Zebidar Times

  • Home
  • Zebidar Times

Zebidar Times ለሀሳብ ነፃነትና ለጉራጌ አንድነት እንተጋለን!

የአብሬት ሼህ መስጂድ ታሪካዊ ቅርስነቱ በጠበቀ መልኩ የማስፋፊያ ግንባታ ሊደረግለት መሆኑን ተገለፀ!!ጥቅምት 29/ 2018   ዓ ም(ወልቂጤ)‎‎በጉራጌ ዞን ከሚገኙ ታሪካዊና ጥንታዊ ስፍራዎች...
08/11/2025

የአብሬት ሼህ መስጂድ ታሪካዊ ቅርስነቱ በጠበቀ መልኩ የማስፋፊያ ግንባታ ሊደረግለት መሆኑን ተገለፀ!!

ጥቅምት 29/ 2018 ዓ ም(ወልቂጤ)

‎በጉራጌ ዞን ከሚገኙ ታሪካዊና ጥንታዊ ስፍራዎች ውስጥ አንዱ የሆነው የአብሬት ሼህ መስጂድ በአዲስና ዘመናዊ ዲዛይን ከ200 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ በይፋ ተጀምሯል።

የ‎ፕሮጀክቱ ማስፋፊያ ግንባታ የመስጂዱን ታሪካዊ ቅርስነት በመጠበቅ፣ ዘመኑ የሚጠይቀውን የመማርያና የአምልኮ አገልግሎት ባካተተ መልኩ ለመገንባት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

‎ከዛሬ 147 ዓመት በፊት በዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት እንደተመሠረተ የሚነገርለት መስጂዱ ‎የእምነት ቦታው እንደ ጥንታውያን ጋሻዎች፣ ሰይፎች፣ ጦሮች፣ የቁርኣን ጥቅልሎች፣ መጽሐፎች እና የትርጉም ሥራዎች፣ የእንጨት ልባሶች፣የጠፈር አልጋዎች እና የማስተማሪያ መሳሪያዎች የመሳሰሉ ብርቅዬ ቅርሶችን በውስጡ ይዟል።

‎ አዲሱ የሚሰራው መስጂድ ሁሉንም ነገር ያካተተ ሲሆን፣ ሂፍዝ ማዕከል(የቁርኣን መሐፈዢያ) ጨምሮ የተሟላ የአምልኮ እና የማስተማሪያ ተቋም እንደሚኖረውም ተገልጿል።

‎የአብሬት ሼህ ልጅ የሆኑት ሰይድ ፋቲህ ሰይድ እንደተናገሩት የግንባታው ዋና ዓላማ፣የመስጂዱን ታሪካዊነት በማስቀጠል የቅድመ አባቶች ራዕይን እውን ማድረግ መሆኑንና ለቀጣይ ትውልድ የሚተላለፍ ትልቅ ሀብት ለማኖር መሆኑን ገልጸዋል።

‎አብሬት ሼህ መስጂድ የጉራጌ ዞን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ የታሪክ አካል ነው ያሉት ሰይድ ፋቲህ ይህንን መስጂድ በአዲስ መልክ የመገንባቱ ሥራ፣ ለሃይማኖታዊ ትውፊቶቻችንና ቅርስ አክብሮት እንዳለን ያሳያል ብለዋል።

በፕሮግራሙ የተገኙት ዶክተር መሐመድ ጀማል በበኩላቸው እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ የሀይማኖትና የቅርስ ጥበቃ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ገልጸው ይህ ታላቅ ፕሮጀክት የመስጂዱን ታሪካዊ እሴት ከመጠበቁም በላይ፣ በአካባቢው ለሚገኙት ወጣቶች ዘመናዊ የሃይማኖት ትምህርት ለመስጠት ያለመ ነው ብለዋል።

‎መስጂዱ የሁሉም ነገር ማዕከል (ሂፍዝ ማዕከልና ቁርኣን መቅሪያ) በመሆን የወረዳችንን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሚና ያሳድጋል ብለዋል።

‎የቸሃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ድንቁ እንደተናገሩት ታሪካዊ ቦታዎችን ማልማትና መጠበቅ የባህልና የልማት አካል መሆኑን አብራርተዋል።

‎የአብሬት መስጂድ የማኅበረሰባችንን ታሪክና መንፈሳዊ ትስስር የሚወክል ትልቅ ሀብት ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ይህ ታላቅ የማስፋፊያ ግንባታ ፕሮጀክት የሃይማኖት ተቋማት በወረዳችን ልማት ማኅበራዊ ትስስርና የቱሪዝም ፍሰት ላይ ያላቸውን ጠቀሜታ ያሳድገዋል ብለዋል ።

የፕሮጀክቱ ስኬት የእምነት ቦታውን ዘመናዊነት በማረጋገጥ፣ ለዘመናት የቆየውን የሃይማኖት መቻቻል ታሪክን የሚያጠናክር ይሆናል ብለዋል!!

በግንባታው ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የቸሃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሱ ድንቁ ጨምሮ የአብሬት ሼህ ልጆች ፣የወረዳው ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል ሲል የዘገበው የቸሀ ወረዳ መ/ ኮ ፅ/ቤት ነው!!

 #ወልቂጤ ከተማ ከቆሻሻና ሰርቶ ከማይበላ ነውጠኛ  እራሷን እያፀዳች ትገኛለች 💪ወደፊት ብቻ 👊  #ወልቂጤ  #ጉራጌ
08/11/2025

#ወልቂጤ ከተማ ከቆሻሻና ሰርቶ ከማይበላ ነውጠኛ እራሷን እያፀዳች ትገኛለች 💪

ወደፊት ብቻ 👊


#ወልቂጤ
#ጉራጌ

ጉራጌ ለፍቅር ሟች ለነውጠኛ ምች ነው።በጉራጌ ዞን የመንግስት ጉድለትና ክፍተት ለዘመናት እየረዳች ልማትና ውሃ ለተጠሙ እያጠጣች ለምትጓዘው ካቶልካዊት ቤ/ክርስቲያን ምስጋናችን ላቅ ያለ ነዉ።...
07/11/2025

ጉራጌ ለፍቅር ሟች ለነውጠኛ ምች ነው።

በጉራጌ ዞን የመንግስት ጉድለትና ክፍተት ለዘመናት እየረዳች ልማትና ውሃ ለተጠሙ እያጠጣች ለምትጓዘው ካቶልካዊት ቤ/ክርስቲያን ምስጋናችን ላቅ ያለ ነዉ።

#ጌታ
#ጉራጌ

መደበኛ ወ ኢመደበኛ 👉 ኢወማ
07/11/2025

መደበኛ ወ ኢመደበኛ 👉 ኢወማ

የቀቤና ነውጠኛ ወልቂጤ ውስጥ ያለው ትልቁ አስተዋፅኦ 🍋 👇
07/11/2025

የቀቤና ነውጠኛ ወልቂጤ ውስጥ ያለው ትልቁ አስተዋፅኦ 🍋

👇

በተግባር የተገነባን ማንነት በፅፈኞችና በአሉባልተኞች ስም የማጥፈት ዘመቻ አይናወጥም!በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ላይ በፅፈኞች እየተደረገ ያለው የስም ማጥፋት...
07/11/2025

በተግባር የተገነባን ማንነት በፅፈኞችና በአሉባልተኞች ስም የማጥፈት ዘመቻ አይናወጥም!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ላይ በፅፈኞች እየተደረገ ያለው የስም ማጥፋት ዘመቻ አጥብቄ እቃወማለው።

ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ፣ በክልሉ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የቁርጠኝነት፣ የሕግ የበላይነትና የህዝባዊ አገልጋይነት ምልክት መሆናቸውን ያስመሰከሩ ሰው ናቸው። አዲሱ ክልል ከተመሰረተበት ውስብስብ መዋቅራዊና አስተዳደራዊ ፈተናዎች አንፃር፣ ርዕሰ መስተዳድሩ የመሩት የለውጥ ጉዞ በአጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ውጤቶችን አስገኝቷል።

የዶ/ር እንዳሻው ዋነኛ መለያ ያለአድሎ በመርህ ላይ ተመስርቶ ክልሉን መምራት ነው። ክልሉ ከተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች የተዋቀረ በመሆኑ፣ ርዕሰ መስተዳድሩ ለሁሉም የክልሉ ነዋሪዎች እኩል ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ጠንክረው እየሰሩ ነው። ከዚህ ቀደም በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነርነት እና በተለያዩ የፌዴራል ተቋማት ውስጥ የነበራቸው ልምድ፣ የሕግ የበላይነትን ማስፈን እና ለሕብረተሰቡ ሰላም ቅድሚያ መስጠት እንዲችሉ አስችሏቸዋል።

በመሆኑም በክልሉ ምስረታ ወቅት የነበሩ የጸጥታ ስጋቶችን በብቃት በመያዝ፣ ሕዝቡ በሰላም ላይ ትኩረት አድርጎ ልልማት ላይ እንዲረባረብ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ችለዋል። ክልሉ ከተመሠረተ በኋላ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰላሙን ጠብቆ እንዲቆም የመቻሉ ምስጢር የጠንካራና የመርህ የበላይነትን ባረጋገጠ አመራር ነው።

ነገር ግን ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በመርህና በቁርጠኝነት ያለአድሎ ክልሉን መምራታቸው ፣ለሌብነት አለመመቸታቸውና የተግባር ሰው መሆናቸው ያላስደሰታቸውና ፍላጎታቸው ማሳካት ያላቻሉ ፅፈኞችና የዘረፋ ቡድኖች ስም የማጥፋትና የማጠልሸት ዘመቻ በመክፈት ዒላማ አድርገዋቸዋል። በተለይም ጉራጌ በመሆናቸው ብቻ ሐሰተኛ እና ዘር ተኮር የጥላቻ ትርክቶች በማኅበራዊ ሚዲያ በፅፈኞች እየተካሄደባቸው ይገኛል።

ይህ ዓይነቱ የስም ማጥፈት ዘመቻ ከመሪው ሥራ እና አፈጻጸም ይልቅ በዘር ማንነት ላይ ትኩረት ማድረጉ፣ የአጥፊዎቹን ጠባብነትና እኩይ ዓላማ ያሳያል።የእነዚህ ፅንፈኞች ድርጊት የመሪውን ሥራዎች በፍትሃዊነት እንዳይታዩ የሚጋርድና አዲስ የተቋቋመውን ክልል የልማት ጅምርን የሚያውክ ነው።

ይህ የስም ማጥፋት ዘመቻ በዋነኛነት የሚመነጨው እንደለመዱት የህዝብን ሀብት መዝገንና መዝረፍ ባልቻሉ አመራሮችና የሌላው መሬት የመውረር ምኞት ባላቸው ጽንፈኛ አክቲቪስቶች ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ዶ/ር እንዳሻውን በማንነታቸው በማግለልና ስማቸውን በማጥፋት ከሕዝብና ከመንግሥት ጋር የገነቡትን እምነት ማናጋት ነው።

ማንኛውም መሪ የሕግ የበላይነትንና ለሁሉም እኩልነትን ለማስፈን ሲነሳ፣ ጠባብ ኃይሎች ከስራ ይልቅ በዘር በማንነት ላይ ያተኮረ ስም ማጥፈት ልዩ ባህሪያቸው መሆኑ የታወቀ ጉዳይ ነው። እነዚህም ፅንፈኛ አክቲቪስቶች ዶ/ር እንዳሻው ጉራጌ በመሆናቸው ብቻ፣ ለክልሉ አመራርነት ብቁ አይደሉም ወይም የጉራጌን ፍላጎት ብቻ ያስፈጽማሉ የሚል መሠረተ ቢስ ትርክት ሲነዙ ይታያሉ።

ነገር ግን ርዕሰ መስተዳድሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ የተመሰረተውን ክልል በማደራጀትና በልማት ጎዳና ላይ በማስኬድ ያሳዩት ቁርጠኝነትና ውጤት ማንኛውንም የዘር መድልዎ ውንጀላ ያከሽፈዋል። ዶ/ር እንዳሻው በመዋቅርና በአመራር ሹመት ላይ የክልሉን ብሔረሰቦች ሁሉ ያካተተ አደረጃጀት ለመፍጠር መስራታቸው፣ የጠባብነት ውንጀላን በግልጽ ይቃረናል። የእያንዳንዱ ብሔረሰብ መብት እንዲከበር መሥራታቸው ብሔራዊ መሪ እንጂ የአንድ ዘር ተወካይ እንዳልሆኑ ያረጋግጣል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ከየዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም በየጊዜው ከተለያየ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር የሚያደርጉት ተከታታይ ውይይቶች እና የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚደረገው ጥረት፣ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች ሁሉ በጋራ ልማትና መልካም አስተዳደር ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ያሳያል። እንዲሁም ያለፉት ዓመታት ጉዞ በሚያስደንቅ የሕዝቦች ተሳትፎ የታጀበ መሆኑ፣ ርዕሰ መስተዳድሩ በሕዝብ ዘንድ ያላቸውን ጥልቅ አመኔታ የሚያሳይ ነው።

ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚመሩት አመራር በሁሉም የክልሉ ሕዝቦች ተጠቃሚነትና በመርህ ላይ የተመሠረተ ነው። በጉራጌ ማንነታቸው ላይ የሚሰነዘረው የጥላቻና የስም ማጥፋት ዘመቻ ተቀባይነት የሌለውና በጠንካራ የሥራ ውጤትና በሕዝባዊ አመኔታ ውድቅ የሆነ ሀሳብ ነው። በመሆኑም የክልሉ ሕዝብና አመራር ትኩረቱን ከዚህ ጠባብ የጥላቻ ትርክት አውጥቶ የተጀመሩትን የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ማጠናከር ላይ ማተኮርና አለበት።

ቀቤና ልዩ ወረዳ ላይ የመሸገው ነውጠኛ ቡድን እስረኞችን የማስመለጥ እቅዱ ከሸፈ።ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥቅምት 28, 2018 ዓ.ልትላንት ማምሻውን በቀቤና ልዩ ወረዳ መሽጎ እሚገኘው ነውጠኛ አ-መ...
07/11/2025

ቀቤና ልዩ ወረዳ ላይ የመሸገው ነውጠኛ ቡድን እስረኞችን የማስመለጥ እቅዱ ከሸፈ።

ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥቅምት 28, 2018 ዓ.ል

ትላንት ማምሻውን በቀቤና ልዩ ወረዳ መሽጎ እሚገኘው ነውጠኛ አ-መደበኛ ቡድን ወልቂጤ ከተማ በአራቱም አጎራባቾች በኩል በመሆን አዳሩን በተኩስ እሩምታ ለማሸበር ሲሞክር አድሯል።

የተኩሱ አላማ የወልቂጤ ማህበረሰብና የፀጥታ አካላትን ትኩረት ተኩስ ወደ ተከፈተበት በመሳብ በቅርቡ ፖሊስ በተለያዩ ወንጀሎች ጠርጥሮ በህግ ቁጥጥር ስር ያዋላቸውን ግብረ-አበሮቻቸውን ከእስር ቤት ለማስመለጥ ያለመ ነው ተብሏል።

ፖሊስ የእነዚህ ነውጠኞች የማህበራዊ ሚዲያ ግብረ-አበሮች ሲያሰራጩት የነበረውን መረጃ በመገንዘብና ቀድሞ በደረሰው ጥቆማ መሰረት እስር ቤቶቹን በተጠንቀቅ በመጠበቁ ያሰቡት እስረኛ የማስመለጡ እቅድ ሳይሳካ ቀርቷል።

መንግስት በሚያስተዳድራቸው የልዩ ወረዳው የወልቂጤ ከተማ አጎራባቾች ለረጅም ሰዓት የቆየ የትንኮሳና የማደናገሪያ የመሳሪያ ተኩስ መሰማቱ ልዩ ወረዳው አሁንም ከኢ-መደበኛ ነውጠኛው ቡድን ተጽዕኖ ውጪ አለመሆኑን አመላካች ነው። ልዩ ወረዳው አሁንም ራሱን መፈተሽና ማጥራት ይጠበቅበታል፤ የክልሉም መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት መስጠት ይጠበቅበታል።

© Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ
Wolkite City Administration Government Communication Affairs Office

06/11/2025

#ኢወማ የተባለ በሲቪክ ማህበረሰም ስም የተቋቋመ ነገረ ስራው የዱርዬ በ3 ዙር ከወልቂጤ ከተማ የዘረፈውን መሳሪያ በሀገር መከላከያና በፌድራል ፖሊስ ላይ በጨለማ እየተኮሰ ነው።

ወንጀለኛና ነውጠኛ ወሮበላ ወጣቶችን ከእስር ለማስመለጥ ህገ ወጥ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው።

#ወልቂጤ
#ጉራጌ

06/11/2025



ወልቂጤ ከተማ ውስጥ ምክንያቱ ያልታወቀ የተኩስ ድምፅ እየተሰማ ነው።

 የሰለጠነ አለም ቁጭ ብሎ በቆሴ ከተማ ከህገ ወጥ ቡድኖች ለገዛው ቁራጭ መሬት ብሎ ወድሞቹን ለጦርነትና ለግድያ የሚቀሰቅሰው የሃድያው አርቲስት ስንታየሁ ጥላሁን(ሂቦንጎ):: ስንታየሁ ጥላሁን...
06/11/2025


የሰለጠነ አለም ቁጭ ብሎ በቆሴ ከተማ ከህገ ወጥ ቡድኖች ለገዛው ቁራጭ መሬት ብሎ ወድሞቹን ለጦርነትና ለግድያ የሚቀሰቅሰው የሃድያው አርቲስት ስንታየሁ ጥላሁን(ሂቦንጎ)::

ስንታየሁ ጥላሁን ሂቦንጎ በሚል ዘፈኑና በሌልችም የሃድይኛ ዘፈኖቹ የሃድያን ህዝብ ቱባ ባህል በማስተዋወቅ ታዋቂነት ያተረፈ በተለያዩ መድረኮችም እየተጋበዘ አሁንም ድረስ የሚዘፍን አርቲስት ነው:: አርቲስት ህዝቡን ባህሉን ብሎም አካባቢውና አገሩን ታሪክን ወግን ፍቅርንና አንድነትን እየሰበከ የተጣላን በማስታረቅ የተራራቀን በማቀራረብ የራሱን አዎንታዊ ተፅዕኖ ይፈጥራል ከሰፈር ወጥቶ አገራዊ ይሆናል የሁሉም ይሆናል እንጂ ስሙንና እውቅናውን ተጠቅሞ የለየለት የጥላቻ ሰባኪ አይሆንም::
ስንታየሁ ግን ማንም በማይጠብቀው መልኩ እንኳን እንደሱ በኢትዮጵያውያን ከፋ ያለ ግለሰባዊ ስብዕናና ማንነት የገነባ ቀርቶ ተራ ውሪ እንኳን ያደርገዋል ተብሎ በማይገመት ከባድ የህዝብ ለህዝብ የማጋጨትና የጥላቻ ቅስቀሳ ላይ በመሳተፍ ምንም የማያውቁ ወጣት ሃድያዎችን ለጥፋትና ለግድያ እያነሳሳ ይገኛል:: ኢትዮጵያን ሁሉ እንዲያውቁት አርቲስት ስንታየሁ(ሂቦንጎ) ከልጆቹና ከቤተሰብቹ ጋር አሜሪካን በጥገኝነት እየኖረና ኡበር ታክሲውን እየነዳ ባለው ጊዜ ነው እንግዲህ ይህ የሃድያ ፕሬስ (Hadiya Press) የሚል የፌስ ቡክ ፔጅ ከፍቶ ጥዋትና ማታ በዚህ ደረጃ ወርዶ ባሳደገው የራሱ ማህበረሰብ ላይ ጥላቻን ግጭትን :ፀብና ሁከት እንዲፈጥሩ ግፋ በለው አይዞን የሚለው:: ይህ አሳፋሪ ድርጊት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በተለይ ቨርጂኒያ ዲሲና ሜሪላንድ ያሉ ኢትዮጵያኖች: ጉራጌዎችና ሚድያዎች በሙሉ ማወቅ ይኖርባቸዋል ኡበር ስትጠሩ ድንገት ከመጣም ቲፕ በሉት:: ስንተየሁ ሂቦንጎ የተማረ ይሁን ተራ ሰው መረጃው የለኝም ነገር ግን እዚህ ጋር የማህበረሰብ ይቅርና የግለሰብ መብት እስከ ጥግ በሚከበርባት አሜሪካ ሆኖ ነፃነቱን እያጣጣመ ወገኖቹ ላይ ውረሩ እረዱ ግደሉ አዋጅ ሲያውጅ ይውላል:: እንግዲህ ዲሲ ሜሪላንድ ያላችሁ ብዙ ማድረግ አይጠበቅባችሁም ይችን ጥንባን የጣለች የጥላቻና የሁከት ጥሪ ከራሱ ገፅ ላይ እስከነ ፎቶው እስክሪን አድርጋችሁ ወደ ኢሚግሬሽን ቢሮ አድርሱለት:: አገሬ በነፃነት መኖር ተከለከልኩ ተገረፍኩ ተሰቀልኩ ብሎ ጥገኝነት የጠየቃት አሜሪካ ጉያ ውስጥ ተወሽቆ ሌላውላይ ጭፍን ጥላቻና ጥቃት እንዲካሄድ እየቀሰቀሱ መኖር ይችል እንደሆን እናያለን:: የአርቲስትነ ካባውን አውልቆ በመጣል የአንድ ተራ ጠብደል መሃይም ስራ ሲሰራ ነው የሚውለው :: ከዚህ በኃላ ከዚህ ፅዪፍና አሳፋሪ ምግባሩን ይዞ ማንም መድረክ ድርሽ እንዳይል እዛው የጥላቻ ጭቃውን ሲያቦካ እንዲውል መደረግ ይኖርበታል:።

The emerging map of
06/11/2025

The emerging map of


Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zebidar Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share