
27/01/2025
በቡታጅራ ከተማ የሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ከተማ አቀፍ የግማሽ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና እየተሰጠ መሆኑን ጽ/ቤቱ አስታወቀ።
(ቡታጅራ ጥር 19/2017 የመንግስት ኮሙኒኬሽን)
የትምህርት ቤቶች ጽ/ት ዛሬ ከ4ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ለሚገኙ ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አስታውቋል።
የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሀቢብ አብደላ በከተማችን ከሰባት በላይ ከ1ኛ ደረጃ እስከ መሰናዶ የፈተና መስጫ የግልና የመንግስት ማዕከላት መኖራቸውን ገልፀዋል።
በዚህም ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ መምህራንን በመመልመል ከፈተና ማዘጋጀት ጀምሮ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
የምዘና ስርዓቱ በተማሪዎች ውጤት ላይ ተወዳዳሪነት ለመጨምር የትምርት ስብራትን ለማሻሻል ተማሪዎችን በክፍል ውጤታቸው በዞን እና በሀገር አቀፍ ፈተና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ወጥነት ያለው የመመዘኛ መስፈርት አሟልተዉ እንዲያልፉና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ ተወዳዳሪ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በጽ/ቤቱ የአጠቃላይ ፈተናና ምዘና ስራ ሂደት ዳይሬክቶሬት አቶ አህመድ ወደዶ በበኩላቸው በከተማችን የሚገኙ የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ምክትል እና ዋና ርዕሳነ መምህራንን በማወያየት 6ኛ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍሎች በክልል አቀፍ እና በሀገር አቀፍ መመዘኛ መስፈርት መሰረት መሆን አለበት በሚል የተጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
ከመማር ማስተማሩ ጋር መምህራን በየክፍል ደረጃ በመመልመል ፈተና መዘጋጀቱና በትላትናው እለት ታሽጎ ወደየትምህርት ቤት መስራጨቱን ለሁሉም የት/ት ደረጃ የመፈተኛ ወጥ የሆነ ሰዓት ወጥቶላቸው እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልዖል።
የመቅቾ ከፍተኛና 2ተኛ ደረጃ ት/ት ቤት ዋና ርዕሰ መምህር አቶ ፈቱዲን ኑሪ የፈተና የ2017 የአንደኛ ሴሚሰተር ከጥር 19 እስከ 23 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እንደሚሰጥ እኛም በወጣው መሰረት ከ9ኛ--12ኛ ክፍል ጀምሮ ተማሪዎች በተረጋጋ መልኩ እየወሰዱ እንደሆነ እና ከ9 -11 በከተማ ደረጃ በሁሉም ክላስተሮች እንደሚሰጠው መሆኑን ተናግረዋል። ለ12ኛ ክፍሎች ለሀገር አቀፍ በሚያዘጋጅ ልክ ከሞዴል ባልተናነሰ መልኩ ዝግጅት ተደርጎ እየተሰጠ መገኘቱን ገልፀዋል።
ፈተናውን አስመልክቶ አስተያየት ከሰጡ ተማሪዎች መካከል ተማሪ አምረላ ከማል እና ተማሪ ልደት ነጋ የቡታጅራ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው ፈተናው የተማርነው እና እኛም ከመማር ጎን ለጎን ቤተ-መጽሐፍት በመጠቀም የማጠቃሻ መፃሕፍቶችን መሰረት ያደረገ መሆኑን ፤በቂ ዝግጅትም እንዳደረጉ ተናግረዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን፦
ቴሌግራም https://t.me/ButajiraCommunication/58
ፌስቡክ https://www.facebook.com/buta1921/
ዩቲዩብ
https://youtube.com/
ትዊተር https://mobile.twitter.com/ButajiraB
ኢንታግራም https://www.instagram.com/butajirab