ዘንድሮ

ዘንድሮ ወቅታዊ ጉዳዮች

ዘንድሮ Times ወቅታዊ እና ተያያዝ ስነ- ልቡናዊ፣ ማኅበራዊ፣ ጤና፣ ባህል፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚክስ እና መሰል ጉዳዮች ላይ መረጃዎችን፣ የባለሙያ ሀሳቦችን፣ ሂሶችን፣ የመፍትሄ እና አስደናቂ ለውጥ ሀሳቦችን የምንጋራበት፣ የምንለዋወጥበት፣ የምንማማርበት እና ዘንድሮን እንዲሁም መጪውን ጊዜ የተሻለ ለማድረግ የሚጠቅሙ ሁለገብ ጉዳዮች የሚስተናገዱበት መድረክ ነው፡፡

ዘንድሮ የትላንት በአንድ ገፁ የትላንትን አምሳል ነው፡፡ ዘንድሮ የዛሬ የግለሰቦች፣ ማኅበረሰብ እና መንግስት ምርጫና ተግባራዊ እንቅስቃሴ አጠቃላይ ድምር ውጤት ነው፡፡ ዘንድሮ የነገን መልክ በእጅጉ የሚወስን የዛሬ ተግባር ነው፡፡ በአጭሩ ዘንድሮ ትላንት፣ ዛሬ እና ነገ

ነው፡፡ ከዚህ እና መሰል እሳቤዎች በመነሳት ይህ ማኅበራዊ ገፅ (ዘንድሮ) በግለሰብ እና ማኅበረሰብ ደረጃ ትላንትን በቅርበት እና ቀናነት መረዳት የምንችልበትን፣ ዛሬን ከመረዳት ባሻገር የተሻለ እንዲሆን ቁልፍ ሚና የምንጫወትበትን ሙያዊ እና ሀገራዊ ፋይዳ ያለው እውቀት፣ ክህሎት እና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ እና ምናባዊ ጉዳዮችን የምንማርበት፤ ነገ ከትላንት እንዲሁም ከዛሬ በእጅጉ የቀናና የላቀ እንዲሆን ዘንድሮ ምን፣ ለምን እና እንዴት መማር፣ ማወቅ፣ መስራት፣ እና መለወጥ እንደሚገባን የምንነጋገርበት መስክ ነው፡፡

Zendro Times, among other things offers useful and up-to-date news, information's, insights and inputs of great minds across the globe on life, society and the world as we know it and/or as it should be. The page also pushes forward ideas and information's that can be used to bring about positive change on self and the world widely ranging from health to lifestyle.

29/06/2025

23/06/2025
እንንቃ! የሚጣፍጥ ሁሉ ማር አይደለም!!!ለብዙ ዓመታት ፕላስቲክ ቆሻሻን በማስወገድ እንቅስቃሴ ውስጥ ስሳተፍ ከታዘብኳቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ የሚጣለውን ፕላስቲክ የመለየት ነገር ነው። ከእነ...
18/06/2025

እንንቃ!

የሚጣፍጥ ሁሉ ማር አይደለም!!!

ለብዙ ዓመታት ፕላስቲክ ቆሻሻን በማስወገድ እንቅስቃሴ ውስጥ ስሳተፍ ከታዘብኳቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ የሚጣለውን ፕላስቲክ የመለየት ነገር ነው። ከእነዚህ ውስጥ ጎልተው የሚታዩት የውሃ ና ሌሎች አልኮል ያልሆኑ መጠጦች መያዣ የላስቲክ ኮዳዎች፥ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ፕላስቲኮችና የቀላል ምግቦች ማሸጊያዎች ናቸው።

በዚህች አጭር መልዕክት ላነሳ የምፈልገው ወላጆች አዘውትረው ለልጆቻቸው በሚገዟቸውና ባብዛኛው ወጣቶችም በሚመገቧቸው ቀላልና የታሸጉ ምግቦች ዙሪያ የሚያሳስበኝን ነገር ነው።

እንደሚታወቀው የሚጣፍጥ ሁሉ ማር አይደለምና እነዚህን በማራኪ ማሸጊያዎች ተጠቅልለው የሚቀርቡ ቀላል ምግቦች ስንገዛ ለጤና የሚኖራቸውን ፋይዳ ተገንዝበን ቢሆን ጥሩ ነው። ዛሬ ሌላው ዓለም እንደነዚህ ዓይነት ምግቦች በጤና ላይ የሚኖራቸውን አደጋ ለመቀነስ የቁጥጥር ስርዓቱን አጥብቆ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን፥ እኛ እዚያ ደረጃ ላይ እስክንደርስ ድረስ ከሌሎች ልንማር የሚገባንን መማር ብልህነት ይሆናል። ዛሬ ካልተጠነቀቅን ነገ ልንቀለብሰው ወደማንችለው የጤና ችግር ውስጥ ሊከተን ይችላልና።

እንደ ብስኩት፣ ድንች ቺፕስ እና ሌሎች በፕላስቲክ መጠቅለያዎች የተጠቀለሉ ምግቦች በተለይ ለልጆች በርካታ የጤና ስጋቶችን ያስከትላሉ፡

🔬 1. የኬሚካል መፍሰስ
ብዙ የፕላስቲክ መጠቅለያዎች እንደ ፖሊኢትይሊን፣ ፖሊፕሮፒሊን ወይም ፒቪሲ ባሉ ቁሳቁሶች የተሠሩ ሲሆኑ፣ እነዚህም የሚከተሉትን ተጨማሪ ንጥረ ንገሮች ሊይዙ ይችላሉ፡

• ፍታሌቶች (ፕላስቲኮች ተጣጣፊ እንዲሆኑ የሚያደርጉ ንጥረ ነገሮች) እና ቢስፌኖል ኤ (ቢፒኤ) የሆርሞን መረበሽ እንደሚያስከትሉ ይታወቃል።

• በሙቀት፣ በፀሐይ ብርሃን ወይም ረዘም ላለ ጊዜ በመከማቸታቸው ምክንያት እነዚህ ኬሚካሎች በትንሽ መጠን ወደ ምግቡ ውስጥ ሊፈሱ ይችላሉ።ልጆች በማደግ ላይ ባለ አካላቸው እና በዝቅተኛ የሰውነት ክብደታቸው የተነሳ ለእነዚህ ሆርሞን አዋኪ ኬሚካሎች የበለጠ ተጋላጭ ናቸው፣ ይህም አካላዊ እድገታቸውን፣ ሁለንተናዊ እድገታቸውን እና የረጅም ጊዜ ጤናቸውን ሊጎዳ ይችላል።

🍟 2. በበዛ ሂደት የተዘጋጁ ምግቦች
በፕላስቲክ መጠቅለያዎች ውስጥ ያሉ ምግቦች ብዙውን ጊዜ ከመጠን ባለፈ ሂደት የተዘጋጁ ሲሆኑ፣ ብዙውን ጊዜ የሚከተሉትን በከፍተኛ መጠን ይይዛሉ፡

• ጨው፣ ስኳር እና ጤናማ ያልሆኑ ስቦች፥

• ሰው ሰራሽ ተጨማሪ የምግብ ማቆያና ማጣፈጫዎች እና መከላከያ ንጥረ ነገሮች፥

እነዚህን ምግቦች ልጆች አዘውትረው መጠቀማቸው ለውፍረት፣ የስኳር በሽታ እና የባህሪ ችግሮች ይዳርጋቸዋል።

🗑️ 3. በአካባቢ ለሚገኙ መርዛማ ንጥረ ነገሮች መጋለጥ
በቤቶች፣ በመንገዶች እና በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ያለ የፕላስቲክ ቆሻሻ ፦

• በአየር፣ በውሃ እና በአፈር ውስጥ ማይክሮፕላስቲኮች (የፕላሲክ ብናኞች ወይም ደቃቆች) እንዲኖሩ ምክንያት ነው።

• በተዘዋዋሪ በምግብ ውስጥ ወይም በምንተነፍሰው አየር ውስጥ ማይክሮፕላስቲኮች እንዲገቡ በማድረግ በጊዜ ሂደት በሰውነት ውስጥ ሊከማቹ ይችላሉ።

✅ ስለዚህ ምን ይሻላል?
• በተፈጥሮ በሚገኙ መጠቅለያዎች የታሸጉ ምግቦችን (ለምሳሌ፣ ፍራፍሬ፣ ለውዝ) መመገብ፥
• በመልሶ ጥቅም ላይ የሚውሉ መያዣዎች (እንደ መስታወት፣ አይዝጌ ብረት ወይም ለምግብ ተስማሚ የሆነ ሲሊኮን) ውስጥ የተከማቹ ምግቦችን መመገብ፣

ስለዚህ፣ አልፎ አልፎ በፕላስቲክ የታሸጉ ምግቦችን መመገብ የከፋ ጉዳት ባይኖረውም፣ ልጆችን አዘውትሮ በፕላስቲክ የታሸጉ ምግቦችን መመገብ ግን ለጤና ጠንቅ ነው።

ልብ እንበል! ወደ ጤናማ ምግቦችና እና ዘላቂ መጠቅለያዎች መሸጋገር ጤናን እና ምድራችንን ይጠብቃል።

✍️ Firew Kefyalew

05/06/2025

Check out Lancet MCH’s video.

01/06/2025

31/05/2025

16/05/2025



30/04/2025
11/02/2024

"ታሪክን መዘከር ብቻ ሳይሆን፣ ከታሪክ መማርም አለብን። ዛሬ የምንገኝበት ሁኔታ ዓድዋን የመሰለ ግዙፍ ታሪክ የሌለን አስመስሏል" ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

10/02/2024

"ኢትዮጵያን ለማጥፋት እግዜርን መሆን ይጠይቃል"
የፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ ድንቅ ንግግር 💚💛❤

"ወደ ሀገር እንዳልገባ ከልክለውኝ በመጣሁበት አውሮፕላን እየተመለስኩ ነው"--- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከደቂቃዎች በፊት በስልክ ነገሩኝ የተወሰደ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አ...
06/02/2024

"ወደ ሀገር እንዳልገባ ከልክለውኝ በመጣሁበት አውሮፕላን እየተመለስኩ ነው"--- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከደቂቃዎች በፊት በስልክ ነገሩኝ የተወሰደ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በአሜሪካ ከነበራቸው አጭር ቆይታ በኋላ ዛሬ ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱ መግባት ተከልክለው በመጡበት አውሮፕላን እየተመለሱ እንደሆነ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በስልክ አሳውቀውኛል።

"እንዴ ኮበለለ፣ ሌላ ግዜ ሀገር ጥሎ ጠፋ ሲባል እኛም አውቀነው ነበር... ድርጊቱ ግን ቤተክርስቲያናችንን ለማዋረድ የተደረገ ነው" በማለት አስተያየታቸውን ሰጡኝ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ አብርሀምን ጨምሮ በርካታ የቤተ ክህነት ሀላፊዎች አየር ማረፊያ በመገኘት መፍትሄ ቢፈልጉም ሳይሳካ ቀርቷል ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር አመለጡ፣ ኮበለሉ፣ ተሰደዱ... ወዘተ የሚሉ መረጃዎች በሰበር ዜናነት የዛሬ ሶስት ሳምንት ገደማ በስፋት እየተሰራጩ ነበር። በወቅቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መረጃው ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀው በዛሬው እለት እንደሚመለሱ አሳውቀው ነበር።

(ከጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ገፅ)

Address

Addis Abeba

Telephone

+251913239965

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዘንድሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ዘንድሮ:

Share