ArbaMinch FM 90.9 / አርባምንጭ ኤፍ ኤም 90.9

ArbaMinch FM 90.9 / አርባምንጭ  ኤፍ ኤም 90.9 የአርባ ምንጭ ኤፍ ኤም 90.9 ሬድዮ የህብራዊነት ድምፅ በመሆኑ ያዳምጡታል ይናገሩበታልም !
(1)

የጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን  ቴክኖሎጂ መምሪያ  የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን ለእይታና ለውድድር  አቀረበ።  የጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ   ሀላፊ  ወ/ሮ ሰላማዊት ...
18/06/2024

የጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን ለእይታና ለውድድር አቀረበ።

የጋሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ቦዳ ከወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደር መዋቅር ጋር በመሆን የተካሔደው ኤግዚቢሺን በቴክኖሎጂና ኢንፎርሜሽን የተሻለ ትውልድ ለመፍጠር የሚኖረው ጠቀሜታ የጎላ ነው ብለዋል።

በዚህም በቴክኖሎጂ የሚባክነውን የሰው ሐይል ተክቶ ለመስራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት ሀላፊዋ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን ዕውቀት በተግባር ስደገፍ የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል።

ወ/ሮ ሰላማዊት ዘመናዊ የሆኑ ቴክኖሎጅዎችን መመሪመር፣መቅዳትና ማላመድ የሚያስችሉ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀው በ10 ዓመት ዕቅድ ችግር ፈቺ የልማትና የለውጥ ዘመን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።

የጋሞ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሰብስቤ ቡናቤ ሁሉም መዋቅር ICT የበለፀገ እንዲሆን በሰው ሀይልና በበጀት የመደገፍ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በፈጣራ ሥራ ማሳያ አውደ ርዕይ ከተለያዩ መዋቅሮች የተጋበዙ የፈጠራ ባለቤቶች ተሣታፊ ሆነዋል።

ዘጋቢ ማስረሻ ዘውዴ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋርዱላ ዞን አርሶ አደሮች በበልግ እርሻ የጤፍ ምርት ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻ ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናገሩ ።አርባምንጭ ሰኔ 11/10/16 (ኤፍኤም 9...
18/06/2024

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋርዱላ ዞን አርሶ አደሮች በበልግ እርሻ የጤፍ ምርት ከመሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻ ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናገሩ ።

አርባምንጭ ሰኔ 11/10/16 (ኤፍኤም 90.9)

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ የካርፋገነት ቀበሌ አርሶ አደር አወቀ ዘውዴ እና ኪታባይታ ሞሌ በበልግ እርሻ ጤፍ ምርት መሰብሰብ ጎን ለጎን የመኸር እርሻ ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

በበልግ ወቅት የተስተዋለውን የዝናብ መብዛት ተከትሎ የጤፍ ምርት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ጠቁመው በመኸር እርሻ ለማካካስ በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል ።

***********

ክልሌ ደቡቤ ኢትዮጵያ ኦዳምፓያ ዞነ ጋርዱላ ካሻቻ ኡላ ኦዳ ካሻና ኦሮሆባ ቃበቻዶ ድንዴ ድንደነ ኡላ ኦዳ ሀካያ ድክሳነቻላ ክያነቻዶ ዋርየነ።

ኡላ ኦዳ ካሻናኸ ሮባ ቃራነ ታርበ ሮበነ ኮባኸ ካሻቻ ኤታናቅዮቶ ኡላ ኦዳ ሀካያኸ ሆባያላኸ/ፖራያላኸ/ አከቻኸ ቅመቻነ ኤርካነቻላ ክያነቻዶ አሰቻነ ኸዋርየነ።

ዘጋቢ፡ እንጃ ገልሲሞ

በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ በህገ ወጥ መንገድ ደረሰኝ አሳትሞ ሲጠቀም  የነበረ እና ታክስ የሰወረ  ግለሰብ በእስራትና በገንዘብ መቀጮ ተቀጣአርባምንጭ ሰኔ11/2016 ዓ.(አርባ ምንጭ...
18/06/2024

በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ በህገ ወጥ መንገድ ደረሰኝ አሳትሞ ሲጠቀም የነበረ እና ታክስ የሰወረ ግለሰብ በእስራትና በገንዘብ መቀጮ ተቀጣ

አርባምንጭ ሰኔ11/2016 ዓ.(አርባ ምንጭ ኤፍ ኤም )፦ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም ቱሉ እንደገለፁት በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ሸሌ ሜላ ቀበሌ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ተሰማርቶ የነበረ ግለሰብ በ2015 ዓ.ም ለታክስና ግብር አሰባሰብ አገልግሎት ብቻ የተፈቀደን ደረሰኝ በህገወጥ መንገድ አሳትሞ ሲጠቀም በፍርድ ቤት ብርበራ ትዕዛዝ መሠረት በአርባምንጭ ከተማ የሚገኝ ቤቱ ሲበረበር መሂ/7ሐ ሴሪ 18ኛ ንሙራ ቁጥር ከ00104 እስከ ዐዐ150 እና 00201_002012 ያለቀሪ በራሪዉን ብቻ በህገ-ወጥ መንገድ የታተመ ደረሰኝ ተገኝቷል ።
የጋሞ ዞን መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ እንደዘገበው ከዐቃቤ ሕግ የቀረበለትን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በጥልቀት የተመለከተው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 4/2016 ዓ. ባስቻለው ቾሎት ተከሳሽ ስጦታ መተኪያ ለታክስና ግብር አሰባሰብ አገልግሎት ብቻ የተፈቀደን ደረሰኝ በህገወጥ መንገድ አሳትሞ በመጠቀምና በግለሰብ እጅ በመገኘቱ እና በተጨማሪ እሴት ታክስ የተሰበሰበ 78 ሺህ 945 ብር ለመንግስት ገቢ አለማድረጉን አረጋግጧል ።

ተከሳሽ ስጦታ መተኪያ በሁለት ክሶች ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ የዞኑ ከፍተኛ ፍ/ቤት በ7 ዓመት ከ 6 ወር ጽኑ እስራት እና በ20 ሺህ ብር እንዲቀጣ ወስኖበታል።

ህብረተሰቡ ከእንዲህ ዓይነት መሰል የወንጀል ድርጊት ከመፈጸም ተቆጥቦ ህግን በማክበርና በማስከበር ረገድ የበኩሉን ሚና እንዲጫወት አቶ አብርሃም ቱሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

በአውሮፓ ዋንጫ ጫወታ  በምድብ 4 ፈረንሳይ ኦስትሪያን 1  ለ 0  አሸነፈችአርባምንጭ ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍኤም 90.9 )  ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተደረገ የምድብ 4 ጨዋታ ፈረንሳይ ኦ...
17/06/2024

በአውሮፓ ዋንጫ ጫወታ በምድብ 4 ፈረንሳይ ኦስትሪያን 1 ለ 0 አሸነፈች

አርባምንጭ ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍኤም 90.9 )

ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተደረገ የምድብ 4 ጨዋታ ፈረንሳይ ኦስትሪያን 1 ለ 0 አሸነፈች፡፡

የፈረንሳይን የማሸነፊያ ጎል ኦስትሪያዊዉ ዎበር በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሯል፡፡

ከዚሁ ምድብ ትናንት በተደረገ ጨዋታ ኔዘርላንድስ ፖላንድን 2 ለ 1 ማሸነፏ ይታወሳል፡፡

ዛሬ ቀደም ብሎ ምሽት 1 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ቤልጂየም በስሎቫኪያ የ1ለ0 ያልተጠበቀ ሽንፈት አስተናገደች፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገ ሌላ ጨዋታ ደግሞ ሮማንያ ዩክሬንን 3 ለ 0 ረትታለች፡፡

ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ

የወባ በሽታን መከላከል የሚያስችል በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ገለጸ፡፡አርባምንጭ ሰኔ 10/10/16/( ኤፍኤም 90.9)ለወባ ተጋላጭ በሆኑ ...
17/06/2024

የወባ በሽታን መከላከል የሚያስችል በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ገለጸ፡፡

አርባምንጭ ሰኔ 10/10/16/( ኤፍኤም 90.9)

ለወባ ተጋላጭ በሆኑ ቀበሌያት ያቆረ ውሃ የማከምና የአከባቢ ቁጥጥር ስራዎች መሰራታቸውም ተመላክቷል፡፡

በዙሪያ ወረዳው የቆላ ሼሌ ቀበሌ ነዋሪ ከሆኑት መካከል ወ/ሮ መቅደስ ዳንኤል እና ወ/ሮ መስከረም ማቄ የግልና የአከባቢ ንጽህናን በአግባቡ በመጠበቅ የወባ ስርጭትን እየተከላከሉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በሼሌ ጤና ጣቢያ ያገኘነው ታምራት ቡሊዶ ከጤና ባለሙያዎች በተሰጣቸው ግንዛቤ የአከባቢያቸውን ንጽህና በመጠበቅ ፣ ለወባ ትንኝ መራቢያ የሚሆኑ ቦታዎችን በማጽዳትና አጎበርን በአግባቡ በመጠቀም ወባን እየተከላከሉ እንደሆነ ተናግሯል፡፡

የኤልጎ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ማርታ መልዬ ቀበሌያቸው ወባማ በመሆኑ አጎበርን በአግባቡ በመጠቀም ያቆሩ ቦታዎችን በማዳፈን ወባን እንደሚከላከሉ ገልጸዋል፡፡

የሼሌ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ባህሩ በሌላ በሽታውን ከመከላከል ጋር ተያይዞ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውንና በጤና ጣቢያው በወባ በሽታ ለተያዙ ትኩረት በማድረግ መድሀኒት በአግባቡ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ወባና ትኩረት የሚሹ በሽታዎች ኦፊሰር ወ/ሮ ሙሉነሽ ሜጋሮ በወረዳው 65 ከመቶ የሚሆነው የህብረተሰብ ክፍል ለወባ በሽታ ተጋላጭ መሆኑንና ለ11 አመታት በተሰራው ጥናት 6 ሺ 80 ሰዎች በወባ ተጠቂ እንደነበሩ ጠቅሰዋ፡፡

በመሆኑም ይህንን መከላከል እንዲያስችል በርካታ ተግባራት መከናወናቸውንና ከነዚህም ውስጥ ያቆሩ ውሃ የማከም፤ የአልጋ አጎበር አጠቃቀም ክትትልና ትኩሳት ያለባቸውን ሰዎች በአፋጣኝ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ ይጠቀሳል ብለዋል፡፡

እንደወረዳ የወባ በሽታን በይበልጥ ለመቀነስ ሰፊ ጥረት እየተደረገ ነው ያሉት ወ/ሮ ሙሉነሽ ህብረተሰቡ ራሱንና ቤተሰቡን ከወባ በሽታ ለመጠበቅ የአልጋ አጎበርን በአግባቡ ከመጠቀም ባለፈ ራሱን ከትንኝ ንክኪ መጠበቅ እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ዘጋቢ ፡ ማርታ ሙሉጌታ

1445 ኛው የኢድ አል አድሃ ወይም አረፋ  በዓልን ምክንያት በማድረግ በአርባምንጭ ከተማለአቅመ ደካሞች   400 በሬዎችን  ድጋፍ ተደረገ ።አርባምንጭ ሰኔ 09/10/16 (ኤፍኤም 90.9)መ...
16/06/2024

1445 ኛው የኢድ አል አድሃ ወይም አረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአርባምንጭ ከተማለአቅመ ደካሞች 400 በሬዎችን ድጋፍ ተደረገ ።

አርባምንጭ ሰኔ 09/10/16 (ኤፍኤም 90.9)

መስጠት በምድርም በሰማይም ከአላህ በረከት የሚያስገኝ በመሆኑ መደጋገፉ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ የጋሞ ዞን አስተዳደር አሳስቧል ።

በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የአርባምንጭ ከተማ መሲኪድ ጃሚኢ ኢማም ሼህ አህመድ አብዱ በዓሉ ካለን አካፍለን በደስታ የምናከብረው ከመሆኑም ባሻገር አንድነትን ፣ መስዋዕትነትን እና መተሳሰብን የምናጎለብትበት ነው ብለዋል ።

የአርባምንጭ ከተማ እስልምና ጉዳይ የቀድሞው ሰብሳቢ ሀጂ አህመድ መሀመድ ሁሴን በበኩላቸው የኢድ አል አድሀ አረፋ በዓልን ስናያከብር ኢብራሂም እና ልጃቸው እስማኤል ለአላህ የታዘዙበትን መንገድ በመከተል መሆን አለበት ሲሉ አሳስበዋል ።

የድጋፉ አስተባባሪ ዶክተር የሲን ሁሴን ከረጂ ድርጅቶች ጋር በመሆን በዓሉን አስመልክተን በከተማው ለሚገኙ ድጋፍ ለሚሹ አካላት 400 በሬዎችን ማከፋፈል መቻሉን ተናግረዋል ።

አክለውም በኡዲሂያ እርድ አንድ ሶስተኛውን ለምስኪኖችና ለአቅመ ደካሞች መለገስ የእምነቱ አስተምሮ እንደሆነም በመግለፅ ።

መስጠት በሰማይም በምድርም በረከት ያስገኛል ያሉት ደግሞ የጋሞ ዞን አስተዳደር ተወካይ እና የመልካም አስተዳደር እና አከባቢ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ የስጋት ስንታ በማዕድ ማጋራት መርሀ ግብር በዞኑ በበዓላት ተመሳሳይ ድጋፎች እየተደረጉ እንደሚገኙ ጠቁመዋል ።

በጋሞ ዞን አስተዳደር ስም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል ደሃ / አረፋ / በዓል በሰላም አደረሳችሁ የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል አቶ የስጋት ።

ድጋፍ ከተደረገላቸው አካላት መካከል ወ/ሮ በረከት በረካና አቶ ኑሪ ያሲን በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው ድጋፉን ላደረጉላቸው አካላትንም አመስግነዋል ።

ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ

1445 ኛው የኢድ አል አድሃ ወይም አረፋ  በዓል በአርባምንጭ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል ።አርባምንጭ ሰኔ 09/10/16 ( ኤፍኤም90.9)  በዓሉ ነብዩ ኢብራሂም ልጃቸው እስማኤልን...
16/06/2024

1445 ኛው የኢድ አል አድሃ ወይም አረፋ በዓል በአርባምንጭ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል ።

አርባምንጭ ሰኔ 09/10/16 ( ኤፍኤም90.9)

በዓሉ ነብዩ ኢብራሂም ልጃቸው እስማኤልን በአላህ ትእዛዝ ለመስዕዋት ሲያዘጋጁ በምትኩ ሙክት በግ መቅረቡን የሚያስታውስ በመሆኑ የመስዋዕት በዓል ተብሎም ይከበራል።

ከዚህም ባሻገር በዓሉ የአብሮነትና የአንድነት እንዲሁም የመስጠት በዓል እንደሆነ የዕምነቱ ተከታዮች ይናገራሉ ።

በአርባምንጭ ከተማ በመስኪዳል ጃሚ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል ።

ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ

መንግስት ለሰላም ያለውን ፅኑ ፍላጎትና የማይናወጥ አቋም በተደጋጋሚ አሳይቷል፡፡የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳመንግስት ለሰላም ያለውን ፅኑ ፍላጎትና የማይናወጥ...
15/06/2024

መንግስት ለሰላም ያለውን ፅኑ ፍላጎትና የማይናወጥ አቋም በተደጋጋሚ አሳይቷል፡፡

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ

መንግስት ለሰላም ያለውን ፅኑ ፍላጎትና የማይናወጥ አቋም ወደ ስልጣን ከመጣበት እለት አንስቶ እስካሁን በተደጋጋሚ አሳይቷል ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ተናገሩ፡፡

ሚኒስትር ዴኤታዋ ሰላማዊት ካሳ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በኢኮኖሚያዊ ምጣኔ ሃብት እድገት፣በክረምት የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን እና የሰላም ጉዳይን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ መንግስት የማይናወጥ የሰላም አቋሙን ለማጽናት የብሄራዊ ምክክር ኮሚሽንን በማቋቋም ብሎም አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ በማድረግ ወደ ተጨባጭ ሥራ አስገብሏል፡፡

አሁንም የምክክር አጀንዳ መለየት ተግባሩን አዲስ አበባ ላይ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተስፋና ምኞትን የያዘው ይህ ትልቅ ሃገራዊ ተግባር እንዲሳካ መንግስት አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ማድረጉን ይቀጥላል ብለዋል።

ከዚህ ባሻገር ነፍጥ አንግበው መንግስትን በሃይል ለመጣል ወደ ሃይል እርምጃ የሄዱ ቡድኖች ወደ ሰላማዊ መንገድ ተመልሰው ሰላማዊ የፖለቲካ መንገድን ለመከተል ቢፈልጉ ሊስተናገዱ የሚችሉበት አሰራር እንዲኖር ማድረጉ መንግስት ሌላው ለሰላም ያለውን ጽኑ አቋም ያሳየበት ነው ብለዋል፡፡

ሰላምን ከመፈለግ ባሻገር ተግባራዊ እርምጃን በመውሰድ፤ የሃገሪቱ የፖለቲካ መድረክም የግጭትና ጦርነት አዙሪት ተላቆ በሰላማዊ መንገድ ሃሳባቸውን ለማቅረብ ለሚፈልጉ አካላት ሁሉ ምቹ እንዲሆን ለማድረግ የሚያግዘውን የአዋጅ ማሻሻያ ማድረጉ በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ያልነበረ አሰራር እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

በአገራችን ያለው የምርጫ ሕግ፣ ከሕጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማዕቀፍ ውጪ ሲንቀሳቀሱ የቆዩ የፖለቲካ ቡድኖች በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ቢፈልጉና እነዚህን አካላት ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ አድርጎ ለመመዝገብ የሚያስችል ድንጋጌ በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ውስጥ ተካቶ አዋጁ እንዲሻሻል ማድርጉ ለሰላም ያለውን አቋም ያሳያል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በጋራ ያዘጋጁት የስልጣና መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል ሀዋሳ፡ ሰኔ 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ መገ...
15/06/2024

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በጋራ ያዘጋጁት የስልጣና መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል

ሀዋሳ፡ ሰኔ 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በጋራ ያዘጋጁት በመሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር እና ሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ላይ ያተኮረ ስልጠና በሃዋሳ ከተማ ተካሂዷል ፡፡

ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለተወጣጡ ሰልጣኞች በመሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር እና መርሆዎች፣በሃቅ ማጣሪያ መንገዶች እንዲሁም በሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ዙሪያ ሰልጠናው ተሰጥቷል፡፡

በስልጠና መድረኩ የተገኙት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የስትራቴጂክ ጉዳዮችና አቅም ግንባታ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ታምራት ደጀኔ እንደገለፁት ሐሰተኛ መረጃ ሐሰት የሆነና የመረጀውን ሐሰተኝነት በሚያውቅ ፤ወይም መረጀውን የሚያሰራጨው ሰው ካለበት አጠቃላይ ሁኔታ አንፃር የመረጃው እውነተኝነት ለመጣራት በቂ ጥረት ሳያደርግ የሚሰራጭ ሁከት ወይም ግጭት የማስነሳት አቅም ያለው ነው። በመሆኑም በስልጠናው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር እና መርሆዎች፣በሐቅ ማጣሪያ መንገዶች እንዲሁም በሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ላይ የባለሙያውን ግንዛቤ ማሳደግ ስለሚገባ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘላለም ገነሞ እንዳሉት የጥላቻ ንግግር በአንድ ሰው ወይም በተወሰነ ቡድን ፤ማንነት ላይ ያነጣጣረ : ሆን ተብሎ ጥላቻን ወይም ጥቃትን የሚያነሳሳ ንግግር ነው ብለዋል ፡፡ በመሆኑም ሙያውን በአግባቡና በጥንቃቄ መተግበር ይገባል ብለዋል።

በስልጠናው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቀቃም ፤ መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆዎች ሙያዊ ስነ ምግባር እና በጥላቻ ንግግር ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎበታል ፡፡ ሰልጣኞች ትክክለኛ መረጃና ሀቅን ከመዘገብ አንፃር ሀለፊነት እንዲወስዱ ከመድረኩ ጥሪ ተላልፏል ፡፡

ደሬቴድ

አምስት ዘመናዊ የአየር ትራክተሮች በይፋ ስራ ጀመሩአርባምንጭ ፣ ሰኔ 8፣ 2016 (ኤፍኤም 90.9) ኢትዮጵያ የገዛቻቸው አምስት ዘመናዊ የአየር ትራክተሮች በይፋ ስራ ጀመሩ።የአየር ትራክተሮ...
15/06/2024

አምስት ዘመናዊ የአየር ትራክተሮች በይፋ ስራ ጀመሩ

አርባምንጭ ፣ ሰኔ 8፣ 2016 (ኤፍኤም 90.9)

ኢትዮጵያ የገዛቻቸው አምስት ዘመናዊ የአየር ትራክተሮች በይፋ ስራ ጀመሩ።

የአየር ትራክተሮቹ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ስራ እንዲጀምሩ ተደርጓል።

በስራ ማስጀመሪያው መርሐ ግብሩ ላይ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴን (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

የዕጽዋት በሽታ ለመከላከል የኬሚካል ርጭት፣ የአሰሳ ስራ የሚያከናውኑ አምስቱ የአየር ትራክተሮች ለግብርናው ዘርፍ ተጨማሪ መረጃን የሚሰጡና ለተጨማሪ አገልግሎት ጥቅም ላይ እንደሚውሉም ተገልጿል፡፡

800 ሚሊየን ብር በሆነ ወጪ የተገዙት የአየር ትራክተሮቹ÷ እስከ 3 ሺህ ሊትር ኬሚካል በአንዴ የመሸከም አቅም ያላቸውና በደቂቃ እስከ 12 ሔክታር መሬት የኬሚካል ርጭት የማከናወን አቅም አላቸው ተብሏል፡፡

የበረሃ አንበጣ፣ ግሪሳ ወፍና ተዛማጅ የሰብል ተባዮችን ለመከላከል፣ የአየር ላይ አሰሳና ቁጥጥር በማድረግ የዕጽዋት በሽታን ለመከላከልም ጥቅም ላይ ይውላሉ ነው የተባለው፡፡

እንደ ፋና ዘገባ በተለይ በግብርና ምርትና ምርታማነት ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ጸረ ሰብል ተባዮችን ለመከላከል ጥቅም ላይ የሚውሉ ናቸው ተብሏል፡፡

የእሳት አደጋን ለመከላከል፣ ዘር ለመዝራት እና ለሌሎች የግብርና ስራዎች አገልግሎት እንደሚውሉም ተጠቁሟል፡፡

የአየር ትራክተሮቹ ለታለመላቸው ዓላማ በማይውሉበት አጋጣሚ በሀገር ውስጥና በውጭ በማከራየት ተጨማሪ ገቢ እንዲያመጡ የሚደረግ መሆኑም ተመላክቷል ።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ ለኢድ አል አደሃ(አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ።የመልዕክቱ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው። ለመላው የእስልምና እምነት ተከ...
15/06/2024

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ ለኢድ አል አደሃ(አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ።

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1445ኛው ኢድ አል አደሃ (ዓረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ።

ሕዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል አድሃ( አረፋ) በዓልን ሲያከብር በሃይማኖቱ አስተምህሮ መሰረት የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና ያለውን በማካፈል መሆን አለበት።

የብዝሃነት ሀገር በሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ
ህዝበ ሙስሊሙ በሃይማኖት ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው ኢድ አል አደሃ (ዓረፋ) በዓል ከሌሎች እምነት ተከታዮች ጋር አንድነቱንና ወንድማማችነቱን በሚያጠናክር መልክ በዓሉን ማሳለፍ እንዳለበት ለመግለፅ እወዳለሁ።

በመጨረሻም በዓሉ የሠላም ፣ የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆን እመኛለሁ።

አባይነህ አበራ
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

ርዕሰ-መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።የመልዕክቱ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው።ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ...
15/06/2024

ርዕሰ-መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1445ኛዉ ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል-አድኃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

በዓሉ አላህ የነብዩ ኢብራሂምን ፍቅርና እምነት ፍጹምነትን ለማስተማር ልጃቸውን ለመስዋዕትነት እንዲያቀርቡ ያዘዘበት፤ እርሳቸውም ለፈጣሪ የነበራቸው እምነትና ፍቅር ጥግ በሚያሳይ ፍጹምነት የሚወዱት ልጃቸው እስማኤልን ወደ መሰዊያው ያቀረቡበት መታሰቢያ በዓል ነው።

ፈጣሪም በልጃቸው ምትክ ለመስዋዕትነት የበግ ሙክት የተካላቸው መሆኑ የሚታወስበት ታላቅ በዓል ነው።

ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር በሃይማኖቱ አስተምህሮ መሰረት የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና ያለውን በማካፈል መሆን ይኖርበታል። እንደዚሁም ከሌሎች እምነት ተከታዮች ጋር አንድነቱንና ወንድማማችነቱን በሚያጠናክር መልክ በዓሉን ማሳለፍ ይገባል፡፡

በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር በመካሄድ ላይ በሚገኘው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ህዝበ ሙስሊሙ ንቁ ተሳትፎና ድጋፉን አጠናክሮ በመቀጠል ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል።

በዓሉ የሠላም፥ የመደጋገፍ፣ የፍቅርና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ! አደረሰን!

ጥላሁን ከበደ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ-መስተዳድር

14/06/2024

በክልሉ እየተስተዋለ ያለውን ሥራ አጥነትን ለመቀነስና ኢኮኖሚውን ለማሳደግ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጸ።

አዘጋጅ፡- ወ/ገብርኤል ላቀው

በክልሉ ለበርካታ ስራ አጦች የስራ ዕድል መፈጠሩንና አቅምን አሟጦ ከመጠቀም አንፃር ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ  የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝ ቢሮ ገለፀ ።አርባምንጭ ...
14/06/2024

በክልሉ ለበርካታ ስራ አጦች የስራ ዕድል መፈጠሩንና አቅምን አሟጦ ከመጠቀም አንፃር ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝ ቢሮ ገለፀ ።

አርባምንጭ ሰኔ 07/10/16 (ኤፍኤም 90.9)

ቢሮው የውጪ ሀገር የስራ ስምሪት እና በስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ አድርጓል ።

በአገራችን የስራ ስምሪት ጋር ተያይዞ በአሰሪውና ሰራተኛው ላይ ውስብስብ ችግሮች በተደጋጋሚ ሲፈጠሩ መስማት የተለመደ ሆኗል ።

ይህን ችግር ለመፍታት ዘላቂና አስተማማኝ ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግትን በመስጠት በዘርፉ የሚስተዋሉ ውስብስብ ችግሮችን ለመፍታት ቢሮው እየሰራ እንደሚገኝ በመድረኩ ተጠቁሟል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ ርዕሰ መስተዳድርና የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ይገዙ በክልሉ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግረው አቅምን አሟጦ ከመጠቀም አንፃር መስራት ያሻል ብለዋል ።

አቶ ተስፋዬ አክለው ምርታማነትና የስራ ባህል ላይ ትኩረት በመስጠት አቅምን መጠቀም እንደሚያስፈልግ አብራርተው አመራሩም ተግባራትን በቅንጅት መፈፀምና ማስፈፀም አለበት ሲሉ አሳስበዋል ።

ድክመቶችን በማረምና ስኬቶቻችንን በማስቀጠል በክልሉ መሰረታዊ ለውጥ ማስመዝገብ አለብን ሲሉም ገልፀው የውጪ ሀገር የስራ ስምሪት ላይም የማስተዋወቅ ስራ አለመሰራቱን ገልፀዋል ።

አቶ ኦኬ ቦሌ የቢሮው ም/ ቢሮ ኃላፊና የከተማ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍ ኃላፊ ሲሆኑ በክልሉ የሚገኙ ማዕከላትን በማጠናከር ምቹ ሁኔታዎችን ለኢንተርፕራይዞች ከመፍጠ ባሻገር የውጪ ሀገር የስራ ስምሪት ላይ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

የጎፋ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝ መምሪያ ኃላፊ አቶ መጎስ መኩሪያና የወላይታ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርኘራይዝመምሪያ ም/ ኃላፊና የከተማ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ብሩክ ባልቻ የስራ ዕድል ፈጠራን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር የማስተሳሰር ስራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል ።

ስልጠናው በውጪ ሀገር የስራ ስምሪት ፣ በስራ ገበያ መረጃ ስርዓት እና በአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ነው የተሰጠው ።

በተሰጠው ስልጠና ዙሪያም አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተሰንዝረው ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል ።

በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ከ12 ቱ የክልሉ ዞኖች የተገኙ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ

በሀገራችን የውሃ ሃብት ልማት አጠቃቀምን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየሰራ መሆኑን የፌደራል ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለፀ፡፡አርባምንጭ ሰኔ 07/10/16 (ኤፍኤም 90.9)22ኛው ዓለም አቀ...
14/06/2024

በሀገራችን የውሃ ሃብት ልማት አጠቃቀምን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየሰራ መሆኑን የፌደራል ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለፀ፡፡

አርባምንጭ ሰኔ 07/10/16 (ኤፍኤም 90.9)

22ኛው ዓለም አቀፍ ዘላቂ የውሃ ሃብት ልማት ሲምፖዚየም በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው፡፡

ዝርዝሩን ብሃርኑ ዳሾ ከአርባምንጭ ቅርንጫፍ አድርሶናል በኃይሉ ሙሉጌታ ያቀርበዋል፡፡
ሲምፖዚየሙ ከ10 የውጭ እና ሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የምርምር ተቋማት የምርምር ግኝቶች የሚቀርቡበት ነው፡፡

በፌደራል ውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ድንጋሞ እንዳሉት የውሃ ሃብት ልማትን የበለጠ ለማረጋገጥ ከዚህ ቀደም ይሰራ ከነበረው በተሻለ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ለውጦች እንዳሉት የሚጠቁሙት አምባሳደር አስፋው በግብርናው ዘርፍ ምርታማነትን በማረጋገጥ ሀገራችን ከምታደርገው ጥረት የውሃ ዘርፍ አንዱ ትሩፋት ነው ብለዋል፡፡

የውሃ ሃብትን በዘላቂነት ለመጠቀም ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም አመላክተዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የሚቀርቡት የምርምር ውጤቶች በውይይት ዳብረው ለሀገር ልማት እድገት አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ ታስቦ በመሆኑ ተናግረዋል፡፡

የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በውሃ ሃብት ልማት ረገድ ግንባር ቀደም በመሆኑ ባለሙያዎችን ከማፍራት ባለፈ በአርባ ምንጭ ከተማ እና በዙሪያ ባሉት አከባቢዎች በውሃ ዘርፍ ከአስተዳደርና ከማህበረሰብ ጋር በቅንጅት ዩኒቨርሲቲው መስራቱን ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም በዩኒቨርሲቲው ያሉ ተማሪዎች ተሰጥቶቸው አዳብረው የሚወጡበት ምሁራን ተማራማሪው የወቅቱን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ለሀገር ልማት እድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ፍሰት አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ጥናት ያቀረቡት ረዳት ፕሮፔሰር ተስፋለም አብርሃም ሲምፖዚየሙ ለቀጣይ የምርመር ስራዎች የሚያነሳሳ ነው ብለዋል፡፡

ዘጋቢ ፡ ብርሀኑ ዳሾ

በምክትል ማዕረግ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬዘር ኮርባይዶ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና ረዳት የመንግስት ተጠሪ ሹመት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።አር...
14/06/2024

በምክትል ማዕረግ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬዘር ኮርባይዶ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የዞን ዋና የመንግስት ተጠሪና ረዳት የመንግስት ተጠሪ ሹመት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።
አርባ ምንጭ ግንቦት 7_2016 ዓ/ም( ኤፍ ኤም 90.9 ሬድዮ)

በዋና አስተዳደሩ ለምክር ቤቱ የቀረቡ ዕጩዎች

1. አቶ ሐመር ሐንሻ ….የኮንሶ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ፣
2. ወ/ሮ የውብዳር ኦላታ…ፓለቲካና ሪዕዮት አለም ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ ዕጩዎች አድርጎ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ከፍተኛ የሥራ ልምድ ያላቸውና በተለያዩ መንግስታዊ የሥራ ኃላፊነቶች ላይ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ዞንና ፌዴራል ተቋማት የሰሩ በሳል የፓርቲው አባላት በመሆናቸው የተከበረው ምክር ቤት አስተያየት ሰጥቶባቸዋል።

የቀረቡት ዕጩዎቹ ህዝቡን በታማኝነት፣ በቅንነትና በበሳል የፖለቲካ መሪነት ህዝቡን እንዲያገለግሉ መክረው ምክር ቤቱ ሹመቱን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።

መረጃው
የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉ/መምሪያ
ሰኔ 07/2016 ዓ.ም

ሊዮኔል ሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን በአሜሪካው ክለብ ማጠናቀቅ እንደሚፈልግ አስታወቀአርባምንጭ ፣ ሰኔ 6፣ 2016 (ኤፍኤም 90.9) አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን በአሜሪካ...
14/06/2024

ሊዮኔል ሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን በአሜሪካው ክለብ ማጠናቀቅ እንደሚፈልግ አስታወቀ

አርባምንጭ ፣ ሰኔ 6፣ 2016 (ኤፍኤም 90.9)

አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ የእግር ኳስ ህይወቱን በአሜሪካው ኢንተር ማያሚ ክለብ ማጠናቀቀቅ እንደሚፈልግ አስታወቀ፡፡

የ8 ጊዜ ባለንዶር አሸናፊው ሜሲ የፈረንሳዩን ክለብ ፓሪስ ሴንት ጀርሜን በመልቀቅ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ወደ አሜሪካ ማቅናቱ ይታወሳል፡፡

“ኢንተር ማያሚ የመጨረሻው ክለቤ ይሆናል ብዬ አስባለሁ” ሲል የ36 ዓመቱ ሜሲ ለኢ.ኤስ.ፒ.ኤን ተናግሯል፡፡

“ከእግር ኳስ ለመገለል ግን ዝግጁ አይደለሁም” ሲልም አክሏል፡፡

ሜሲ በዚህ ዓመት ለክለቡ ባደረጋቸው 12 ጨዋታዎች 12 ጎሎችን ያስቆጠረ ሲሆን ፥ 13 ለግብ የሚሆነ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

ከሀገሩ ብሔራዊ ቡድን ጋር በፈረንጆቹ 2022 የዓለም ዋንጫን ያነሳው ሚሲ ፥ በኢንተር ማያሚ ክለብ እስከ 2025 ድረስ የሚያቆይ ኮንትራት ያለው ሲሆን ፤ ውሉን ለተጨማሪ ጊዜ የማረዘም እድልም አለው፡፡

ሊዮኔል ሜሲ በባርሴሎና ቆይታው 10 የላሊጋ ድሎችን ጨምሮ 4 ጊዜ የሻምፒንስ ሊግ ዋንጫን ማንሳቱ ይታወሳል፡፡

የክልሉ መንግሥት ኢንዱስትሪ ልማት ለማስፋፋት እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሠራ መሆኑ ተገለፀ።አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም...
13/06/2024

የክልሉ መንግሥት ኢንዱስትሪ ልማት ለማስፋፋት እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሠራ መሆኑ ተገለፀ።

አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የተመራ ሉዑክ የወራቤ ኢንዱስትሪ ማዕከል የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝ አካህዷል።

በ400 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የወራቤ ኢንዱስትሪ ማዕከል 127 ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ተብራርቷል።

ማዕከሉ 11 የተለያዩ ፋብሪካዎችን በውስጡ የያዘ ሲሆን ለ23 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሐላፊ ዶ/ር እንዳልካቸው ጌታቸው የክልሉ መንግሥት ኢንዱስትሪ ልማት ለማስፋፋት እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሠራ ነው ብለዋል።

ቀድሞ ወደ ሥራ ከገባው የወራቤ ኢንዳስትሪ ልማት መንደር የቀሰሙት ልምድ የሚበረታታ መሆኑን ሀላፊው አብራርተዋል።

አቶ ጥላሁን ብርሐኑ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ በበኩላቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ያሉ ፀጋዎችን በመጠቀም የግሉን ባለሀብት በማስተባበር በቀጣይ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለመገንባት መታቀዱን ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተስፋዬ ይገዙን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ፡-ወ/ገብርኤል ላቀው

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ከክልሉ ልማት ፓርኮች ጋር በመሆን የወራቤ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝ አካህዷል።አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ...
13/06/2024

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ከክልሉ ልማት ፓርኮች ጋር በመሆን የወራቤ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝ አካህዷል።

አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) ኢትዮጵያ ታምርት ትሸምት እንቅስቃሴን ለመደገፍ ኢንዱስትሪ ልማት ማጠናከር ለአገር ኢኮኖሚ ያለው ፋይዳው የጎላ ነውም ተብሏል።

በ400 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የወራቤ ኢንዱስትሪ ማዕከል 127 ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ተብራርቷል።

የመሬት አቅርቦት እና መሠረተ ልማት የማሟላት የኢንዱስትሪ ማዕከል መገንባት ለአካባቢው ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ይገኛል።

ማዕከሉ ተገንብቶ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ 6 ቢሊዮን ብር የሚገመት ካፒታል ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

የልማት አማራጮችንና እምቅ አቅም መነሻ በማድረግ ከየግል ባለሐብቶችና ከወራቤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት እየተሠራ ስለመሆኑ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መሐመድ አብራርተዋል።

በማዕከሉ በግብርና እና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛል።

በጉብኝቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተስፋዬ ይገዙን ጨምሮ የተለያዩ የቢሮ ሐላፊዎች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ፡- ወ/ገብርኤል ላቀው

"ግብርን ከመሰብሰና ማስተዳደር ጋር ያሉ ጉድለቶች ሊፈቱ ባለመቻላቸው ለዘርፉ እንቅፋት ፈጥሯል" ፡- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደአርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም ...
13/06/2024

"ግብርን ከመሰብሰና ማስተዳደር ጋር ያሉ ጉድለቶች ሊፈቱ ባለመቻላቸው ለዘርፉ እንቅፋት ፈጥሯል" ፡- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን አሟጦ በመሰብሰብና በመጠቀም አስተማማኝ የፋይናንስ አቅም መፍጠር የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ ተካሂዷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የገቢ አሰባሰብ ሥራዎች ልዩ የንቅናቄ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እንደተናገሩት በክልሉ ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል ይኖር ዘንድ ገቢን አሟጦ መጠቀም ያስፈልጋል።

በክልሉ የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱ ያለበትን ደረጃ ከፍ ለማደረግ የውስጥ አቅምን መጠቀም ያስፈልጋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ክልሉ ካለው እምቅ ሀብት አኳያ መሰብሰብ ያለበት የገቢ መጠን ዝቅተኛ መሆኑ ልዩ ትኩረት የሚሻው ነውም ብለዋል።

ክልሉን በአዲስ መልክ ስናደራጅ አቅማችን ህዝባችን ነበረ ያሉት አቶ ጥላሁን ጤናማና ፍታሀዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን መዘርጋት ህዝቡ የሚጠብቅብንን የልማትና የመልካም አስተዳደር መመለስ እንድንችል አቅም ይፈጥራልም ሲሉ ተናግረዋል።

ግብርን ከመሰብሰና ማስተዳደር ጋር ያሉ ጉድለቶች ሊፈቱ ባለመቻላቸው ለዘርፉ እንቅፋት እንደፈጠረም ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አስታውሰው በፋይናንስ ስርዓቱ ገቢ በሌለበት ወጪን ማብዛት ክልሉን ለአላስፈላጊ ብክነት መዳረግ ነውና ሊታረም ይገባም ብለዋል።

አቶ ጥላሁን አያይዘውም በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ያስፈልጋልም ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ በበኩላቸው የክልሉን የፋይናንስ ስርዓት የሚያዛቡ አሠራር ሊታረሙ ይገባልም ብለዋል።

በክልሉ በ2016 በጀት አመት በፋይናንስ ስርዓት ውስጥ የወጪ ቅነሳ መመሪያን ተከትሎ አለ መፈፀምና በየጊዜው የጥሬ ገንዘብ ጉድለት መከሰት እንዲሁም ያልታቀዱ ግዥዎች በከፍተኛ ሁኔታ መኖራቸውን አንስተዋል።

አቶ ተፈሪ አያይዘውም የተሰበሰበ ሂሳብ ክምችት ከፍተኛ መሆን ለዚህም የማዳበሪያ እዳ አለመመለስ ምክንያት መሆኑ ችግሩን እንዳባባሰው ጠቅሰዋል።

ዘጋቢ፡- በኃይሉ ሙሉጌታ

በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን አሟጦ በመሰብሰብና  በመጠቀም አስተማማኝ የፋይናንስ አቅም መፍጠር የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀመረ።አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (...
13/06/2024

በክልሉ የሚገኙ ፀጋዎችን አሟጦ በመሰብሰብና በመጠቀም አስተማማኝ የፋይናንስ አቅም መፍጠር የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ መካሄድ ጀመረ።

አርባምንጭ፡ ሰኔ 6/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የገቢ አሰባሰብ ሥራዎች ልዩ የንቅናቄ መድረክ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደን ጨምሮ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።

ዘጋቢ፡- በኃይሉ ሙሉጌታ

ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም ችግር በሠላም መጠናቀቁን የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ አሰታወቀ።አርባምንጭ ሰኔ 05/10/16 (ኤፍኤም 90.9)...
12/06/2024

ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ያለምንም ችግር በሠላም መጠናቀቁን የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ አሰታወቀ።

አርባምንጭ ሰኔ 05/10/16 (ኤፍኤም 90.9)

የጋሞ ዞን ትምህርት መመሪያ ኃላፊ አቶ አብረሃም አምሳሉ የፈተናው መጠናቀቁን ተከተሎ በሰጡት ማብራሪያ የዘንድሮው ሀገረ አቀፍ 8ኛ ክፍል መለቀቅያ ፈተና ከወትሮው በተለዬ መልክ ያለምንም ችግር ፊፁም ሠላማዊ መንገድ በዞኑ በ 136 ጣብያዎች መጠናቀቁን አስታውቋል ።

ለፈተናው ከተመሰገቡት ተማሪዎች 98 በመቶው ፈተናውን መውሰዳቸውን እና ቀሪዎቹ በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ምክንያት ለፈተና ያለመቀመጣቸውን ጠቁመው ተማሪዎችም በስነምግባር የተላበሱ እንደነበሩ ኃላፊው አሰረድተዋል ።

ለፈተናው ስኬት በየደረጃው ያሉ ድርሻቸውን በአግባቡ የተወጡ አካላትን አመስግነው ፈተናው ከነገ ጀምሮ ወደ ክልል ማዕከል መጓጓዝ እንደምጀምር አቶ አብርሃም አመላክቷል ።

በተመሳሳይም መልኩ የአርባምንጭ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጋለ ቦቾ በበኩላቸው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመሰራቱ ፈተናው ያለምንም ችግር እና የድስፕሊን ጥሰት በሁሉም ጋር ሳይከሰት መጠናቀቁን ገለፀው በሂደቱ የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል ።

ወ/ሮ ፀሀይነሽ ንጉሴ በከተማው የጫሞ ክላስተር ሱፐረባይዘር ሲሆኑ ከዚህ በፊት ያልተረጋገጠ መልስ ይዞ መግባትና የስነ-ምግባር ከፍተቶች በተማሪዎች ዘንድ ይስተዋሉ አንደነበረ ተናግረው የዘንድሮው የተሻለ መሆኑን ተናግረዋል ።

ከፈታኝ መምህራን መካከል መምህር ጀማኔ ወ/ጊዩረጊስ አንዳሉት ተማሪዎች ፈተናውን ከኩረጃ በፀዳ መልክ በራሳቸው እንድሰሩ መደረጉን ጠቅሰዋል ።

ከተፈታኝ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ምህረት በቀል አኛ ተማሪ አብነዜር ዳይኔ ጥሩ ቅድሜ ዝግጅት በማድረግረጋቸው ፈታናውን በአግባቡ መስራታቸውን አመላክተዋል ።

ዘጋቢ ፡ አለሚቱ አረጋ

አረንጓዴ አሻራችንን እውን በማድረግና አካባቢን በመጠበቅ በኢኮ -ቱሪዝምና በካርቦን ሽያጭ ተጠቃሚ ለመሆን ለደኑ ዘርፍ ልዩ ትኩረት እንደሚያሻ ተገለፀ ።"መሬትን ማገገም  ፣ በረሀማነትንና ድ...
12/06/2024

አረንጓዴ አሻራችንን እውን በማድረግና አካባቢን በመጠበቅ በኢኮ -ቱሪዝምና በካርቦን ሽያጭ ተጠቃሚ ለመሆን ለደኑ ዘርፍ ልዩ ትኩረት እንደሚያሻ ተገለፀ ።

"መሬትን ማገገም ፣ በረሀማነትንና ድርቅን ለመቋቋም " በሚል መሪ ቃል የዓለም የአከባቢ ቀን በአለም ለ51፣ በሀገራችን ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ በአርባምንጭ ተከብሯል ።

አርባምንጭ ሰኔ 05/10/16 (ኤፍኤም 90.9)

የጋሞ ዞን ደንና አከባቢ ጥበቃ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጋሻሁን ሞላ ችግኞችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ በማድረግ እና በመንከባከብ የአየር ንብረት ለውጥ እያሳደረ የሚገኘውን ተፅዕኖ መመከት እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

በጋሞ ዞን ለተከላ ከተዘጋጁ 63 ሚሊዮን ችግኞች መካከል ከ38 ሚሊዮን በላይ ችግኞች በ13 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ መትከል መቻሉንም ገልፀዋል አቶ ጋሻሁን ።

የጋሞ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ መኮንን ሞገስ የአየር ንብረት ለውጥ ህልውናችንን እየተፈታተነ ይገኛል ብለው መላው ህብረተሰብ ችግኝ ተካላው ላይ መሳተፍ ለችግሩ እልባት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የጋሞ ዞን ሁለት ብሄራዊ ፓርኮች እና በርካታ ጥብቅ ደኖች መገኛ መሆኑን ያወሱት አቶ መኮንን እነዚህን ገፀ - በረከቶቻችንንም በመጠበቅ የቱሪዝሙን ዘርፍ ማሳደግ ያሻል ብለዋል ።

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ገዙ ተራራዎችን ማልማት የውሀ መጠንን ከመጨመር ባሻገር አከባቢን ከደለል እንደሚጠብቅ ጠቁመው የጋንታ ተራራን ማልማት ለአርባምንጭ ከተማና ለሁለቱ ሀይቆች ህልውና አስፈላጊ እንደሆነ ገልፀዋል ።

መርሀ ግብሩ ችግኝ በመትከል ብቻ የሚወሰን አለመሆኑንና ቀድሞ የተተከሉትን የመንከባከብ መሆኑን ያነጋገርናቸው አካላት ነግረውናል ።

"መሬትን ማገገም ፣ በረሀማነትንና ድርቅን ለመቋቋም " በሚል መሪ ቃል የዓለም የአከባቢ ቀን በአለም ለ51፣ በሀገራችን ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ በአርባምንጭ ከተማ በተከናወነው የችግኝ ተከላ የጋሞ ዞን ፣ የአርባ ምንጭ ከተማእና ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ጨምሮ የአከባቢው ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

ዘጋቢ ፡ ተመኙህ ገረሱ

የ2016 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ቀን መርሃግብር በሠላም መጠናቀቁን የኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታውቋል።የኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኩሴ...
12/06/2024

የ2016 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ቀን መርሃግብር በሠላም መጠናቀቁን የኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታውቋል።

የኮንሶ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኩሴ ጭሎ እንደገለፁት በዞኑ በ27 የፈተና ጣቢያዎች ሲሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የ8ኛ ክፍል ፈተና ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ገልጸዋል።

መፈተኛ ጣቢያዎቹ ካራት ከተማ፣ ካራት ዙሪያ፣ ከና፣ ሰገን እና ኮልሜ ወረዳዎች ላይ ውሎውን በሠላም አጠናቀዋል ብለዋል።

አቶ ኩሴ አክለውም ተፈታኝ ተማሪዎች በዛሬው በመጀመሪያ ቀን ሀገር አቀፍ የፈተና መርሃግብር መሠረት አማርኛ፣ ኢንግሊዘኛ፣ ሂሳብ እና ስነዜጋ የትምህርት ዓይነቶች መፈተናቸውን አስታውቀዋል።

የፈተና ሂደቱ ፍፁም ሠላማዊና ከኩረጃ በፀዳ መንገድ መጠናቀቁን አቶ ኩሴ አስረድተዋል።

መረጃው
የኮንሶ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉ/መምሪያ
ሰኔ 04/2016 ዓ/ም

11/06/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Emebet Girma, Birkneh Endashaw, ዝም ይሻላል, Tilahun Yohannes, Rahel Kidane, Abiyot Doka, Tagesse Chotira Zewude, Mesay Belachew, Abel Alemayehu, Alemu Mardofe, Akililu Argaw, Firomsaa Asaffaa, Abebaw Azagn, Aman Alex, Zerihun Worku, ተካ የልጁ ልጅ, Tadesse Yismaw Getachew, Gamo Arbamnch, Amaniye Ye Dansa Liji, ህልም አለኝ, Wonde Ye Wondu Lij, Sdfsgh Chelrf, ለቀንም ቀን አለ

11/06/2024

ራስን የሚገዛ ፣በዕውቀት ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ለመፈጠር በትምህርት ሴክተር የተጠናከረ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ ።

አዘጋጅ፡- አለሚቱ አርጋ

የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንትን እና ሌሎች ዘጠኝ ሰዎችን ጭኖ በበረራ ላይ የነበረው አውሮፕላን መከስከሱ ተረጋገጠ፡፡አርባምንጭ፡ ሰኔ 4/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9)  የማላዊ ...
11/06/2024

የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንትን እና ሌሎች ዘጠኝ ሰዎችን ጭኖ በበረራ ላይ የነበረው አውሮፕላን መከስከሱ ተረጋገጠ፡፡

አርባምንጭ፡ ሰኔ 4/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንትን እና ሌሎች ዘጠኝ ሰዎችን ጭኖ በረራ ላይ የነበረው አውሮፕላን ቺካንጋዋ በመባል የሚጠራው ተራራማ ስፍራ ላይ መከስከሱን የሀገሪቱ መንግሥት አሳውቋል።

ዴይሊ ሚረር እንደዘገበው በአደጋው ምክንያት ምክትል ፕሬዚዳንት ሳኦሎ ቺሊማ እና ባለቤታቸውን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉ ታውቋል።

ኢትዮጵያውን ስደተኞችን የያዘች ጀልባ ተገልብጣ 38 ሞቱ -100 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀምአብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ከየመን የባሕር ዳርቻ አቅ...
11/06/2024

ኢትዮጵያውን ስደተኞችን የያዘች ጀልባ ተገልብጣ
38 ሞቱ -100 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም

አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ከየመን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ ተገልብጣ ቢያንስ 38 ሰዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናት አስታወቁ።

ከአደጋው የተረፉ ሰዎች ለነፍስ አድን ሠራተኞች እንደተናገሩት ጀልባዋ 250 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍራ የነበረ ሲሆን፣ ለመገልበጥ የበቃችውም በካበድ ነፋስ ምክንያት ነው ተብሏል።

መሞታቸው ከታወቀው 38 ሰዎች ውጪ ሌሎች 100 ሰዎች የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን፣ እነሱን ለማግኘት ፍለጋ እየተደረገ ነው።

ከየመን ዋና ከተማ አደን በስተምሥራቅ የምትገኘው የሩደም አካባቢ ባለሥልጣናት እንዳሉት አደጋው በደረሰባት ጀልባ ላይ ተሳፈረው ከነበሩት አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሲሆኑ፣ የመንን ወደ ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለመሸጋገሪያነት ይጠቀሙባታል።

የሩደም አካባቢ አስተዳዳሪ የሆኑት ሃዲ አል-ኹርማ ለሮይተርስ ዜና ወኪል እንደተናገሩት በጀልባዋ ላይ የመስመጥ አደጋው የደረሰው ወደ ባሕር ዳርቻው ከመቃረቧ በፊት ነው።

በስፍራው የነበሩ ሰዎች 250 የሚሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ አደጋው የደረሰባት ጀልባ ላይ የነበሩ በርካታ ሰዎችን ሕይወት ማትረፋቸው ተነግሯል።

“ዓሳ አስጋሪዎች እና ነዋሪዎች አብረዋቸው በጀልባዋ ላይ የነበሩ 100 የሚሆኑት ሰዎች የደረሱበት አለመታወቁን የተናገሩ 78 ሰዎችን በሕይወት አድነዋል” ሲሉ ባለሥልጣኑ ተናግረዋል።

ጨምረውም በአደጋው ምክንያት የጠፉትን ሰዎች ለማግኘት የሚደረገው ጥረት የቀጠለ ሲሆን፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ድርጅትም ስለደረሰው አደጋ እንዲያውቅ መደረጉ ተገልጿል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሪፖርት እንደሚያመለክተው ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት ብቻ 97,000 ስደተኞች በጦርነት ውስጥ ወደ ምትገኘው የመን ገብተዋል።

በየመን ያለው ጦርነት እና በቅርቡ የየመን ሁቲ ታጣቂዎች በቀይ ባሕር ላይ ጥቃት እየሰነዘሩ ቢሆንም ስደተኞች ወደ አገሪቱ በአደጋኛ የባሕር ጉዞ መግባታቸውን ቀጥለዋል።

ከጂቡቲ በመነሳት በሕገወጥ መንገድ በቀይ ባሕር በኩል ወደ ሳዑዲ አረቢያ እና ሌሎች የባሕረ ሰላጤው አገራት በሚጓዙ ስደተኞች ላይ ተመሳሳይ አደጋ በተደጋጋሚ ሲደርስ ቆይቷል።

በዚህ አደገኛ መንገድ የሚጓዙት አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ ለሕገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ከፍተኛ ገንዘብ ከመክፈላቸው በተጨማሪ እንግልት እና በደል እንደሚደርስባቸው ይናገራሉ።

ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ ብቻ በተከታታይ በደረሱ ሁለት አደጋዎች 60 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ባሕር ውስጥ ሰምጠው ለሞት መዳረጋቸው መዘገቡ ይታወሳል። BBC

ራስን የሚገዛ ፣በዕውቀት ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ለመፈጠር በትምህርት ሴክተር የተጠናከረ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ ።አርባምንጭ፡ ሰኔ 4/201...
11/06/2024

ራስን የሚገዛ ፣በዕውቀት ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ለመፈጠር በትምህርት ሴክተር የተጠናከረ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ ።

አርባምንጭ፡ ሰኔ 4/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) ቢሮው የ 8ተኛ ክፍል ሀገረ አቀፍ ፈተና በጋሞ ዞን በአርባምንጭ ከተማ በይፋ አስጀምሯለ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማር ፈተናዎች ምዘና ክፍል ኃላፊ አቶ ኢሳያስ እንድሪያስ ፈተናውን ባሰጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት ራስን የሚገዛ ፣ በዕውቀት ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ለመፈጠር በትምህርት ሴክተር የተጠናከረ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገለፀዋል ።

የ8ተኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና በክልሉ በሁሉም ዞኖች በ2ሽህ 872 መፈተኛ ጣቢያዎች ለ134 ሺህ 281 ተማሪዎች ፈተናው በሠላማዊ መንገድ መሰጠት
መጀመሩን አስታውቋል ።

ፈተናው ሰላማዊና ከኩረጃ በፀዳ መልክ እንድሆን በቅ ዝግጅት መደረጉን የገለፁት ኃላፊው ኩረጃ አስፀያፊ ተግባር በመሆኑ ተማሪዎች በዕውቀት ተወዳዳሪ ለመሆን ፈተናውን በተረጋጋ መንፈስ መሰራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል ።

የዘንድሮው ፈተና ከእጅ ንክኪ ነፃ በሆነ መልክ በኮምፒውተር ስለምታረም ተማሪዎች የፈተና መስጫ ወረቀቱ ላይ በአግባቡ እንድቀቡ አቶ ኢሳያስ አስገንዝበዋል ።

የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብረሃም አምሳሉ በበኩላቸው ፈተናው በዞኑ በ136 ጣቢያዎች 32 ሺህ 633 ተማሪዎች ፤ በ812ፈታኝ መምህራን በ174 ሱፐርባይዘሮች ።፤ በ 2ዐ መዋቅሮች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሠላማዊ መንገድ እየተሰጠ ይገናኛል ።

ፈተናው ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ከ ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት አየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ አብረሃም ከኩረጃ የፀዳ እንድሆንም በአንድ ክፍል እስከ 30 ተማሪዎች እንዲሁም በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንደሚቀመጥ መደረጉን ጠቁመው ተማሪዎች ፈተናውን ያለምንም ስጋት በተረጋጋ ሁኔታ እንድሰሩ መልዕክታቸውን አስተላልፏል ።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች ጸ/ቤት ኃላፊ አቶ ቦጋሌ ቦቾ በከተማው በ 7 የፈተና ጣቢያዎች 3 ሺህ 900 ተማሪዎች በቂ ማብራሪያ የተሰጣቸው መሆኑን ተናግረው ሀሰተነኛ እና በአሉባልታ ተማሪዎች እንዳይረበሹ አሳስበዋል ።

የ8ተኛ ክፍል ሀገረ አቀፍ ፈተና ያለምንም ፀጥታ ችግር በሠላም ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ አባላትን በዙሪያና በፈተና ጣብያዎች በማሰማራት ወደ ሥራ መግባቱን የአርባምንጭ ከተማ አሰተዳደር ፖሊስ አዛዥ ምክትል እንስፌክተረ ዳፋሮ ቶማስ ተናግረዋል ።
ፈተናው ከሰኔ እስከ 5 ድረስ እንደሚሰጥ መረጃው አመላክቷል ።

ዘጋቢ ፡ አለሚቱ አረጋ

የአርባምንጭ  ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች  በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን ትምህርት  በተግባር ለመደገፍ እየተደረገ  ባለው ስራ በማህበረሰብ አቀፍ ፕሮግራም ተማሪዎች የወባ በ...
10/06/2024

የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን ትምህርት በተግባር ለመደገፍ እየተደረገ ባለው ስራ በማህበረሰብ አቀፍ ፕሮግራም ተማሪዎች የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ስራ ላይ መሆናቸው ተገለፀ።


አርባምንጭ፡ ሰኔ 3/2016 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ኤፍ.ኤም 90.9) የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የማህበረሰብ አቀፍ ፕሮግራም አስተባባሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር ደስታ ሃፍቱ ኮሌጁ በመማር ማስተማር ስራ ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየሰራ ባለው ተግባር ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን ትምህርት በተግባር እንዲደግፉ እየተሰራ ይገኛሉ ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ስራው ባሻገር ከ50 በላይ በሆኑ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ላይ ጥናትና ምርምር እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

ወባ ተላላፊ ከሆኑ በሽታዎች መካከል አንዱ ሲሆን ካልተጠነቀቁ አካላዊ ፣ ስነ ልቦናዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ባሻገር ቶሎ ካልታከሙ ለሞት የሚዳርግ አንደሆነም ገልፀዋል።

የዩኒቨርስቲው የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህር ኤርሚያስ ወርቁ በወባ ትንኝ አማካኝነት ከበሽተኛው ሰው ወደ ጤነኛ ሰው የሚተላለፍ ሲሆን የበሽታውን ምልክቶች ወደ ጤና ድርጀት ሄዶ ካልታከሙ ለዘላቂ የጤና ችግር ይዳረጋል ብለዋል።

የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚድዋይፈሪ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ቤተልሔም ሲሳይና ተማሪ ኤፍሬም አበራ በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን እውቀት 400 ቤቶች ላይ ባደረጉት ልየታ ህብረተሰቡ ያቆሩ ውሃዎችን ከማፋሰስና ማዳፈን ላይ ከሚታየው ውስንነት ባሻገር አጎበርን ላልተፈለገ ዓላማ በማዋላቸው የወባ በሽታ እየተስፋፉ መሆኑን ገልጸዋል ።

ዘጋቢ፡- ማስረሻ ዘውዴ

Address

ARBAMINCH
Arba Mintch
0979711926

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ArbaMinch FM 90.9 / አርባምንጭ ኤፍ ኤም 90.9 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share