ኢትዮ አዲስ ቲዩብ የአዕምሮ መረጃ ማዕከል

ኢትዮ አዲስ ቲዩብ  የአዕምሮ መረጃ ማዕከል Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ኢትዮ አዲስ ቲዩብ የአዕምሮ መረጃ ማዕከል, News & Media Website, Addis Ababa.

"ዳታን" የያሬድ ነጉ የሙዚቃ አልበም ሊለቀቅ ነውኪነት ኢንተርቴመንት የድምጻዊ ያሬድ ነጉ "ዳታን" የተሰኘው የመጀመሪያ አልበም ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ይህ "ዳታን" የተሰኘው አ...
14/01/2025

"ዳታን" የያሬድ ነጉ የሙዚቃ አልበም ሊለቀቅ ነው

ኪነት ኢንተርቴመንት የድምጻዊ ያሬድ ነጉ "ዳታን" የተሰኘው የመጀመሪያ አልበም ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ይህ "ዳታን" የተሰኘው አልበም በግጥም ወንደሰን ይሁብ፣ ፍሬዘር አበበወርቅ፣እዩቤል ብርሃኑ፣ ሃ/ማርያም መንግስቴ ፣ ጃሉድ አወል፣ሄኖክ ክብሩ(ጎፈር)መልእቲ ኪሮስ እና ፈለቀ ማሩ በዜማ ፋኑ ጊዳቦ ፣ ፀጋው ተክሉ (ቹቹ) ፣ኤሊያስ ግዛቸው ፣ጃሉድ አወል፣ሙሉአለም ታከለ እና ዩሃና ሲሆን በመዚቃ ቅንብር ሚካኤል ኃይሉ (ሚኪ ጃኖ) ፣ስማገኘው ሳሙኤል፣ፋኑ ጊዳቦ፣ ጊልዶ ካሣ፣ሱራፌል የሺጥላ እና ሃይፐር በሚክሲንግ ይትባረክ ክፍሌ ማስተሪንግ ክሩቤል ተስፋዬ ተሳትፈውበታል፡፡

ተወዳጁ ድምጻዊ ያሬድ ነጉ የመርካቶ አራዳ የመጀመያው ስራው ሲሆን እንዲሁም በርከት ያሉ ነጠላ ዜማዎችን በመስራት እና በአገራችን ካሉት ወጣት ድምጻውያን አጠቃላይ ዕይታው ከ160,000,000 ሚሊየኖች ዕይታ በላይ በመታየት ግንባር ቀደም እና ተወዳጅነትን በማትረፍ ሀገሩን በመወከል ኮክ ስቱዲዮ በመጋበዝ ከኢተርናሽናል አርቲስቶች ጋር ሙዚቃን መጫወት ችሏል፡፡ ከነዚህም መካከል:- ከዳይመንድ፣ ያሚ አላዲ፣ሪቫኒ እና ሃርመናይዝ ጋር ሙዚቃን በብቃት መጨወት ችሏል፡፡
ድምጻዊ ያሬድ ነጉ ከሀገራች በርካታ ወጣት ድምጻዊያን ጋር ሙዚቃን አብሮ በመስራት በህዝብ ዘንድ እውቅናን ተወዳጅነትነ አግኝቷል፡፡
ዳታን አልበም 11 track ያሉት ሲሆን አርቲስቱ የአለቀ አልበም አፍርሶ እንደ አዲስ የሰራው አልበም ነው ፡፡ "ዳታን” አልበምን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 3 ዓመት እና ከፍተኛ በጅት ፈጅቷል።አልበሙ ላይ ሦስት የሙዚቃ ቪዲዮዎችን ተሰርቶ የተጠናቀቁ ሲሆን ይህ አልበም ሙሉ በሙሉ ወጪ በድምጻዊ ያሬድ ነጉ ፕሮዲዩስ ተደርጓል፡፡
ይህ "ዳታን” አልበም ብዙ የተደከመበት እና የተለፋበት አልበም_ስለ ፍቅር፣ስለመለያየት እና ስለሀገር የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ይዳስሳል።
"ዳታን" የተሰኘው አልበም የፊታችን አርብ ጥር 09 በያሬድ ነጉ ዩቲዩብ ቻናል እና በሁሉም አለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች በዞጃክ ወርልድ አማካኝነት ይገኛል፡፡

14/01/2025

በቤይሩት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 164 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
_
( ጥር 05 ቀን 2017 ዓ.ም.አዲስ አበባ):-በሊባኖስ በአስቸጋሪ ሁኔታ የነበሩ እና ለአደጋ የተጋለጡ ኢትዮጵያውያ ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል ።በዛሬው ዕለት ወደ ሃገራቸው የተመለሱት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 164 ነው።

13/01/2025

አሜሪካ መግታት በተሳናት የሎስ አንጀለሱ የሰደድ እሳት የሟቾች ቁጥር 24 ደረሰ። በአካባቢው ተጠናክሮ የቀጠለው ከባድ ንፋስ የሰደድ እሳቱን ሊያጠናክረው እንደሚችል መስጋታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
የሰደድ እሳቱ ባደረሰው አደጋ እስካሁን ከሞቱት በተጨማሪ በአስራዎቹ የሚቆጠሩ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ። በአደጋው እስከ 180 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብት እና ንብረት ወደ አመድነት ተቀይሯል ነው የተባለው።
በአሜሪካ ሁለተኛ ትልቋን ከተማ ለአንድ ሳምንት ያህል እያቃጠለ የሚገኘው እሳቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች እና ህንጻዎችን ወደ አመድነት ቀይረዋል፤ ከ100 ሺ በላይ ሰዎችን ደግሞ ከመኖሪያቸው አፈናቅሏል ።
አሜሪካን እያሳሳበ የመጣው እስካሁን የደረሰው ውድመት እና ጥፋት ሳይሆን ከዚህ በኋላ ከባዱ ነፋስ እሳቱን አስፋፍቶ ከዚህም የከፋ ውድመት እንዳያደርስ ነው።
የሀገሪቱ ብሄራዊ ሜትሮሎጂ ትንበያ እንዳመለከተው ከነገ ማክሰኞ ጥር 6 ጀምሮ በሰዓት 110 ኪ/ሜ የሚገሰግስ ከባድ ንፋስ ሊከሰት ይችላል።

12/01/2025

የዓለም ቱጃሮችን ያስነባው ሰደድ እሳት !!!

ከባለፈው ማክሰኞ ጀምሮ በካሊፎርኒያ ግዛት ሎስአንጀለስ የተከሰተው ሰደድ እሳት በፍጥት በመዛመት ከፍተኛ ውድመት እና ጉዳት እያስከተለ ቀጥሏል፡፡

እስካሁን 10 ሺህ ውድና ቄንጠኛ ቪላዎች አመድ ሆኑ። ዕውቅ እና ቱጃር የሆሊውድ ተዋንያን ውድ ንብረቶች እንዳልነበሩ ሆኑ። ከአንድ ታዳጊ ሀገር ዓመታዊ በጀት በላይ የሆነ 150 ቢሊዮን ዶላር ሀብት ተቃጥሎ አመድ ተዛቀ።

እሳቱ አሁንም እያወደመ ቀጠለ። በመቶዎች የሚቆጠሩ ግዙፍ ህንፃዎች የእሳት እራት ሆኑ። በሺህ የሚቆጠሩ የእሳት አደጋ ሰራተኞች ዕምቢ ብሏቸው 900 ዕስረኞች ከማረሚያ ወጥተው በእሳት ማጥፋት ስራ ቢሰማሩም ሰደድ እሳቱ ከውቅያኖስ በሚመጣ አደገኛ ንፋስ ሃይል እያገኘ በሁለት አቅጣጫ በፍጥነት እየተዛመተ ነው። በወርቅ የተንቆጠቆጡ የሚመስሉ ቤቶች ጋዩ።

የማያልቅ የሚመስለውን ውድ ሀብታቸውን ያጡት ሀብታም የሆሊውድ አክተሮች ዕምባ አውጥተው አለቀሱ። ታዋቂው ሀብታሙ የሆሊውድ አክተር ጀምስ ውድ ሀብቱ ተቃጥሎበት ከቢቢሲ ጋር በነበረው ቃለመጠይቅ በዕምባ ታጥቦ ዕምባውን መቆጣጠር ሲያቅተው ቃለመጠይቁን አቋረጠ። ልቤ ተሰበረ አለ።

በዓለም ከእግዚአብሔር በቀር ምንም እንደማያስመካ በግልጽ ለሁሉም ታይቷል ። የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ የሚለው የእግዚአብሔር ቃል ያልገባቸው ይህን የሚያውቁበት ክስተት በልዕለ ሃያሏ ሀገር አሜሪካ በቱጃሮች መንደር በካሊፎርኒያ በሎስአንጀለስ ተፈጠረ።

ሰው ሆይ ማንም ሁን ምንም ይኑርህ ምንህም ዋስትና ሆኖ አያስመካህም ።

11/01/2025

በእሳት እና በረዶ የተፈተነችው ልዕለ ኃያል ሀገር

የዓለማችን ልዕለ ኃያል ሀገር አሜሪካ ከሰሞኑ እሳት እና በረዶ ለጥፋት አብረውባት ሰንብታለች፡፡

ሀገሪቱ በአንድ በኩል ያገኘውን ሁሉ በሚበላ ከባድ ሰደድ እሳት፤ በሌላ በኩል ደግሞ አጥንትን በሚሰረስር በረዶ ተፈትናለች፡፡

በሎስ አንጀለስ ከተማ የተነሳው ሰደድ እሳቱ እስካሁን የ10 ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ የተረጋገጠ ሲሆን፤ ከ170 ሺህ የሚበልጡ ሰዎችም መኖሪያቸውን ለቀው ለመሸሽ በተጠንቀቅ እንዲያሳልፉ አድርጎ ነበር፡፡

በከባድ ሙቀት እና ኃይለኛ ንፋስ የታጀበው ሰደድ እሳቱ ከ10 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን፣ ህንጻዎችን እና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን አውድሟል፡፡

10/01/2025

በአሜሪካ ሎሳንጀለስ የተከሰተው ሰደድ አሳት ዙሪያ ምን አዳዲስ ክስተቶች አሉ?

በአሜሪካ ሎሳንጀለስ ዙሪያ የተቀሰቀሰው ከባድ የሰደድ እሳት አደጋ ትናንት ምሽት ጀምሮ ወደ ሆሊውድ ኮረብታዎች እየተስፋፋ መሆኑ ተገልጿል።

ከባለፈው ማክሰኞ ጀምሮ በርካታ ቦታዎችን በፍጥነት ያዳረሰው በደረቅ ንፋስ እየተፋፋመ ያለው እሳት የማጥፋት ዘመቻውን ያከበደው ሲሆን ከ100 ሺ በላይ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ታዘዋል።

በእሳት አደጋው የደረሰው የኢኮኖሚ ጉዳት ከ57 ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚገመት ተገልጿል።

የነዳጅ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደረገከዛሬ ከታህሳስ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋ...
07/01/2025

የነዳጅ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደረገ

ከዛሬ ከታህሳስ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

በዚህም ቤንዚን በሊትር ብር 101.47 ሲገባ ናፍጣ በሊትር ብር 98.98 ሆኗል።

04/01/2025

በአፋር ክልል፣ ሳጋንቶ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ፍል ውሃዎች እየወጡ ነው
*****

በአፋር ክልል፣ ዱለሳ ወረዳ በተከሰት የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ፍል ውሃዎች እየተፈጠሩ ይገኛሉ።

በወረዳው በሳጋንቶ ቀበሌ የደረሰውን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ በስፍራው በአካል በመገኘት የመስክ ምልከታ ያደረገ የኢቢሲ ሪፖርተር በቀበሌው በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ፍል ውሃዎች እየወጡ መሆኑን መታዘቡን ገልጿል።

በቀበሌው በተለይ በዶፈን ተራራ ላይ የመሬት መንቀጥቀጡ በመጠኑም በድግግሞሹም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን በዚህም ሳቢያ ተራራው እየተናደ እንደሆነ ገልጿል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በፈጠረው ግፊት በቀበሌው እንፋሎት አዘል ፍል ውሃ እና ቅባት አዘል ጥቁር ውሃ ከመሬት እየፈለቀ መሆኑንም ጠቅሷልል።

በቀበሌው የሚኖረው አርብቶ አደር ማህበረሰብ ከሥፍራው ተነስቶ በሌሎች አካባቢዎች እንዲሰፍር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

በመሬት መንቀጥቀጡ ሳቢያ በፈንታሌ እና በዶፈን ተራራ መካከል የተፈጠረው የመሬት ስንጥቅ ክፍተቱ እየጨመረ መሆኑንም አክሏል።

03/01/2025

አራተኛው አርኪ የሪል ስቴት ኤክስፖ በስካይ ላይት ሆቴል ተከፈተ
የቤት ሻጮችና ገዢዎች፣ እንዲሁም ገንቢዎች የተለያዩ ተቋማትን ለማገናኘትና ለማስተሳስር ዕድል ይሰጣል የተባለለት አራተኛው አርኪ ሆምስ ኤክስፖ በዛሬው ዕለት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ ተከፍቷል።

ከዛሬ ታህሳስ 25 እስከ ታህሳስ 27/2017 በሚካሄደው በዚህ ኤክስፖ በርካታ የቤት አልሚዎች እየገነቡት ስላለው ቤት ግንባታዉ ያለበት ደረጃ፣ ሊገነቡት ስላቀዱት ቤት፣ ቤቶቹን ዋጋ፣ ስለሚፈልጉት እቃ እና አገልግሎት ከኤክስፖ ተሳታፊዎችና ከጎብኚዎች ጋር መረጃና ልምድ ይለዋወጣሉ ተብሏል።

ወቅቱ የበዓል እንደመሆኑ በርካታ ዲያስፖራዎች ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ በመሆኑ የኤክስፖውን ሳይጎበኙ ቤት እንዳይገዙ በሚል ሙሉ ቅድመ ዝግጅት የተደረገበት ልዩ የገና በዓል ቅናሽ መኖሩም ተገልገልፃል።

አርኪ ኤቨንት ኦርጋናይዘር ያዘጋጀው ይሄ ኤክስፖ በዘርፉ ላይ የተሰማሩ የቤት አልሚ ድርጅቶች እና አጋር አካላት እንደሚሳተፉ የተገለፀ ሲሆን ኤክስፖው መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ፤ አንድ ላይ በማቀናጀት በከተማ እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ ሊሰሩ የታሰቡ መዋቅራዊ ቅንጅቶችን ለመፍጠር ምቹ ዕድል የሚፈጥር ገዥና ሻጭን በአንድ ላይ በማገናኘት በቀጥታ የሚፈልጉትን የቤት ዓይነት የሚመርጡበት ስለአጠቃላይ ሂደት በግልፅ መረጃ የሚለዋወጡበት በርካታ አማራጮች ያሉበት ለተረጋጋና ምክንያታዊ የቤት ግዥ ዉሳኔ ምቹና ዓይነተኛ አጋጣሚ እንደሚፈጥር የዝግጅት ክፍሉ ያስታወቀ ሲሆን ሁሉም ቤት ገዥ እና አልሚ ይህ ዕድል ሳያመልጠዉ ኤክስፖዉን እንዲሳተፍ ጥሪ አቅረቧል፡፡

03/01/2025

በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ ዶፋን ተራራ ላይ የተከሰተው የቮልካኖ ፍንዳታ

ኢትዮ ባንኮክ የውበት አካዳሚ ተከፈተ ኢትዮ ባንኮክ የውበት አካዳሚ በዛሬው እለት በተለያዩ የውበት ሙያዎች በአጭር ጊዜ ብቁ አድርጎ ለማሰልጠን የሚያስችል የማሰልጠኛ ማዕከል መክፈቱን አስመል...
02/01/2025

ኢትዮ ባንኮክ የውበት አካዳሚ ተከፈተ

ኢትዮ ባንኮክ የውበት አካዳሚ በዛሬው እለት በተለያዩ የውበት ሙያዎች በአጭር ጊዜ ብቁ አድርጎ ለማሰልጠን የሚያስችል የማሰልጠኛ ማዕከል መክፈቱን አስመልክቶ ለተለያዩ የሚዲያ ባለሙያዎች አካዳሚውን አስጎበኘ።

በሙያው ረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸው መምህራን እና የማስተማሪያ ቁሳቁሶች ጋር አካቶ ስልጠና ለመስጠት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ የማዕከሉ መስራች እና ስራ አስኪያጅ አቶ ክብሮም ተስፋማርያም የገለጹት ሲሆን በቀጣይ አቅም ለሌላቸው እና በሙያው ለመስራት ፍላጎት ላላቸው ልዩ ትኩረት በመስጠት ከመደበኛው ክፍያ ባነሰ እና ለተመረጡ ደግሞ ስልጠናውን በነጻ ለመስጠት መታሰብን አቶ ክብሮም ተስፋማርያም ጨምረው ገልጸዋል።

አካዳሚው ሙሉ የፀጉር አሠራር ፣ የሜካፕ ጥበብ ፣ አይላሽ ፣ የፌሻል እና የቆዳ እንክብካቤ እና በኢትዮጵያ እስከ አሁን በስልጠና ደረጃ የማይሰጡ የውበት ስልጠናዎችን ለመስጠት መታሰብን በመርሐግብሩ ላይ ተገልጿል።

ዩቶፕያ ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን "ዩቶፕያ ግሪን ፈንድ " አስተዋወቀ። Ethio addis tube ዩቶፕያ ቴክኖሎጂ በቀጣይ አምስት አመት ውስጥ 10,000 ደንበኞችን የኤሌክት...
01/01/2025

ዩቶፕያ ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን "ዩቶፕያ ግሪን ፈንድ " አስተዋወቀ።

Ethio addis tube ዩቶፕያ ቴክኖሎጂ በቀጣይ አምስት አመት ውስጥ 10,000 ደንበኞችን የኤሌክትሪክ የመኪና ባለቤት ለማድረግ እቅድ ይዞ እየሰራ እንደሚገኝ በዛሬው በቤስት ዌስተርን ሆቴል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልጿል።

ሙሉ ቅድመ ክፍያ መክፈል የማይችሉ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከተለመደው የመኪና ፋይናንሲንግ በተለየ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተቀባይነት ያለው ከወለድ ነጻ የሆነ እና እስከ አስር አመት ድረስ እየተሰራ የሚከፈል የመኪና ሊዝ አከፋፈል ማመቻቸቱን ዩቶፕያ ቴክኖሎጂ መስራች እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አዶኒክ ወርቁ ገልጸዋል።

በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ መርሐግብር ላይ ተዋናይ እንግዳሰው ሀብቴ (ቴዲ) ብራንድ አምባሳደር አድርጎ የሾመ ሲሆን ኤም. ጂ ሞተር ከተሰኘ ተቋም ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ሰምምነት ፈጽሟል።

ድርጅታችን ላለፉት 5 አመታት ሲሰራበት የቆየውን በኢትዮጰያ ፈርቀዳጅ የሆነውን እና ለአካባቢ ንብረት ተስማሚ እንዲሁም ለነዳጅ የሚወጣውን የውጭ ምነዛሪ የሚ ያስቀር "ዩቶፕያ ግሪን ሞቢሊቲ” ፕሮጀክት እየተገበረ ሲሆን በውስጡ አራት ንኡስ ዘርፎችን አካቷል። በዚህም የመጀመሪያው “ዩቶፕያ አውቶሞቲቪ" በታዳሽ ሀይል የሚሰሩ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን የመገጣጠም የማቅረብ እና የመጠገን አገልግሎት ሁለተኛው "ዩቶፕያ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጂንግ የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ ሙሊት ጣቢያዎችን ከታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ጋር መገንባት ሶስተኛው ደግሞ "ዩቶፒያ የኤሌክትሪክ መኪና ታክሲ እና "ዩቶፕያ ግሪን ፈንድ” ለደንበኞቻችን የኤሌክትሪክ መኪና ፋይናንሲንግ ማመቻቸት እንደሆነ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።

የቶፕያ ቴክኖሎጂ ለደንበኞቹና ለአካባቢ ምቹ አስተማማኝ እና ዘላቂ የልማት መፍትሄዎችን በማስተዋወቅ ላይ ሲሆን አውቶሞቲቭ ፣ በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ ፣በማኑፋክቸሪንግ ፣ በግብርና ምርት ፕሮሰሲንግ እና ኤክስፖርት እንዲሁም በአይ ሲቲ ሴክትሮች የተሰማራ እንዲሁም ልምድ ባካበቱ ባለሙያዋች የተመሰረተ የቴክኖሎጂ እና ትሬዲንግ ኩባንያ ነው።

መስከረም አበራ የኢቨ ሞዲስ አምባሳደር ሆናለች | አርቲስት መስከረም አበራ ኢቨ ሞዲስ የህጻናት ዳይፐር የብራንድ አምባሳደር ሆና ተሹማለች።የብራንድ አምባሳደርነቱ ለአንድ አመት የሚቆይ ሲሆን...
28/12/2024

መስከረም አበራ የኢቨ ሞዲስ አምባሳደር ሆናለች | አርቲስት መስከረም አበራ ኢቨ ሞዲስ የህጻናት ዳይፐር የብራንድ አምባሳደር ሆና ተሹማለች።

የብራንድ አምባሳደርነቱ ለአንድ አመት የሚቆይ ሲሆን የቢል ቦርድ የቲቪና የሬድዮ ማስታወቂያዎችን መስራት የሚያስችላት መሆኑን ነው የተነገረው።

ደስታዬ በሙያዬ መቆየት ነው የምትለው መስከረም አበራ የህዝቡን ስሜት እኔ ፍላጎት መረዳት ዋነኛ ፍላጎቴ ነው ብላለች።

በቂ የሚወራ እና የሚያስመሰግን ስራ አልሰራሁም የምትለው መስከረም ከዚህ በኋላ ብዙ ለመስራት ተዘጋጅቻለሁ ብላለች።

ኢቨ የህጻናት ዳይፐር ለማስተዋወቅ ስምምነት የፈጸመችው አርቲስት መስከረም አበራ በሴቶች እና ህጻናት ጉዳይ የማስተዋውቀው ምርት አውቄው ነው ብላለች።

ልጅ የለኝም ግን ልጅ ለወለዱ ወዳጆቼ በመስጠት ምርቱን እንዲጠቀሙ አደርጋለሁ የምትለው አርቲስቷ የስምምነቱን መርህ ባከበረ መልኩ እሰራለሁ ስትል ተናግራለች።

ማህበራዊ ሚዲያንም ለህዝቡ በሚጠቅም እና የግል ህይወቴን ባልነካ መልኩ ምርቱን ለማስተዋወቅ ጥረት አደርጋለሁ ብላለች።

በጥራት አንደራደርም ያሉት የኢቨ ሞዲስ ማርኬቲንግ ዳሬክተሯ ለንጽህና ከፍተኛ ጥንቃቄ እናደርጋለን ብለዋል።

ኢንጅነር ቢጂ ናይከር አሸነፈ!በኢኮኖሚ ዘርፍ የ10,000.00 ( አስር ሚሊዮን ብር)  እና 5 ኪሎ የሚመዝን የብር ዋንጫ አሸናፊ ኢንጅነር ቢጂ ናይከርኢንጅነር ቢጃይ ናይከር "አባመላ" በመ...
26/12/2024

ኢንጅነር ቢጂ ናይከር አሸነፈ!

በኢኮኖሚ ዘርፍ የ10,000.00 ( አስር ሚሊዮን ብር) እና 5 ኪሎ የሚመዝን የብር ዋንጫ አሸናፊ ኢንጅነር ቢጂ ናይከር

ኢንጅነር ቢጃይ ናይከር "አባመላ" በመባል የሚታወቀው በስራ ፈጠራ በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ እድገት ውስጥ ቁልፍ ሚና ያለው ሰው ነው። ቤጃይ ኢቲዮ ቀደም ሲል ከውጭ የሚገቡ የኢንዱስትሪ መሳሪያዎችን በማምረት በሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች የስራ እድል ከመፍጠሩም በላይ በተለያዩ ዘርፎች አዳዲስ መፍትሄዎችን ፈርቀዳጅ አድርጓል። የቢጃይ ብልህነት እንደ ዘላቂ የኃይል ምንጮችን ማዳበር ባሉ ፕሮጀክቶች ውስጥ ያበራል። የስራ ፈጣሪነት ፍላጎት ያላቸውን ዜጎች ለመምከር ያለው ቁርጠኝነት ባሰለጠናቸው ከ110,000 በላይ ሰዎች ላይ ይታያል። የቴክኖሎጂ ፈጠራን እና ማህበረሰቡን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት በማጣመር ጠንካራ ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለው ቁርጠኝነት ና እውነት አባመላ ያሰኘዋል።

በየወሩ የሚደረግ የአብሮሆት "የጥበብ ማዕድ" ተከፈተ     ብሄራዊ አንድነታችንን  በኪነ ጥበብ አማካኝነት መግለጽን ዋንኛው ዓላማ ያደረገ መድረክ በይፋ ተከፈተ።የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪ...
25/12/2024

በየወሩ የሚደረግ የአብሮሆት "የጥበብ ማዕድ" ተከፈተ

ብሄራዊ አንድነታችንን በኪነ ጥበብ አማካኝነት መግለጽን ዋንኛው ዓላማ ያደረገ መድረክ በይፋ ተከፈተ።

የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ አባ ገዳዎች ፣ አንጋፋ እና ወጣት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የነበርንበትን፣ ያለንበትን እና የምንደርስበትን የሚያመላክት "ስለነገ" መርሃ ግብርና "አብርሆት የጥበባት ማዕድ" ዝግጅት በይፋ አስጀምሯል።

በሀገራዊ ድሎቻችንና ፣ በደስታችንም በሀዘናችንም የማይለየንን የኪነ ጥበብን አቅም ለመጠቀም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ ተጠቅሷል

የአዲስ አበባ ከተማ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሣው በፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኪነ ጥበብን ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር የሀገራችን ልዕልና ዕውን ለማድረግ መጠቀም ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ብዝሀ ሀብት ያላት ሀገር ናት ያሉት ዶ/ር ሂሩት ነገን ዛሬ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ኪነ ጥበብ የበኩሏን ሚና እንድትወጣ የኪነ ጥበቡ ማህበረሰቡ ዛሬ ይፋ በተደረጉት " ስለ ነገ " እና በሌሎችም መርሃ ግብሮች ላይ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባው ገልፀዋል።

በየወሩ የሚደረገውን የ"አብርሆት የጥበባት ማዕድ" ዝግጅትን ጨምሮ ፣ የነበርንበት ፣ ያለንበትና የምንደርስበት የሚዘከርበት " ስለ ነገ " የተሰኘ ፕሮግራም በተለያዩ የኪነ ጥበብ ይዘቶችና ቅርጾች በቀጣይ በተከታታይ እንደሚቀርቡ በዶ/ር ሂሩት ካሳው ተመላክቷል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሙአዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ በሰጡት ምክረ ሀሳብ በኪነ ጥበብ ዝግጅቱ ተሰጥዋቸውን
ያቀረቡ ታዳጊዎች ዕድሉን ካገኙ ብዙ መስራት የሚችሉ መኖራቸውን ማሳያ ናቸው ብለዋል።

አዲስ አበባ የኪነ - ጥበብ ባለሙያዎች መናኸሪያ መሆኗን ጠቁመው በየአካባቢያቸው ለታዳጊ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባቸው የገለፁ ሲሆን እንደ ከተማ ነዋሪ የድርሻቸውን እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።

አርቲስት መቅደስ ፀጋዬ በፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፈችው መልዕክት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ሰብሰብ ብለው ሀሳባቸውን የሚለዋወጡበት መድረክ መዘጋጀቱ ብዝሀነታችን ለዓለም ለማስተዋወቅ ዕድል ስለሚፈጥር ልንጠቀምበት ይገባል ብላለች ።

በፕሮግራሙ ላይ ታዋቂ ገጣሚያን ስራዎቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ፣ ህብረ ብሔራዊ አኢትዮጵያዊነትን ከፍ የሚያደርጉ ውብ ህብር ዜማዎችም ቀርበዋል።
የክብር እንግዳ የሆኑት አቶ አብርሃም ታደሰ " በደስታችንም በሀዘናችንም የማይለየንን የኪነ ጥበብን አቅም መጠቀም ይገባናል ብለዋል።


የነበርንበትን ትናንት፣ ያለንበትን ዛሬ እና የምንደርስበትን ነገን የሚያመላክት ጥበብን የሚሸምን፤ በጥበብ ሀገርን የሚያሻግር "ስለነገ" የሚያልም ትውልድን በመፍጠር ኪነ ጥበብ ያላትን ሚና እንድትወጣ የተዘጋጀው መርሃ ግብር ይበል የሚያሰኝ ነው።

"መዝገበ ጸሎት በብሬል"  የተሰኘ መጽሐፍ በስጦታ ሊበረከት ነው።  | በሕፃን ሶሊያና ተሾመ እና በሕፃን ሔራን ተሾመ አማካኝነት የተዘጋጀው "መዝገበ ጸሎት በብራል" የተሰኘ መንፈሳዊ መጽሐፍ...
24/12/2024

"መዝገበ ጸሎት በብሬል" የተሰኘ መጽሐፍ በስጦታ ሊበረከት ነው።

| በሕፃን ሶሊያና ተሾመ እና በሕፃን ሔራን ተሾመ አማካኝነት የተዘጋጀው "መዝገበ ጸሎት በብራል" የተሰኘ መንፈሳዊ መጽሐፍ የፊታችን ታህሳስ 27 ቀን 2017 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዮኒቨርስቲ ከቀኑ 6:00 ጀምሮ በተዘጋጀ መርሐግብር እንደሚመረቅ እና በእለቱም የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን በማስመልከት ለተለያዩ ለአይነ ስውራን ማዕከላት በስጦታ እንደሚበረከት ተገለጸ።

አጠቃላይ የምርቃት እና የስጦታ መርሐግብር አስመልክቶ የሕጻናቱ ወላጅ እናት ወይዘሮ ትግስት ካሳ በዛሬው እለት ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት በአዝማን ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት መጽሐፉ በሕፃን ሶሊያና ተሾመ እና በሕፃን ሔራን ተሾመ አማካኝነት በአንድ ወር ውስጥ የተዘጋጀው መዝገበ ጸሎት በብራል የተሰኘ ለአይነ ስውራን የተዘጋጀው መጽሐፍ ከተመረቀ በኋላ በሕጻናቶቹ አማካኝነት ለአይነ ስውራን በስጦታ ለማበርከት ፅኑ ፍላጎት እንዳላቸው " ገልጸዋል።

በሊተ የማማከር ፣ የስልጠና እና ኩነቶች አዘጋጅ አስተባባሪነት የሚከናወነው የመጽሐፍ ምርቃት እና የስጦታ
መርሐግብር ሁሉም ህብረተሰብ ክፍል ተገኝቶ ህጻናቱን እንዲያበረታታ እንዲሁም በቀጣይ ከ500 በላይ የብሬል መጽሐፍቶችን በስጦታ ለማድረስ መታሰቡን የሊተ የማማከር ፣ የስልጠና እና ኩነቶች ዋና ስራ አስኪያጅ ዘማሪት ህይወት ወልዴ ገልጸዋል።

መጽሐፍ የዘወትር ጸሎት፣ ውዳሴ ማርያም፣ አንቀጸ ብርሀን፣ ይወድስዋ መላዕክት እና ሰኔ ጎሎጎታ የያዘ ሲሆን ለበርካቶች ይደርስ ዘንድ ማገዝ እንዲቻል የአንዱ መጽሐፍ ዋጋ 4000 ብር መሆኑን እና ሁሉም እንዲያግዝ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
👉 1000622473872
አቢሲኒያ ባንክ
👉 91613069

ለበለጠ መረጃ
0965531422
0923114411

ፍሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ በዚህ አመት ከ800 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘፍሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ አ.ማ ይህን ያስታወቀው በዛሬው እለት 8ተኛ ዓመታዊ መደበኛ እና 2ተኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉ...
21/12/2024

ፍሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ በዚህ አመት ከ800 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ

ፍሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ አ.ማ ይህን ያስታወቀው በዛሬው እለት 8ተኛ ዓመታዊ መደበኛ እና 2ተኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ነው።

አክስዮን ማህበሩ የፋናንስ አፈጻጸም ሪፓርቱን ለባለ አክስዮኖች ይፋ ያደረገ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የድርጅቱ አጠቃላይ ገቢ 829 ሚሊየን 253 ሺህ 092 ብር መሆኑን ገልጿ ከታክስ በፊት የነበረዉ ጠቅላላ ትርፍ 36 ሚሊዮን 658 ሺህ 747 ብር መሆኑን አስታውቋል።

ይህም ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ትርፍ ጋር ሲነፃፀር 84 በመቶ እድገት ማሳየቱ ተገልጿል።

በተጨማሪም ፍሊንትስቶን ኢንጅነሪግ አክስዮን ማህበር የተጣራ ትርፉ 25 ሚሊዮን 61 ሺህ 865 ብር እንደሆነ የገለፀ ሲሆን በአንድ አክሲዮን ላይ የተገኘ ትርፍ 33.62 ሆኖ መመዝገቡን አስታውቋል።

በዚህም በበጀት አመቱ የኩባንያዉ ጠቅላላ ንብረት 2.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ገልፆ ይህም ባለፈዉ ዓመት ከነበረዉ ሂሳብ 1.7 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነፃፀር 24 በመቶ ልዮነትን አሳይቷል ተብሏል።

አክስዮን ማህበሩ የአክሲዮኖች ሽያጭ በአመቱ የተከናወነው ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ አስታውቆ አብዛኛው የሽያጭ ስራ ከቤቶች ይልቅ ወደ አክሲዮኖች ሊያተኩር እንደቻለ አስታውቋል።

በዚህም የተነሳ በአጠቃላይ 269 ሺህ 433 ያህል አክሲዮኖች መሸጡ የተነገረ ሲሆን የባለአክሲዮኖቹን ቁጥርም ከ7 ወደ 1 ሺህ 799 ማደጉን አክሲዮን ማህበሩ ገልጿል።

ሸክም ቢቀል  ተመረቀየፕሮጃይኒስት ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅትና የመክሊት ማይክሮ ፋይናንስ መስራችና የፕሮጃይኒስት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ነጻነት መንግስቱ ሸክም ቢቀል የተሰኘ መጽሀፍ...
21/12/2024

ሸክም ቢቀል ተመረቀ

የፕሮጃይኒስት ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅትና የመክሊት ማይክሮ ፋይናንስ መስራችና የፕሮጃይኒስት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ነጻነት መንግስቱ ሸክም ቢቀል የተሰኘ መጽሀፍ ለውድ አንባቢያን ቀርቧል።

ጸሀፊዋ ከትውልድ ቦታቸው አሶሳ የጀመረውን የህይወት መንገድ፣ በወቅቱ የኢትዮጵያ የፖለቲካ መስመር የነበራቸውን የረጅም ዘመን የትግል ምዕራፍ፣ሰንገደ ላይ በደርግ በግፍ ከተገደሉት 11 ጓዶች አንዱ የነበሩት የቀድሞ ባለቤታቸው ይርጋ ተሰማን የተዳፈነ ሀቅ፣ ቆይቶም በዘመነ ኢህአዴግ የሽግግር መንግስት ወቅት በውጭ ንግድ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር ሆነው ሲያገለግሉ በኋላም በቀድሞው የሽግግር መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ታምራት ላይኔ የአንድ መስመር ደብዳቤ ገሸሽ ተደርገው ሁለቱን (ፕሮጃይኒስትና መክሊትን) መስርተው ያሳለፉትንሌላ ገጽ የህይወት ምዕራፍ በሚገባ ተርከውታል።

ጸሀፊዋ በሸክም ቢቀል መጽሀፋቸው በኢትዮጵያችን የሴቶች ማህበራዊ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎዎች በቅጡ ያልተዘገቡ ሸክሞችን ያነሳሉ። ሴቶች የህይወት ተሞክሮዎቻቸውን ጽፈው ለትውልድ የማቆየት ልምድ የላቸውም።ወንዱም ቢሆን ከሴት የተሻለ ይሰራዋል ለማለት ካልሆነ በስተቀር እሱንም ቢሆን እንደሃገር የሚገባንን ያህል እየዘገበ ነው ለማለት ይከብዳል ይላሉ ጸሀፊዋ።

ሴቶች ከቤተሰብ ሀላፊነት ሸክም እና ልጆችን ከማሳደግ አልፎ በአካባቢና በአገር ኢኮኖሚ እድገት፣ በአገር የነጻነት ተጋድሎ፣ ለአገረ መንግስት ግንባታ እና ለአገር ዕድገት ያደረጉት አስተዋጽዖ ጎልቶ አልወጣም ሲሉ በቁጭት ይተርኩታል።

ይህንን የኖረ ቁጭት የሚወጣና ስነ ጽሁፋዊ ውበቱን ጠብቆ የተሰናሰለ ታሪክን ለትውልድ የሚያሸጋግረው በወ/ሮ ነጻነት መንግስቱ የተጻፈው ሸክም ቢቀል የተሰኘው መጽሀፍ ዛሬ ታህሳስ 12/2017 ዓ/ም በሂልተን ሆቴል ተመርቋል።

ሸክም ቢቀል
1. የነጻነት ጉዞ፣ ትሩፋቶች፣ እንቅፋቶችና በኋላም በረከቶች
2. ይርጋ ተሰማ ሲታወስ ስብዕናና የትግል ሕይወት፤
3. በሰንገደ የጭዳ በጎች በሚል በተሰናሰሉ ሦሥት ዋና ዋና ክፈሎች ስር በ428 ገፆች ከካበተ ልምድና እውቀት ተከትቦ በግሩም አጻጻፍ ተሰንዷል።
ጸሀፊዋ ወይዘሮ ነጻነት መንግስቱ መጽሀፉ ለውድ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ከነበራቸው ፅኑ ፍቅር የተነሳ የህዝቦችን ነጻነትና እኩልነት ለማረጋገጥ ሁሉን ጥለው እስከ አሲምባ ከተጓዙ በኋላ ሰንገደ እስር ቤት ውስጥ ለተገደሉ 11 የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ(ኢሕአፓ) ሰማዕታት ይሁንልኝ ብለዋል።
መጽሀፉ በይፍዊ ስነ ስርዓት ተመርቆም በሀገር ቤትም ይሁን በባህር ማዶ ለሚገኙ አንባብያን ለገበያ ቀርቧል።

ውድ አንባቢያን በብዙው እንድታተርፉበት ተጋብዛችኋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮ አዲስ ቲዩብ የአዕምሮ መረጃ ማዕከል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share