጡ ገልፀው ሁሉም ሕፃናት እንዲከተቡ ጥረት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።


​በዘመቻ ማስጀመሪያው መርኃ ግብር ላይ ከክልል፣ ከዞንና ከአንሌሞ ወረዳ የተውጣጡ የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

​በጫኬቦ ኤርጫፎ

Address

Hossana

Telephone

+251465551908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya zone Government Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hadiya zone Government Communication:

Share