New adda

New adda New

የ45 ትምህርት ቤቶች መምህራን ሥራ አቆሙ !በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሐዲያ ዞን ምሥራቅ ባድዋቾ ወረዳ፣ ለተከታታይ ሦስት ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው የገለጹ ከ1,600 በላይ የ45 ትም...
17/10/2023

የ45 ትምህርት ቤቶች መምህራን ሥራ አቆሙ !

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሐዲያ ዞን ምሥራቅ ባድዋቾ ወረዳ፣ ለተከታታይ ሦስት ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው የገለጹ ከ1,600 በላይ የ45 ትምህርት ቤቶች መምህራን፣ ሥራ ማቆማቸውን አስታወቁ።

አማራጭ ገቢ እንደሌላቸው የገለጹት መምህራኑ፣ ቤተሰቦቻቸውን ማስተዳደር እንደተሳናቸውና ለረኀብ እንደተጋለጡ አመልክተዋል። በወረዳውም፣ የ2016 ዓ.ም. የትምህርት መርሐ ግብር እስከ አሁን እንዳልተጀመረ፣ መምህራኑ አክለው ተናግረዋል።

የሐዲያ ዞን ትምህርት መምሪያ፣ መምህራኑ ለተከታታይ ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው አምነው፣ ችግሩ በበጀት እጥረት እንደተፈጠረና ለመፍታትም ጥረት እየተደረገ እንደኾነ አስታውቀዋል።

Via : VOA

በሲዳማ ክልል ከተመደቡ ሠራተኞች ከግማሽ በላይ የኾኑቱ “ቋንቋ አትችሉም” ተብለው ተቀባይ እንዳጡ ቅሬታቸውን ገለጹከቀድሞ የደቡብ ክልል መንግሥት ሠራተኞች 349ኙ፣ በሲዳማ ክልል ቢመደቡም፣ ...
11/10/2023

በሲዳማ ክልል ከተመደቡ ሠራተኞች ከግማሽ በላይ የኾኑቱ “ቋንቋ አትችሉም” ተብለው ተቀባይ እንዳጡ ቅሬታቸውን ገለጹ

ከቀድሞ የደቡብ ክልል መንግሥት ሠራተኞች 349ኙ፣ በሲዳማ ክልል ቢመደቡም፣ ክልሉ ግን 223ቱን አልቀበልም ማለቱንና በዚኽም ለእንግልት መዳረጋቸውን፣ ሠራተኞቹ ገለጹ።

"ሲዳምኛ ቋንቋ አትችሉም፤” የሚል ምክንያት በክልሉ እንደተሰጣቸው ለአሜሪካ ድምፅ የገለጹት ሠራተኞቹ፣ በምደባ መስፈርቱ ውስጥ ባልነበረ ቅድመ ኹኔታ በደል ተፈጽሞብናል፤ ሲሉ፣ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

የሲዳማ ክልል የሕዝብ አገልግሎት ቢሮ፣ የክልሉ የሥራ ቋንቋ ሲዳምኛ በመኾኑ፣ ለክልሉ ከተመደቡት መካከል ቋንቋውን የሚችሉትን ብቻ እንደተቀበለ አስታውቋል።

ዜናውን ያጠናከረው VOA ነው

የህዝቦችን አብሮነት እና አንድነት በማጠናከር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ከዳር ማድረስ እንደሚገባ ተገለጸሀዋሳ፡ መስከረም 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የህዝቦችን አብሮነት እና አንድነት በ...
08/10/2023

የህዝቦችን አብሮነት እና አንድነት በማጠናከር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ከዳር ማድረስ እንደሚገባ ተገለጸ

ሀዋሳ፡ መስከረም 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የህዝቦችን አብሮነት እና አንድነት በማጠናከር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ከዳር ለማድረስ በጋራ መረባረብ እንደሚገባ የሀዲያና የከምባታ ዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች ተናገሩ።

ዋና አስተዳዳሪዎቹ የጠምባሮ ልዩ ወረዳ የመዋቅር ጥያቄ በሠላማዊ ትግል ምላሽ እንዲያገኝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላትንም አመስግነዋል።

ከ31 አመታት ሰላማዊ ትግል በኋላ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመዋቅር ጥያቄ ምላሽ በማግኘቱ ለጠምባሮ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መለስ አጪሶ እና የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫ ናቸው።

ከባለፉት ዓመታት ጀምሮ የከምባታና የሀድያ ህዝቦች ከጠምባሮና ከሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ጋር በአብሮነት ይኖሩ የነበሩ መሆናቸውን የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪዎቹ፥ የህዝቦች አብሮነት አሁንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ዋና አስተዳዳሪዎች በተለይ ሠላማዊ ትግሉ ከዳር እንዲደርስ ህዝቡን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ኃላፊነት የተወጡ የሀገር ሽማግሌዎችን የምክር ቤት አባላትን እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያቶች ዞንና ወረዳን የመሩ አካላትን አመስግነዋ ።

በልዩ ወረዳው የሚያጋጥሙ ማንኛውም መጥፎም ሆነ መልካም ጉዳይ የጋራ በመሆኑ እጅ ለእጅ ተያይዘን የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ መስራት አለብን ሲሉም ተናግረዋል ።

በተላይ በአካባቢዎቻችን ያሉንን ፀጋዎቻችንን በአግባቡ በመጠቀም ስራ አጥነትን ለመቀነስ እና ኢኮኖሚን ከፍ ለማድረግ የባከኑ ግዜያትን ለማካካስ መስራት ይገባል ብለዋል።

ለልዩ ወረዳ መቋቋሚያ የከምባታ ዞን የ2 ሚሊየን ብር እንዲሁም የሀዲያ ዞን የ1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል ።

በመርሀ ግብሩ የተሳተፉ የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው የልዩ ወረዳነት ጥያቄ ከ31 ዓመታት በኋላ ምላሽ ማግኘቱ የሠላማዊ ትግል ዉጤት በመሆኑ በእጅጉ መደሰታቸዉን ገልጸው፥ በቀጣይ ለልዩ ወረዳ ልማት የድርሻቸዉን እንደሚያበርክቱ ተናግረዋል።

07/10/2023
06/10/2023

ተጀመረ

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New adda posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to New adda:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share