08/09/2022
በሀዲያ ዞን ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሀብት አሰባሰብ መርሃግብር እየተካሄደ ነው
ጳጉሜ 3/2014 ዓ.ም (የሀዲያ ዞን መ/ኮ/ጉ/መምሪያ)
በሀዲያ ዞን የሚገኙ የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ያሰባሰቡትን ድጋፍ ለዞኑ ሀብት ሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ እያበረከቱ ነው።
የወረዳና የከተማ አስተዳደሮቹ የእርድ ሰንጋ፣ የፍየልና የበግ ሙክቶችን ጨምሮ ሰንባች የምግብ ቁሳቁስ ነው ለዞኑ ሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ እያበረከቱ የሚገኙት።
ድጋፍም ከአርሶ አደሮች፣ ከአጀረጃጀቶች፣ ከሀይማኖትና የትምህርት ተቋማት ከንግዱ ማህበረሰብ የተሰበሰበ ነው ተብሏል።
በድጋፍ ርክብክቡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫ፣ የዞኑ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ጌታቸው ሌሊሾን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ የመንግሥት የስሬ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ።