New adda

New adda New

በሀዲያ ዞን ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሀብት አሰባሰብ መርሃግብር እየተካሄደ ነው ጳጉሜ 3/2014 ዓ.ም (የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ/መምሪያ)በሀዲያ ዞን የሚገኙ የወረዳና የከተማ አስተ...
08/09/2022

በሀዲያ ዞን ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሀብት አሰባሰብ መርሃግብር እየተካሄደ ነው

ጳጉሜ 3/2014 ዓ.ም (የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ/መምሪያ)

በሀዲያ ዞን የሚገኙ የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ያሰባሰቡትን ድጋፍ ለዞኑ ሀብት ሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ እያበረከቱ ነው።

የወረዳና የከተማ አስተዳደሮቹ የእርድ ሰንጋ፣ የፍየልና የበግ ሙክቶችን ጨምሮ ሰንባች የምግብ ቁሳቁስ ነው ለዞኑ ሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ እያበረከቱ የሚገኙት።

ድጋፍም ከአርሶ አደሮች፣ ከአጀረጃጀቶች፣ ከሀይማኖትና የትምህርት ተቋማት ከንግዱ ማህበረሰብ የተሰበሰበ ነው ተብሏል።

በድጋፍ ርክብክቡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫ፣ የዞኑ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ጌታቸው ሌሊሾን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ የመንግሥት የስሬ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ።

የአካባቢውን የልማት ችግሮች ለመቅረፍ የአስተሳሰብና የአመለካከት አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዶ/ር ታደለ ቡረቃ ገለጹ። ይህም የተገለፀው "ማዳ  የልማትና...
29/08/2022

የአካባቢውን የልማት ችግሮች ለመቅረፍ የአስተሳሰብና የአመለካከት አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዶ/ር ታደለ ቡረቃ ገለጹ። ይህም የተገለፀው "ማዳ የልማትና እርዳታ ድርጅት" የፕሮጀክት ልማት ማስጀመሪያ ኮንፍረንስ በከምባታ ጠምባሮ ዞን በጠምባሮ ወረዳ ባካሄደበት ወቅት ነው። "ማዳ የልማትና እርዳታ ድርጅት" በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የጠምባሮ ተወላጆች የአካባቢውን የልማት ችግሮች በአካባቢው ልጅ ለመሸፈን በማለም የተቋቋመ ሀገር በቀል ግብረሰናይ ድርጅት ነው።
ድርጅቱ ከተመሠረተው ነሐሴ 2012 ዓ/ም ጀምሮ ለሙዱላ ከተማ ኮብል ስቶን ስራ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች ሀብት በማሰባሰብ የጀመረውን የልማት አጋርነት በማጠናከር በቅርቡ ደግሞ በወረዳው ቆላማ አካባቢዎች በተከሰተው ድርቅ የአስቸኳይ እርዳታ ምላሽ በመስጠት በህብረተሰቡ ዘንድ የወገን ደራሽነት አለኝታ የበለጠ ማስመስከር የቻለ የልማት ድርጅት ነው። ማዳ የልማትና እርዳታ ድርጅት የመጀመሪያ የሆነውን የፕሮጀክት ልማት ማስጀመሪያ ኮንፈረንስ ለህብረተሰቡ ባበሰረበት ወቅት የተገኙት የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ወ/ማሪያም አያሶ እንደገለጹት ድርጅቱ ማህበረሰቡ ስለልማት ያለው አመለካከትና ግንዛቤ እንዲሁም የህዝቡ የልማት ተሳትፎ ከፍ እንድል ማስተማር፣ ማነቃቃት እና ይህንኑን የሚደግፉ ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረግ ላይ ዓላማ ያደረገ ነው።የድርጅቱ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገ/ወልድ አሸንጎ በበኩላቸው የአካባቢውን ህብረተሰብ የልማት ተጠቃሚና ተሳታፊ ለማድረግ በልማት ማስጀመሪያው ኮንፈረንስ የድርጅቱ የመጀመሪያ ፕሮጀክት በሆነው በት/ት ልማት ዘርፍ መምህራን ለተማሪዎች ተገቢውን እውቀት እንዲያስጨብጡና በስነ-ምግባር ታንፀው ለሀገር እድገትና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም አመላክተዋል። በጠምባሮ ወረዳ በ2015 ዓ/ም በህብረተሰቡ ትብብር አንድ የልህቀት ት/ቤት በመክፈት በ12ኛ ሞዴል ክፍል ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የጠቆሙት የቦርድ ሰብሳቢው ለዚህ ስኬታማነት ድርጅቱ መምህራንን በማሰልጠን፤ የት/ት ግብዓቶችን በማሟላትና የኢንተርነት ማዕከላት በማቋቋም ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ታደለ ቡረቃ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የአካባቢውን የልማት ችግሮች በአካባቢው ማህበረሰብ ለመፍታት ድርጅቱ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።የተከናወኑ የልማት ተግባራት በአግባቡ እንዲጠበቁና እንዲንከባከቡ የሚያስችሉ የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲሰርጽ ድርጅቱ በቅንጅት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።በአካባቢው የት/ት ውጤታማነትን የበለጠ ለማጠናከር በት/ት ልማት ዘርፍ የተወጠነውን ለማሳካት ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም ዶ/ር ታደለ ገልፀዋል።የጠምባሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ታድዎስ ጆርጋ የጠምባሮ ምሁራን የአስተሳሰብ አንድነት ፈጥረውና ያላቸውን እውቀት ለህብረተሰብ ለውጥ በማሰብ ወደ ተግባር የቀየሩት ማዳ የልማትና እርዳታ ድርጅት ግቡን እንዲያሳካ የወረዳው መስተዳድር አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ከኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መካከል አቶ ዳዊት ጡሜቦ እና አቶ ደግነት አለምቦ ድርጅቱ በህብረተሰቡ ዘንድ የአስተሳሰብና የአመለካከት አንድነት በማስረጽ ለልማት በጋራ መቆምን ዓላማ ካደረገው ከዚሁ ድርጅት ጎን በመሆን ለተጀመረው የልማት ውጥን ስኬታማነት የሚያደርጉትን የገንዘበ፣ የጉልበትና የእውቀት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ እናቶች እና ህጻናት ጤናና ስርዓተ-ምግብ አገልግሎቶች የ2014 በጀት አመት አፈጻጸም ውይይት የመግባቢያ የውል ሰምምነት በመፈራረም ተጠናቀቀበመድረኩ የእናቶች ህፃናት...
21/08/2022

የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ እናቶች እና ህጻናት ጤናና ስርዓተ-ምግብ አገልግሎቶች የ2014 በጀት አመት አፈጻጸም ውይይት የመግባቢያ የውል ሰምምነት በመፈራረም ተጠናቀቀ

በመድረኩ የእናቶች ህፃናት እና ስርዓተ ምግብ የ2014 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም እንዲሁም የ2015 በጀት አመት ዕቅድ የቀረበ ሲሆን በዘርፉ የታዩ የአፈጻጸም ችግሮችና በቀጣይ ለህብረተሰቡ ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ጠቋሚ ሰነድ ቀርቦ በችግሮቹ እና በመፍትሄዎቻቸው ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበውን የውይይት ሰነድ መነሻ በማድረግ በሰጡት አስተያየት እንደገለጹት የማህበረሰቡን ፍትሀዊ የጤና ተጠቃሚነት እና የጤና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥተው መስራት ይገባል።

የ2014 በጀት አመት የተሻለ የፈጸሙበትና ህብረተሰቡን ተደራሽ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ጎልተው የወጡበትና በውስንነት የተነሱትን ደግሞ ሊሻሻሉ የሚችሉትን በመለየት በቀጣይ በጀት አመት ቀድሞ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዲቻል ለማድረግ የተደረገ ውይይት ነው ብለዋል።

የተሻለ አፈጻጸም የታየባቸው አካባቢዎች ላይ የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍ አመራሩ ባለቤት ሆኖ በመስራቱ የተሻለ ውጤት ማምጣት መቻሉን የገለጹት ተሳታፊዎቹ ሞዴል ቀበሌዎችንና ወረዳዎችን ለመፍጠር ማገዙን ገልጸዋል።

አቶ ሸምሱ ሀይረዲን የመምሪያ ኃላፊ በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራት የተሻለ አፈጻጸም የታየባቸው ሲሆኑ ዝቅተኛ አፈጻጸም ያሉባቸውን ወረዳዎች በመለየት ፍትሀዊ የጤና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች በቀጣይ ይሰራሉ ብለዋል።

በዘርፉ በጥንካሬ የተገለጹትን ተግባራት በማጎልበት ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየባቸውን ለይቶ በቀጣይ ማህበረሰቡን ከጤና ፍትሀዊ ተጠቃሚነት አንጻር ለማመጣጠን የሚያስችሉ የንቅናቄ ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል ሀላፊው።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በሚያደርጉት ውይይት ወረዳዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲለዩ በማድረግ እና የአፈጻጸም ደረጃቸውን ወደ ተመጣጠነ ደረጃ ላይ ለማምጣት የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመው ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን መዋቅሮች በመለየት በዛ ልክ ድጋፍ ለማድረግ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

አቶ ጁሃር አድማማ በመምሪያው የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአንኳር ጉዳዬች ላይ የባለፈው በጀት አመት በአራቱም ዋና ዋና ፕሮግራሞች የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም የተሻለ ቢሆንም ውስንነት ያለባቸውን ተግባራትን በቀጣይ በጀት አመት ትኩረት ሰጥተን የምንሰራቸው ይሆናል ሲሉ ገልፀዋ።

በ2015 የእናቶች ጤና አገልግሎት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ያሉት አቶ ሸምሱ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የቅድመ ወሊድና የድህረ ወሊድ አገልግሎት ፣የኤች አይ ቪ ኤድስ ህክምና፣ የማህጸን በር ካንሰር ምርመራና ህክምና በትኩረት ይሰራል።

የጨቅላ ህጻናት ህክምናን በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ክትባትን ጨምሮ በማሻሻል የሚሰራ ይሆናል ያሉት አቶ ሸምሱ በተለይ ከስርዓተ ምግብ ጋር ተያይዞ ዘርፈ ብዙ የስርዓተ ምግብ ተግባሪ ተቋማትን በማቀናጀት መቀንጨርን በ2030 ዜሮ ለማድረግ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑ ገልፀዋል።

በመድረኩ መጨረሻ የ2015 በጀት ዓመት በዋና ዋና ተግባራት ላይ የዞን ጤና መምሪያ የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት ከወረዳ እና ከተማ አስተዳደር የጤና ፅ/ቤቶች ጋር በተዘጋጀ ሰነድ ላይ በመግባባት የውል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

Source የሰልጤ ዞን ጤና መምሪያ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ስር የነበሩ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ተቀበሎ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወ...
18/08/2022

የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ስር የነበሩ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ተቀበሎ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወስኗል
***************
(ኢ ፕ ድ)
የፌዴሬሽን ምክር ቤት በዛሬው የአስቸኳይ ጉባኤ ስብሰባ ውሳኔ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ስር የነበሩ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ተቀብሎ ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወስኗል።

በጋራ አዲስ ክልል እንዲመሰርቱ የቀረበውን ሀሳብ ተቀብሎ የህዝበ ውሳኔ እንዲያካሂዱ የተወሰነላቸው የወላይታ ዞን፣ የጋሞ ዞን፣ የጎፋ ዞን፣ የደቡብ ኦሞ ዞን፣ የጌዴኦ ዞን፣ የኮንሶ ዞን፣ እንዲሁም የደራሼ ልዩ ወረዳ፣ የአማሮ ልዩ ወረዳ፣ የቡርጂ ልዩ ወረዳ፣ የአሌ ልዩ ወረዳ እና የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ናቸው።

ቀሪዎቹ የሀድያ ዞን፣ ሀላባ ዞን፣ ከንባታ ጠንባሮ ዞን፣ ጉራጌ ዞን፣ ስልጤ ዞንና የም ልዩ ወረዳ በነባሩ ክልል የሚቀጥሉ መሆኑም ታውቋል።

ነሃሴ 9/2014በደቡብ ክልል በህዝቡ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት እየተካሄደ ነውየደቡብ ክልል የፓርላማ ተወካዮች፣ የክልሉ አመራሮች፣የዞንና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ...
15/08/2022

ነሃሴ 9/2014

በደቡብ ክልል በህዝቡ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት እየተካሄደ ነው

የደቡብ ክልል የፓርላማ ተወካዮች፣ የክልሉ አመራሮች፣የዞንና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎችና አፈ ጉባኤዎች እንዲሁም የክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ከዚህ ቀደም በህዝብ ተነስተው በነበሩ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲሁም የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በሀዋሳ የጋራ ውይይት እያካሄዱ ነው።

መድረኩን የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሌ እና የርዕሰ መስተዳድሩ ተወካይና በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ኡስማን ሱሩር እየመሩት ሲሆን ከህብረተሰቡ በየዘርፉ ተነስተው ለነበሩ ጥያቄዎች የተሰጡ ተግባራዊ ምላሾችና የተቋማት እንቅስቃሴዎች ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

ተመሳሳይ የህዝብ ተመራጮች የጋራ የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ አስታውቀዋል ።

የቡታጅራ ከተማ፣ የመስቃን እና የምስራቅ መስቃን ወረዳዎች እና የቀቤናና ማረቆ ብሔረሰብ ምክር ቤቶች ከአጎራባች የዞን መስተዳድሮች ጋር በክላስተር በአንድ የጋራ ክልል ለመደራጀት የቀረበውን ...
13/08/2022

የቡታጅራ ከተማ፣ የመስቃን እና የምስራቅ መስቃን ወረዳዎች እና የቀቤናና ማረቆ ብሔረሰብ ምክር ቤቶች ከአጎራባች የዞን መስተዳድሮች ጋር በክላስተር በአንድ የጋራ ክልል ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በመደገፍ የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ያሳለፈውን "የክልል እንሆናለን" ውሳኔ ውድቅ አደረጉ።

የዞኑን ምክር ቤት ውሳኔም አገር ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ፣ የህዝቦችን የዘመናት አብሮነትና የልማት ተጠቃሚነትን የሚፃረር ሲሉ የየምክር ቤቶቹ አባላት ኮንነዋል።

የቡታጅራ ከተማ በ2014 ዓ.ም 4ኛ ዙር፣ የመስቃን ወረዳ በ2014 ዓ.ም 2ኛ ዙር፣ የምስራቅ መስቃን ወረዳ በ2014 ዓ.ም በ2ኛው ዙር፣ የማረቆ ብሔረሰብ ደግሞ በ2014 ዓ.ም 4ኛ ዙር አስቸኳይ የምክር ቤት ስብሰባቸውን ባደረጉበት ወቅት ነው የዞኑን ውሳኔ በሙሉ ድምጽ ውድቅ ያደረጉት።

የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰብና ህዝቦች ክልልን ኢትዮጵያ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት በማስገባት በሁለት ክልል በክላስተር ለማደራጀት የውሳኔ ሃሳብ መቅረቡ ይታወሳል።

የቀረበው ምክረ ሃሳብ ሁሉም የክልሉ ህዝብና መንግስት ኢትዮጵያ ያለባትን ጫና ከግምት በማስገባት ውሳኔውን ተቀብለው በየዞን ምክር ቤታቸው አጽድቀዋል።

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ግን ከአጎራባች የዞን መስተዳድሮች ጋር በክላስተር ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ምክረ ሃሳብ ውድቅ ማድረጉን መግለጹ ይታወሳል።

አጎራባች የዞን መስተዳድሮችን በክላስተር በክልል ለማደራጀት የቀረበው የውሳኔ ምክረ ሃሳብ ለኢትዮጵያና አካባቢው ማህረሰብ ወሳኝና ጠቃሚ ነው ያሉት የቡታጅራ ከተማ፣ የመስቃንና የምስራቅ መስቃን ወረዳዎች እንዲሁም የማረቆ ብሔረሰብ ምክር ቤቶች ከህዝብ ተወካዮች፣ ከየወረዳ አመራሮችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ምክክር በማካሄድ ከአጎራባች የዞን መስተዳድሮች ጋር በክላስተር ለመደራጀት በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ መስማማታቸውን አስታውቀዋል።

ምክር ቤቶቹ የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ውሳኔ የህዝቦችን የጋራ አንድነት፣ አብሮ የመኖር ፍላጎትና መሬት ላይ ያለውን ሀቅ የሚፃረር መሆኑን በመጥቀስ ውሳኔውን ተቃውመውታል።

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ባሳለፈው ውሳኔ ላይ የሁሉም የዞኑ አካባቢዎች ቅቡልነት እንዳለው ተደርጎ የተሰራጨው መረጃም ተቀባይነት የሌለውና መሰረተ ቢስ መሆኑ በምክር ቤቶቹ አባላት ተነስቷል።

መንግስት ያቀረበውን የውሳኔ ምክረ ሃሳብ በመደገፍም ከስልጤ፣ ከሀድያ፣ ከከንባታ፣ ሃላባና የም ህዝቦች ጋር በክላስተር በክልል ለመደራጀት መወሰናቸውን በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል።

መንግስት አጎራባች የዞን መስተዳድሮችን በአንድ የጋራ ክልል ለማደራጀት ያቀረበውን የውሳኔ ምክረ-ሃሳብ በመቀበል የምስራቅ ጉራጌ የዞን አደረጃጀት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ አጽንኦት በመስጠት በየምክር ቤቶቹ ውሳኔ ተላልፏል።

የማረቆ ብሔረሰብ ምክር ቤት አባላትም "የብሔረሰብ አስተዳደር ልዩ ወረዳ አደረጃጀት" ተፈቅዶ እራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳደሩበት ስርዓት እንዲፈጠርላቸው አፅንኦት ሰጥተዋል።

የቀቤና ብሔረሰብ ምክርቤትም በክላስተር የመደራጀት ውሳኔን በሙሉ ድምፅ በዛሬው ዕለት ማፅደቁን የወረደው ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

ከአጎራባች የዞን መስተዳድሮች ጋር በክላስተር በክልል ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ምክረ ሃሳብም ፍትሃዊ ተጠቃሚነትንና የዜጎችን አብሮነት የሚያስቀጥል እንደሆነ በምክር ቤት አባላት ተንጸባርቋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

ጠ/ሚ ዐቢይ ሀረር ገቡነሐሴ 7/2014  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀረር ከተማ ገብተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀረር ከተማ ሲገቡ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና ሌሎች ከፍተኛ ...
13/08/2022

ጠ/ሚ ዐቢይ ሀረር ገቡ

ነሐሴ 7/2014 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀረር ከተማ ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀረር ከተማ ሲገቡ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀረር ከተማ የተገኙት በሀረሪ ክልል በሚደረገው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር መዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ለመገኘት ነው።

ተስፋዬ ኃይሉ (ከሀረር)

ነሃሴ 7/2014የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ የ2014 ዓ.ም የዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ዓመታዊ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአርባምንጭ እየተካሄደ ነው:: በ 2014 ዓ...
13/08/2022

ነሃሴ 7/2014

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ የ2014 ዓ.ም የዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ዓመታዊ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ በአርባምንጭ እየተካሄደ ነው::

በ 2014 ዓም የስራ ዘመን ያጋጠሙ አለም አቀፍና አገር አቀፍ ችግሮችን በመቋቋም ስኬታማ ስራዎች ተከናውነዋል ተብሏል::

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ም/ኃላፊ እና የዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት በ2014 ዓ.ም አገር አቀፍና አለም አቀፍ ጫናዎችን በመቋቋምና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ኤች አይቪ ኤድስን የመከላከልና ምርመራን ለማዳረስ ስኬታማ ስራ ተሰርቷል::

ችግሩ በስፋት የሚታይባቸውን ቦታዎች በእድሜ ፣ በጾታ እንዲሁም በአካባቢ በመለየት ራስን በራስ መመርመርን ጨምሮ በግልም ሆነ በጋራ ለሚመጡ ተገልጋዮች ተደራሽ ማድረግ ተችሏል::

የኤች አይቪ ኤድስ ስርጭት ከቦታ ቦታ ይለያይ እንጂ ስርጭቱ መጨመሩን የገለፁት አቶ ሳሙኤል ይህንንም ለመቀነስ በተለይ ችግሩ ጎልቶ በሚታይባቸው አካባቢዎች ይበልጥ መስራት እንደሚጠበቅ ገልፀዋል ::

በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ከድጋፍ አንፃር የአመራር ቆራጥነት ማነስ ፣ የኪትና ሊሎች ግባአት እጥረትን ችግረ ማጋጠሙንም ገልፀዋል::

ከ15-19 ዕድሜ ክልል የሚገኙ ወጣቶችን በመከላክል ስራው ማካተት እንዲሁም በቫይረሱ የተያዙትን ወደ ህክምና እንዲገቡ የማድረግ ስራ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች በመሆናቸው በቀጣይ ኃላፊነት በመውሰድ እንዲሰሩ አቶ ሳሙኤል አሳስበዋል::

በአፈፃጸም ግምገማው መድረክ ላይ ከክልልና ዞን የተውጣጡ አመራሮችና አጋርድርጅቶች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ::

ወራቤ ዩንቨርስቲ  ለ3ኛ ዙር በተለያዩ የትምህርት መረሐ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ነው
13/08/2022

ወራቤ ዩንቨርስቲ ለ3ኛ ዙር በተለያዩ የትምህርት መረሐ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ነው

የሆሳዕና ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 9ኛ የሥራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ለ2015 ዓ.ም የከተማው አስተዳደር ዕቅድ ማስፈፀሚያ 750 ሚሊየን ብር  በጀት በማጽደቅ ተጠናቀቀ።የከተማው  የመን...
12/08/2022

የሆሳዕና ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 9ኛ የሥራ ዘመን 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ለ2015 ዓ.ም የከተማው አስተዳደር ዕቅድ ማስፈፀሚያ 750 ሚሊየን ብር በጀት በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነሐሴ 6/2014 ዓ.ም

የከተማው ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዓለሙ እንደገለጹት ምክር ቤቱ ያፀደቀው በጀት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ሲነፃፀር የ38.8% ብልጫ አለው ።

ምክር ቤቱ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ያካሄደው ጉባኤ ከምክር ቤቱ ፣ ከአስፈፃሚና ከዳኝነት አካሉ የቀረበለትን የክንውንና የዕቅድ ሪፖርቶች ተወያይቶ አጽድቋል።

የምክር ቤቱ ጉባኤ ከዚህም በተጨማሪ የአለም ባንክ ፕሮጀክት የዕቅድና የአፈፃፅም ሪፖርት ፣ በከተማው ተሻሽሎ የቀረበው የውሃ ታሪፍና የገቢ ማሻሸያ ሰነዶች ለይ ተወያይቶ አፅድቋል ።

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የሕዳሴ ግድብ ሦስተኛ ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ ከስፍራው አበሰሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዐባይ ስጦታችን ነው፣ ስጦታችንን መጠቀም የእኛ ኃላፊነት ነውም ብለዋል። ሦስቱ የ...
12/08/2022

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የሕዳሴ ግድብ ሦስተኛ ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ ከስፍራው አበሰሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ዐባይ ስጦታችን ነው፣ ስጦታችንን መጠቀም የእኛ ኃላፊነት ነውም ብለዋል። ሦስቱ የተፋሰስ ሀገራትም በጋራ ከዚህ ስጦታ ተጠቃሚ ናቸው በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የዐባይ ወንዛችን የሚገባውን አስቀርቶ የሚገባቸውን ይዞ መጓዙን ቀጥሏል በማለት የሁሉንም የተፋሰስ ሀገራት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ እንደምትሠራ አስታውሰዋል። ለመላው አፍሪካውያን የእንኳን ደስ አለን መልዕክትም አስተላልፈዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት  በሚል ርዕስ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። የከተማው መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነሀሴ 06/2014 ዓ.ም በስልጠናዉ ከስድስቱ ቀበሌያ...
12/08/2022

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በሚል ርዕስ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

የከተማው መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነሀሴ 06/2014 ዓ.ም

በስልጠናዉ ከስድስቱ ቀበሌያት ከተለያዩ የወጣት አደረጃጀቶች የተዉጣጡ ከ80 በላይ የሆኑ በወጣቶች ስብዕና ማዕከል አዳራሽ እየተሳተፉ ይገኛል ።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሰሀ ታደሰ ባስተላለፉት መልዕክት ስልጠናዉ
ኀብቁ ፣ ተወዳዳሪና ተፅኖ ፈጣሪ ሆነዉ ሀገርና እራሳቸዉን እንዲጠቅሙና ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በማዋሀድ አዳዲስ ልምዶችን ከመፍጠርና ከማነቃቃት አንፃር ስልጠናዉ ያለዉ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በንቃት እንዲከታተሉ አሳበዋል።

ሰልጣኝ ወጣቶች በበኩላቸዉ ባገኙት ግንዛቤ ራሳቸዉን ብቁ ተወዳዳሪ ለማድረግ እንደሚረዳቸዉና በተለይ ስለ መሪነት ያገኙት ግንዛቤ ወደፊት አርቀን እንድናይ የሚደረገን ስለጠና ስሉ ነው ተናግረዋል።

እንኳን ደስ አለን!!የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ እንኳን ደስ አለን።- አቶ መለሰ ዓለሙበብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ...
11/08/2022

እንኳን ደስ አለን!!
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ እንኳን ደስ አለን።

- አቶ መለሰ ዓለሙ
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

ነሐሴ 4/2014 የሀዲያ ዞን አንዳንድ  ነዋሪዎች የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛ ተርባይን ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ የሀዲያ ዞን አንዳንድ ነዋሪዎች ታላቁ የኢት...
11/08/2022

ነሐሴ 4/2014

የሀዲያ ዞን አንዳንድ ነዋሪዎች የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛ ተርባይን ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ

የሀዲያ ዞን አንዳንድ ነዋሪዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ 2ኛው ተርባይን ስራ በመጀመሩ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

የጥንት አባቶቻችን ዓባይን ሊገነቡ እየሞከሩ ሳይሳካ አልፈዋል። በታሪክ ውስጥ ማለፍ ዕድል ነው፣ ታሪክ ሠርቶ ማለፍ ግን ዕድልም ድልም ነው፡፡ ይሄ ትውልድ በዓባይ ግድብ ባለ ዕድልም ባለ ድልም ነው ያሉትን የጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዓቢይ አህመድ አገላለጽ ነዋሪዎች አድንቀዋል።

አቶ ሰለሞን አበበና መቶ አለቃ ተደለ ባፌ በሀዲያ ዞን የሆሳዕ ከተማው ነዋሪ ሲሆኑ ዓባይ ኢትዮጵያን በብርሃኑ ሊያደምቃት ኃይል ሆኖ ሊያባራ ቢቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን ለማገልገል ከጫፍ በመድረሱ ታላቅ ሀገራዊ ኩራት እንደተሰማቸው ይናገራሉ።

ሌላኛው የከተማው ነዋሪዎች ከሆኑት መካከል ወ/ሮ ዓልመ መሃመድ እና ወጣት ምትኩ ተሾመ ሕዝባችን ልማት ናፋቂ እንጂ ጥላቻና ግጭት እንደማይፈልጉ ዓባይ ማሳያ ነው ይላሉ።

ዓባይ እንዳይገነባ የውጭና የውስጥ ጫናውን በመቋቋም ለዛሬው ስኬት በመድረሳችን ልባው ደስታ ተሰምቶናል ነው ያሉት የከተማ ነዋሪዎች።

በቀጣይም በኢትዮጵያዊን ወኔ ሙሉ በሙሉ ግንባታውን አጠናቅቀን የልባችን እንደሚሞላ አንጠራጠርም ያሉት ነዋሪዎቹ የግድቡ ግንባታ እስከ መጨረሻ ለማድረስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል ።

በርካታ ፈተናዎችን ተቋቅመው ለዛሬ ስኬት እንድንበቃ ያስቻሉትን ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዓቢይ አህመድ ጨምሮ ሁሌም ሳይሰለቹ ብርድና ሀሩር ሳይበግራቸው በግንባታው ለተሰተፉ የግድቡ ሰራተኞችና ለጠበቁት የሠራዊት አባለት ምስገና አቅርበዋል።

ኢትዮጵያውያን የታለቁ የሕዳሴ ግድብ ከንድፍ አልፎ፣ ግንባታው ተገባድዶ፣ ግዙፍ ውኃ በጉያው ይዞ ኃይል ማመንጨት እንዳስቻልን ሁሉ ይህንንም ሀገራዊ ስሜትና በአንድነት ወደ ድል በመቀየር በቀጣይ በሁሉም መስክ ድልና ስኬት ለማስመዝገብ በተባበረ ክንድ ልንሰራ ይገባል በማለት ነዋሪዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዘገባው የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ/መምሪያ ነው።

ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን በልማት ስራዎች ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርግ ከሆነ የማይቻል የልማት ስራ እንደማይኖር በሆሳዕና ከተማ የሴች ዱና ቀበሌ አስተዳደር ገለጸ።በአሁኑ ወቅት የቀ...
07/08/2022

ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን በልማት ስራዎች ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርግ ከሆነ የማይቻል የልማት ስራ እንደማይኖር በሆሳዕና ከተማ የሴች ዱና ቀበሌ አስተዳደር ገለጸ።

በአሁኑ ወቅት የቀበሌው ነዋሪዎች የሚጠበቅባቸውን የመንግስትን ግብር በወቅቱ በመክፈል እየተወጡ ያለው ባለቤትነት የታቀዱ የልማት ስራዎችን በታቀደለት ግዜ ለማከናወን እንደሚያግዝም የቀበሌው ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገልጿል።

በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው ግብር የማስከፈል ፕሮግራምን በማስመልከት ንግግር ያደረጉት የሴች ዱና ቀበሌ አስተዳደር አቶ ታምራት ካሣ መንግስት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን የነቃ የልማት ተሳትፎ የሚያደርግ ከሆነ የማይመለስ እና የማይቻል የልማት ጥያቄና ስራ እንደማይኖር ተናግራዋል።የቀበሌው ነዋሪዎችም በልማት ስራዎች ላይ እያደረጉ ያለው ተሳትፎ የሚበረታታ ነው በማለት አመስግነዋል።በሌሎች በልማት ስራዎች ከሚያደርጉ ተሳትፎ ባሻገር በአሁኑ ወቅትም ግብርን የመክፈል ጠቀሜታ ተረድተው በወቅቱ በተነሳሽነት እየከፈሉ መሆናቸው የዚህ የልማት ተሳታፊነት ማሳያ መሆኑንም አቶ ታምራት አብራርተዋል።በመሆኑም የነዋሪዎችን የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ የተጀመሩ የውሃ፣የመብራት እና የመንገድ ስራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስገንዝበዋል።የሴች ዱና ቀበሌ ጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ቦጋላ ደምሴ በበኩላቸው ለግብር ከፈዩ ህብረተሰብ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሰረት ግብርን በወቅቱ መክፈል በመቻላቸው የገቢ መጠን ከአመት አመት እያደገ መምጣቱን ጠቁመዋል።በዚህም በ2013 በጀት ዓመት ከ36 ሚሊየን ብር በላይ የተሰበሰበ ስሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ49 ሚሊየን የሚበልጥ ገቢ መሰብሰቡን አቶ ቦጋላ አውስተዋል።ለገቢው መጨመር ከቀበሌ እስከ ከንቲባ እና ዞን አስተዳደር ድረስ ያሉ ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት ተቀናጅተው መስራት በመቻላቸው ነው ብለዋል።በዘንድሮ ዓመትም ከ70 ሚሊየን የሚበልጥ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅደው ወደ ስራ መገባቱንም አቶ ቦጋላ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የቀበሌው ነዋሪዎች የሚጠበቅባቸውን የመንግስትን ግብር በወቅቱ በመክፈል እየተወጡ ያለው ባለቤትነት የታቀዱ የልማት ስራዎችን በታቀደለት ግዜ ለማከናወን እንደሚያግዝም አቶ ቦጋለ ገልጸዋል።በዕለቱ ግብር በመክፈል ላይ ከነበሩት ያነጋገርናቸው ግብር ከፋዮች በሰጡት አስተያየት ለመንግስት የሚከፍሉት ግብር ተመልሰው ለራሳቸው ልማት እንደሚውል በመገንዘብ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እየከፈሉ መሆኑን ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት በከተማው እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከህብረተሰቡ የሚሰበሰበው ገቢ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል የተጠናከረ ክትትል መደረግ እንደለበትም አሳስበዋል።

❝.. በመጨረሻም በሁሉም ጉዳዮች ላይ ጥሩ መረዳዳት ላይ ደርሰናል!❞ ~  አቶ ጌታቸው ረዳበትግራይ ስላለው ሁኔታ በቂ ማብራርያ ተሰጥቷል። በምዕራብ ትግራይ ስላለው ሁኔታ እና የትግራይ መንግ...
03/08/2022

❝.. በመጨረሻም በሁሉም ጉዳዮች ላይ ጥሩ መረዳዳት ላይ ደርሰናል!❞ ~ አቶ ጌታቸው ረዳ
በትግራይ ስላለው ሁኔታ በቂ ማብራርያ ተሰጥቷል። በምዕራብ ትግራይ ስላለው ሁኔታ እና የትግራይ መንግስት ለድርድር ከመቅረቡ በፊት መደረግ ስላለባቸው ሁኔታዎች እና እውነታዎችን የትግራይ የበላይ አመራሮች በቂ ማብራርያ ሰጥተናል ብሏል።
ዛሬ ወደ መቀሌ ተጉዘው የነበሩት የአሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ልዩ ልኡኮች ከትግራይ ክልል ባለስልጣናት ለኢትዮጵያ መንግስት የተፃፈ ደብዳቤ ይዘው ተመልሰዋል።

ማይክ ሐመር እና አኔት ዌበር ይዘው የተመለሱት ደብዳቤ ላይ የትግራይ ክልል ሀላፊዎች በክልሉ እንደ ስልክ፣ ኤሌክትሪክ፣ ባንክ ወዘተ አገልግሎቶችን ለማስጀመር ወይም የተጎዱትን ለማደስ ከፌደራል ለሚመጡ ባለሙያዎች ክልሉ የደህንነት ዋስትና እንደሚሰጥ አሳውቋል።

መንግስት ከዚህ በፊት ጥገና ለማድረግ የተሰማሩ ባለሙያዎች ላይ በትግራይ ሀይሎች ጥቃት ደርሶባቸው እንደነበር ገልፆ ነበር፣ ይህም ተጨማሪ ጥገና ለማድረግ አስቸጋሪ ሁኔታ እንደፈጠረ አሳውቆ ነበር።

ቀናት ወደ ሳምንታት፣ ሳምንታት ወደ ወራት፣ ወራት ወደ አመት እያዘገመ ቢሆንም ከቤተሰቦቻቸው የተጠፋፉ እና በስልክ እንኳን ደውለው ያሉበትን የማያውቁ፣ ለፍተው ያገኙትን ገንዘብ ማውጣት አቅቷቸው የተራቡ እና በጭለማ መኖር እጣ ፈንታቸው የሆኑ ዜጎች ይህ እውን ሆኖ ችግራቸው ይፈታ ዘንድ እኔም እመኛለው። መልዕክቱን #ሼር emsmereja

ታይዋን ለሶስት ቀናት ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ አወጀችይህ የአደጋ መቋቋም ዝግጁነት ሀይል ከዛሬ ጀምሮ እስከ ቀጣዩ ሀሙስ ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል።በቻይናው ግሎባል ታይምስ ላይ ትንታኔዎችን ...
02/08/2022

ታይዋን ለሶስት ቀናት ከፍተኛ የውጊያ ጥንቃቄ አወጀች

ይህ የአደጋ መቋቋም ዝግጁነት ሀይል ከዛሬ ጀምሮ እስከ ቀጣዩ ሀሙስ ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል።

በቻይናው ግሎባል ታይምስ ላይ ትንታኔዎችን በመጻፍ የሚታወቀው ሁ ጂያን የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ናንሲ ፔሎሲን አጅበው ወደ ታይዋን ለማስገባት ካሰቡ ይህ አሜሪካ በግልጽ በቻይና ላይ ወረራ እንደፈጸመች ይቆጠራል። የቻይና ጦርም አውሮፕላኑን መምታት እንዳለበት በትዊተር ገጹ አስፍሯል።

የአሜሪካ እና ቻይና የጦር አውሮፕላኖች እና የባህር ላይ ወታደሮቻቸውን ወደ ታይዋን አቅርበዋል።

01/08/2022

“ዚርኮን” ከድምፅ በ9 እጥፍ የሚፈጥነው አዲሱ የሩሲያ ሱፐር ሶኒክ ሚሳዔል

“የማይበገር” የተባለው ሚሳዔሉ ከባህር ላይ ተተኩሶ የአሜሪካዋ ዋሽንግተንን ለመምታት 5 ደቂቃ ይበቃዋል
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሩሲያ የጦር መርከቦች በቅርብ ዋት ውስጥ “ዚርኮን” የተባለውን አዲስ ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል እንደሚታጠቁ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ በትናትናው እለት እንዳስታወቁት፤ ዚርኮን አዲስ ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል “የማይበገር” አዲስ የጦር መሳሪያ ነው።
በሰዓት ከ6 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የሚምዘገዘገው ሃይፐርሶኒክ ሚሳዔል
አዲሱ የሩሲያ ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል ከድምፅ በ9 እጥፍ የሚፈጥ እና በቀላሉ የማይመታ እንደሆነም ነው እየተነገረ ያለው።
ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔል ምን የተለያ ያደርገዋል?
ሚሳዔሉ እስከ 1 ሺሀ ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ የማጥቃት አቅም ያለው ሲሆን፤ ሚሳዔሉ በፍጥነቱ በዓለማችን ላይ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም።
ሩሲያ በሚሳዔሉ ላይ ሙከራ ማድረግ የጀመረችው በፈረንጆቹ 2021 የበልግ ወቅት ሲሆን፤ የመጀመሪያዎቹ ሙከራዎችም ከሰርጓጅ መርከቦች ላይ የተደረገ ነው ተብሏል።
ሚሳዔሉ ለባህር ኃይል እና ለመድር ጦር እንዲሆን ተደርጎ የተሰራ ሲሆን፤ ለባህር ኃይል የተሰራው ለሰርጓጅ እና ባህር ላይ ለሚጓዙ መርከቦችም እንዲታጠቁት ተደርጎ ነው የተሰራው።
የሚሳዔሉ ፍጥነት ከድምጽ በ9 እጥፍ ይበልጣል የተባለ ሲሆን፤ ይህም የአየር መከላከያ ስርዓቶች አስቸጋሪ እና የማይመታ አድርጎታል።
“አደገኛው” የሩሲያ “ዛላ ኬ.ዋይ.ቢ” ድሮን
ሚሳዔሉ በአየር ላይ እያለ የመገለባበጥ አቅም ያለው ሲሆን፤ አውዳሚ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ የኒውክሌር አረር መሸከም የሚችል መሆኑም ተነግሯል።
የሩሲያ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ከሆነ ሚሳዔሉ ከዓለም አቀፍ የውሃ አካል ላይ ከተተኮሰ የአሜሪካዋ ዋሽንግተንን ለመምታት 5 ደቂቃ ብቻ ይፈጅበታል።
የቢሪታኒያው ሚረር ጋዜጣ እንዳስነበበው ከሆነ ደግሞ ሚሳዔሉ ከዓለም አቀፍ የውሃ አካል ላይ ከተተኮሰ የብሪታኒያዋ ለንደን ከተማን ለመምታ 4 ደቂቃ ብቻ ይበቃዋል ተብሏል።
የሩሲያው ታስ የዜና ወኪል መንነታቸው ያልተጠቀሰ የጦረ ምንጭን ጠቅሶ ባወጣው መረጃ፤ ዚርኮን ሱፐርሶኒክ ሚሳዔልን የታጠቁ የሩሲያ የጦር መርከቦች በቀጣይ መስከረም ወር ወደ ስምሪት እንደሚገቡ አስታውቋል።
✍️Alain

20/10/2020

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አፀደቀ

ሆሳዕና ፣ ጥቅምት 10፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አቅራቢነት ልዩ ልዩ ሹመቶችን አጸደቀ።

በዚህ መሠረት፦

1ኛ. አቶ ጥራቱ በየነ - በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ
2ኛ. ዶክተር መስከረምh ፈለቀ - ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ
3ኛ . ኢንጂነር አያልነሽ ሀ/ማርያም - ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ
4ኛ. ዶክተር መስከረም ምትኩ - የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
5ኛ. ዶክተር ሚልኬሳ ጃጋማ - መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ
6ኛ. ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ - ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ
7ኛ. አቶ ተፈራ ሞላ - ሰራተኛና ማህበራዊ ቢሮ ኃላፊ
8ኛ. አቶ ሙሉጌታ ተፈራ - ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

12/10/2020

የፌስቡክ ኩባንያ በፌስቡክ ገጽ አማካኝነት የሚሰራ ምርቶችን መሸጥ እና መግዛት የሚያስችል የመገበያያ መተግበሪያ ለኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ መጀመሩን አስታውቋል፡፡

የፌስቡክ የግብይት መድረኩ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጓቸውን ምርቶች በቀላሉ በፌስቡክ ገጻቸው አማካኝነት መግዛት እና መሸጥ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

በኢትዮጵያም አገልግሎቱ ከዚህ ወር መጨረሻ ጀምሮ ቀስ በቀስ ተደራሽ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን፥ እስከ ሕዳር ወር መጨረሻ ድረስ ሙሉ ለሙሉ እንደሚጀምር ታውቋል፡፡

የአገልግሎቱን መጀመር አስመልክቶ የፌስቡክ የምስራቅ አፍሪካ እና የአፍሪካ ቀንድ የሕዝብ ፖሊሲ ዋና ኃላፊ ሜርሲ ንድግዋ፥ "በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሮኒክ ግብይትን የሚያግዝ የፌስቡክ መገበያያ መድረክ በማስጀመራችን ደስታ ይሰማናል" ብለዋል።

የፌስቡክ ገጽን በመጠቀም ኢትዮጵያውያን የተወሰነ ግብይት እያከናወኑ እንደሆነ ስለምናውቅ የፌስቡክ ኩባንያም ደህንነቱ እና አስተማማኝነቱ የተጠበቀ አዲስ የግብይት መተግበሪያ ለኢትዮጵያውያን ማቅረቡ ትልቅ ስኬት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በግብይት መተግበሪያው ላይ ያለውን የግብይት መድረክ ቁልፉን በመጫን ወይም የፌስቡክ ግብይት ድረ ገጽን በመጎብኘት የሚፈልጉትን የዕቃ ዓይነት ከዝርዝሮቹ መሃል በዓይነትም ሆን በቦታ መምረጥ አልያም የሚፈልጉትን የምርት ዓይነት በቀጥታ ገብተው መጻፍ ይችላሉ፡፡

የግብይት ቁልፉን ሲጫኑ ተጨማሪ ዝርዝሮችን የሚያሳይ ሲሆን በሜሴንጀር አማካኝነት መልዕክቶችን ለሻጮች መተው ያስችላል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የሻጩን አጭር ግለ ታሪክ በመጫን ስለ ሻጩ መረጃ ማግኘት እና የሽያጭ ደረጃ ድልድሉን ማየት የሚያስችል ሆኖ ግዢና ሻጮች ስለ ክፍያ እና ለሎች ዝርዝር ሁኔታውን መረጃ የሚለዋወጡበት መድረክ ነው፡፡

ስለግብይት መተግበሪያው አሰራር ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ከታች ያለውን ድረ-ገጽ መጎብኘት ይችላሉ፡፡.

Address

Hossana
Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New adda posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to New adda:

Share