Gebeya Media

Gebeya Media This is the official Gebeya Media page.
(1)

"Economic growth for social security"

Follow us on:
Telegram፦ t.me/gebeyanews
YouTube፦ youtube.com/
Gebeya Business፦ youtube.com/
TikTok፦ vm.tiktok.com/ZMHKxXmEkuP8W-wJFBO/

"የኒውክሌሩ ጦርነት ታወጀ! የአያቶላ ሃሚኒ ቁጣ እና የዓለም ስጋት! እስራኤልና አሜሪካ በኢራን ላይ ጦርነት አወጁ!"ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!👇
18/12/2025

"የኒውክሌሩ ጦርነት ታወጀ! የአያቶላ ሃሚኒ ቁጣ እና የዓለም ስጋት! እስራኤልና አሜሪካ በኢራን ላይ ጦርነት አወጁ!"

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!👇

ገበያ ሚዲያን ይወዳጁ !Telegram👉 https://t.me/gebeyanewshttps://youtube.com/ to Gebeya Media! Gebeya Media is an online media startup that offers...

በ200 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው አዋሽ ካፒታል አ.ማ. በይፋ ሥራ ጀመረ  ታህሳስ 09/2018 (ገበያ ሚዲያ) ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ...
18/12/2025

በ200 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው አዋሽ ካፒታል አ.ማ. በይፋ ሥራ ጀመረ

ታህሳስ 09/2018 (ገበያ ሚዲያ) ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ ያገኘነውና በ200ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው አዋሽ ካፒታል አ.ማ. በዛሬው ዕለት በይፋ ሥራ ጀምሯል።

በሥራማስጀመርያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአዋሽ ካፒታል አ.ማ. የቦርድ ሰብሳቢ እናየአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው፤ "ሀገራችን በፋይናንስ ዘርፍ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አዲስ ምዕራፍበመግባት ዘርፈ ብዙ ለውጦችን እያደረገች በምትገኝበት በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን መቋቋሙ ለቢዝነስ ዘርፉትልቅ መነቃቃትን የሚፈጥር ነው" ብለዋል።

የአዋሽ ባንክ ተቀጥላ ኩባንያ የሆነው አዋሽ ካፒታል አ.ማ ሕጉ የሚጠይቃቸውን መስፈርቶችና መመዘኛዎችበተገቢው ሁኔታ በሟሟላት ሙሉ የኢንቨስትመንት ባንክ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ሕዳር 10ቀን 2018 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን መቀበሉን አሳውቀዋል፡፡

አክለውም አዋሽ ካፒታል አ.ማ ለሀገራዊ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት በተገቢው ሁኔታ ራሱን በማደራጀት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣትየዝግጅት ምዕራፉን በማጠናቀቅ በ200 ሚሊዮን ካፒታል ሥራ መጀመሩ ገልጸዋል፡፡

አዋሽ ካፒታል አ.ማ. የተለያዩ የኢንቨስትመንት ባንክ አገልግሎቶችን ማለትም በድርጅት ፋይናንስ እና የማማከር አገልግሎት፥ በዋስትናንግድ እና የማገናኘት ስራ፥ በምርምር እና የገበያ ኢንተሊጀንስ፥ በአረንጓዴ ፋይናንስ እና የESG ወይምከባባዊ፣ ማህበራዊና አስተዳዳራዊ የማማከር አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለፁት ደግሞ፤ የአዋሽ ካፒታል አ.ማ. ዋና ሥራ አስፈጻሚአንዱአለም ኃይሉ (ዶ/ር) ናቸው።

አዋሽ ካፒታል አ.ማ በሀገሪቱ ውስጥ ካሉት ፍቃድ የተሰጠቻው የኢንቨስትመንት ባንኮች አራተኛው በመሆን ነው በዛሬው ዕለት ታህሳስ 9 ቀን2018 ዓ/ም በይፋ ሥራ የጀመረው።

በሚሊዮን ሙሴ

#ገበያ #ኢትዮጵያ

ጀነራል አል-ቡርሃን የሱዳንን ጦርነት ለማቆም ከትራምፕ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁታህሳስ 09/2018 (ገበያ ሚዲያ) የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር እና የሱዳን...
18/12/2025

ጀነራል አል-ቡርሃን የሱዳንን ጦርነት ለማቆም ከትራምፕ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ

ታህሳስ 09/2018 (ገበያ ሚዲያ) የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር እና የሱዳን ጦር ጠቅላይ አዛዥ ጀነራል አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን፤ በሀገሪቱ ሰላምን ለማስፈን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ጋር በቅርበት ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።

አልቡርሃን ይህን ያሉት በሳውዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሰልማን ግብዣ ወደ ሪያድ አቅንተው ባደረጉት ይፋዊ ጉብኝት ማጠቃለያ ላይ ሲሆን፤ ይህ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በሱዳን ከሚያዝያ 2023 ጀምሮ የቀጠለውን ደም አፋሳሽ ግጭት ለመቋጨት አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ መሆኑ ተነግሯል።

ከዚህ በተጨማሪ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ አል-ቡርሃን ፕሬዝዳንት ትራምፕ "የሱዳንን ጦርነት ለማቆም እና ሰላምን ለማምጣት ያላቸውን ጽኑ አቋም" ያደንቃሉ ብሏል።

በተለይም ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ የሱዳንን ቀውስ "በዓለም ላይ አስከፊው ሰብአዊ ቀውስ" በማለት መጥራታቸውን ተከትሎ፤ የሱዳን መንግሥት ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና ከልዩ የሰላም መልዕክተኛው ማስአድ ቡሎስ ጋር በመተባበር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸው አረጋግጠዋል።

ሳውዲ አረቢያ፣ አሜሪካ፣ ግብፅ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ግጭቱን ለማስቆም ጥረት እያደረጉ ቢቆዩም፣ ቀደም ሲል፤ የቀረቡ የሰላም ሃሳቦች በጄነራል አል-ቡርሃን በኩል ውድቅ ተደርገው እንደነበር ይታወሳል።

ሆኖም የሳውዲው አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሰልማን በዋሽንግተን ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጉዳዩ ላይ ጣልቃ እንዲገቡ ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን፤ አዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የያዘው አቋምም አል-ቡርሃን የሰላም አማራጮችን በድጋሚ እንዲመረምሩ ዕድል የፈጠረ ይመስላል።

በጄነራል አል-ቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር እና በጄነራል መሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) የሚመራው የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል መካከል የሚካሄደው ግጭት እስካሁን ድረስ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን፤ ከ13 ሚሊዮን በላይ ሱዳናውያንን ለስደትና ለከፋ ረሃብ ዳርጓል።

በሚሊዮን ሙሴ

#ገበያ #ኢትዮጵያ #ሱዳን #አሜሪካ #ትራምፕ

ሀሰተኛ መድኃኒቶች እና የሕክምና ምርቶችን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ ብሔራዊ ስትራቴጂ ይፋ ሆነታህሳስ 09/2018 (ገበያ ሚዲያ) የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን ከጤና ሚኒስቴር...
18/12/2025

ሀሰተኛ መድኃኒቶች እና የሕክምና ምርቶችን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ ብሔራዊ ስትራቴጂ ይፋ ሆነ

ታህሳስ 09/2018 (ገበያ ሚዲያ) የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር፣ የሕዝብ ጤናን ለመጠበቅ እና የኢትዮጵያን የጤና አጠባበቅ ስርዓትን ለማጠናከር ያለመ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና ሃሰተኛ መድኃኒቶች እና የሕክምና ምርቶችን መከላከል የሚያስችል ብሔራዊ ስትራቴጂ በይፋ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል።

በዚህም የሕክምና ምርቶች ደህንነት፣ ውጤታማነት እና ጥራት በጤና ስርዓቱ ላይ የሕዝብ አመኔታን እና የዓለም አቀፍ የጤና ሽፋንን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናግረዋል።

ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና ሃሰተኛ የሕክምና ምርቶች ሕይወትን አደጋ ላይ በመጣል፣ በጤና አጠባበቅ ላይ ያለውን እምነት በመቀነስ እና ብሔራዊ የጤና ግቦችን በማዳከም ከባድ ስጋት መፍጠራቸውንም አንስተዋል።

ስለሆነም "የተቀናጀ፣ ቀጣይነት ያለው እና በሚገባ የሚተዳደር የቁጥጥር እርምጃ ያስፈልጋል" ያሉት ሚኒስትሯ፤ የስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ዓላማዎች በማስረጃ ላይ በተመሰረቱ ስልቶች እና ጠንካራ የአስተዳደር እና የክትትል ማዕቀፎች አማካኝነት ለተግባር ግልጽ ሆኖ መዘጋጀቱን ተናግዋል።

በዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ የኢንዱስትሪ ተዋናዮች፣ የትምህርት ተቋማት፣ የሲቪል ማህበረሰብ፣ የልማት አጋሮች እና ሕዝቡን ጨምሮ፤ የእቅዱን ትግበራ በንቃት እንዲደግፉ ጥሪ ማቅረባቸውን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በበኩላቸው፤ ባለስልጣኑ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና ሃሰተኛ የሕክምና ምርቶችን ስርጭት ለመግታት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

#ገበያ #ኢትዮጵያ #መድኃኒት #ጤና

መልካም ቀን!  ሚድያ
18/12/2025

መልካም ቀን!
ሚድያ

ባለስልጣኑ 17 የጤና ባለሙያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) የአዲስ አበባ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በከተማዋ የጤና ባለሙያዎችን ሥነ-ምግባ...
17/12/2025

ባለስልጣኑ 17 የጤና ባለሙያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ

ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) የአዲስ አበባ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በከተማዋ የጤና ባለሙያዎችን ሥነ-ምግባር እና ሕክምና ስርዓት በተመለከተ በአጠቃላይ በአራት ወራት ውስጥ ወደ 21 የሚሆኑ የጤና ተቋማት ቅሬታ እንደቀረበባቸው አስታውቋል።

በዚህም ቅሬታውን ተከትሎ በባለስልጣኑ ሥር በሚገኘው ኮሚቴ በተደረገ ቁጥጥር 17 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ተጠያቂ መሆናቸውን፤ በባለስልጣኑ የጤና ባለሙያዎች ሥነ-ምግባርና ሕክምና ምክትል ዳይሬክተር አቶ መትከል ገብረመድህን ለገበያ ሚዲያ ተናግረዋል።

በዚህም መሠረት፤ ከቃል ማስጠንቀቂያ እስከ ከሥራ እገዳና የፍቃድ እግድ ድረስ እርምጃ መወሰዱን አንስተው፤ የሁሉም ጤና ባለሙያዎች እርምጃ ባለፉት አራት ወራት ውስጥ ብቻ የተወሰደ መሆኑን አሰረድተዋል።

በመሆኑም 10 የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ 3 ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ፣ 3 ባለሙያዎችን ደግሞ ከሥራ ማገድ እና ፍቃድ መቀማት እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን፤ የአንድ ወርና የስድስት ወር የሥራ እግድ እና የፍቃድ እግድ እንዲመልሱ መደረጉን ገልጸዋል።

በተጨማሪም አንድ ባለሙያ የአንድ ዓመት የሥራ እግድ እንደተላለፈባቸው የተናገሩት ምክትል ዳይሬክተሩ፤ ባለፉት አራት ወራት ለባለሥልጣኑ ወደ 21 የሚሆኑ የጤና ተቋማት ላይ ከሕብረተሰቡ ዘንድ ቅሬታ መቅረቡን ለገበያ ሚዲያ ተናግረዋል።

አያይዘውም፤ በከተማዋ የችግሩን መንሰራፋት ከአቤቱታ አቅራቢዎች በመረዳት በተለየ መልኩ መሰል እርምጃዎች እና የቁጥጥር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል ባለሙያዎች የሙያ ሥነ-ምግባራቸውን እንዲያከብሩና ሕብረተሰቡም መሰል ድርጊቶችን ሲያስተውል፤ ጥቆማዎችን በመሰጠት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በመላኩ ደምሰው

#ገበያ #ኢትዮጵያ

በመዲናዋ ከ200 በላይ ልዩ ልዩ የተሽከርካሪ ዕቃዎች ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) ጥናትን መሠረት በማድረግ በተከናወነ ኦፕሬሽን ከ...
17/12/2025

በመዲናዋ ከ200 በላይ ልዩ ልዩ የተሽከርካሪ ዕቃዎች ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ

ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) ጥናትን መሠረት በማድረግ በተከናወነ ኦፕሬሽን ከ200 በላይ ልዩ ልዩ የተሽከርካሪ ዕቃዎች ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

ፖሊስ በከተማዋ ከተለያዩ አካባቢዎች ተሠርቀው በሕጋዊ የንግድ ሽፋን ወደ ገበያ የሚገቡ የመኪና ዕቃዎችና ሕገ-ወጥ ነጋዴዎች ላይ ተገቢው ጥናት ሲደረግ መቆየቱን ገልጿል።

በዚህም ሦስት ተጠርጣሪዎች ሕጋዊ የንግድ ፍቃድን እንደሽፋን በመጠቀም የተሰረቁ የተሽከርካሪ እቃዎችን እየገዙ መልሰው እንደሚሸጡም በተደረገው ጥናት እንደተደረሰበት አስታውቋል።

በዚህም መሠረት የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በክ/ከተማው ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ሶማሌ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ ሦስት ግለሠቦች፤ ይህንን የወንጀል ድርጊት እንደሚፈጽሙም እንደተደረሰበት ነው የተገለጸው።

ፖሊስ የህብረተሰቡን መረጃ ተንተርሶ ባደረገው ጥናት የደረሠበትን ውጤት መነሻ በማድረግ ከፍርድ ቤት ተገቢውን የብርበራ እና የመያዣ ፈቃድ በማውጣት ባደረገው ብርበራ 97 የተለያዩ የተሽከርካሪ ስፖኪዮ፣ 97 የፊትና የኋላ መብራት፣ 11 የዝናብ መጥረጊያ፣ 13 አርማዎችና 5 ጌጅ ከሦስት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል።

ፖሊስ በተያዙት ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢውን ምርመራ የማስፋት ተግባር እያከናወነ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ በቀጣይ ክስ እንደሚያስመሠርት አመላክቷል።

የተጠቀሱት ንብረቶች የተሰረቀባቸው ሰዎች ልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ ንብረቶቻቸውን መምረጥ እንደሚችሉም ተገልጿል።

#ገበያ #ኢትዮጵያ #ወንጀል #ስርቆት

"በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ 👉 ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በጋራ ተጠቃሚነ...
17/12/2025

"በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ

👉 ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በጋራ ተጠቃሚነት በተለያዩ ዘርፎች ያሉ አጋርነቶችን ለማስፋት ቁርጠኝነታችንን ያረጋገጠ ነው ብለዋል

ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት በተከናወነው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም "ሁለቱ የጥንታዊ ሥልጣኔ ባለቤት አገራት መካከል ያለው ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነትና አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረበት ወቅት ላይ እንገኛለን" ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች ያላቸው ግንኙነት ማደጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ሕንዳውያን ባለሀብቶች በጤና ፣ በግብርና እና አምራች ዘርፎች ከ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስት በማድረግ ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

ሁለቱ ሀገራት በያሉበት አህጉር ተፅህኖ ፈጣሪ መሆናቸውን ገልጸው ለጋራ ተጠቃሚነትና ብልፅግና በስትራቴጂካዊ ትብብር በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር እንድትሆን ሕንድ ድጋፍ ማድረጓንም ጠቁመዋል።

በርካታ ኢትዮጵያዊያን በሕንድ የትምሀርት ዕድል አግኝተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአየር ንብረት ለውጥ በመከላከል፣ በጤና በግብርና፣ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ነን ብለዋል።

አዲስ ሐሳቦችን ለሚያፈልቁ የሥራ ፈጣሪ ወጣቶችና ተቋማትን መገንባትና ማበረታታት የኢትዮጵያን መጪ ዘመናት የሚቀይርና የሚወስን ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በዚህ ታላቅ ምክር ቤት ውስጥ ሕጎቻችሁ ይወጣሉ፤ እዚህ ውስጥ የሕዝቡ መሻት የመንግሥት መሻት ይሆናል ያሉ ሲሆን፤ በውይይትና ዲሞክራሲያዊ መንገድ የህግ የበላይነትን ማክበር ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተደረገላቸው የክብር አቀባበልና ለተበረከተላቸው የኢትዮጵያ ታላቁ የክብር ኒሻን ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ማመስገናቸውን ገበያ ሚዲያ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በኢትዮጵያ የሚገኙት ጠ/ሚ ናሬንድራ ሞዲ ትናንት ማምሻውን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእራት ግብዣ የተደረገላቸው ሲሆን፤ በዚህም ሥነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ ታላቁ የክብር ኒሻን ተበርክቶላቸዋል።

በዚህም ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ታሪካዊ ወዳጅነት ያላቸው ኢትዮጵያና ሕንድ በራስ አቅምና በሀገር በቀል የዕድገት መንገድ የዳበረ ኢኮኖሚ ለመገንባት አቅም ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሕንድ የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አጋር መሆኗን ያመላከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት በጋራ ተጠቃሚነት በተለያዩ ዘርፎች ያሉ አጋርነቶችን ለማስፋት ቁርጠኝነታችንን ያረጋገጠ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

አክለውም፤ ኢትዮጵያ በአምራች፣ በዲጂታል ዘርፍና ከብክለት ነጻ በሆነዉ የኃይል አማራጭ ለበርካታ ወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ መስማማታቸውን አስታውቀዋል፡፡

#ገበያ #ኢትዮጵያ #ሕንድ #ዲፕሎማሲ

የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ጅቡቲ በሚቆዩባቸው ቀናት ሕይወታቸው እያለፈ በመሆኑ ጭነት እስኪደርሳቸው ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲጠብቁ ተጠየቀ ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) የከባድ መኪና አሽ...
17/12/2025

የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ጅቡቲ በሚቆዩባቸው ቀናት ሕይወታቸው እያለፈ በመሆኑ ጭነት እስኪደርሳቸው ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲጠብቁ ተጠየቀ

ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ጭነት ለመጫን ጅቡቲ በሚቆዩባቸው ቀናት በሙቀት ሳቢያ ሕይወታቸው እያለፈ በመሆኑ፤ ጭነት እስኪደርሳቸው ኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ እንዲጠብቁ እንዲደረግ የኢትዮጵያ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማህበር ጠይቋል።

የማኅበሩ ሥራ አስፈጻሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዳንኤል ተመቸው ለገበያ ሚዲያ እንደገለጹት፤ ሙቀት ሲገባ ጭነት ባለመኖሩ አሽከርካሪዎች ተራ ደርሷቸው ለመጫን "ከ 15 ቀን እስከ 1 ወር" ይፈጅባቸዋል።

በዚህም መሃል የስኳር ሕመምተኛ፣ የደም ግፊት ሕመምተኛ፣ ሳያውቀውም የልብ ሕመም ያለበት ሰው እንዲሁም ጤነኛ ሰውን "በጣም የሚፈትን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

አሽከርካሪዎች በአካባቢው እስከ 50 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት ባለበት፣ የሙቀት ማቀዝቀዣ በሌለበት እና ባልተመቻቸ ሁኔታ እንደሚቆዩ ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ "ሰውነታቸው የመድረቅ እና ዲሃይድሬት የመሆን ሁኔታ ስለሚፈጠር” በዚህ ሁለት ዓመት ውስጥ ብቻ ወደ ስምንት አሽከርካሪዎች ሕይወታቸው አልፏል" ብለዋሌ

ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም "ይህንን ለመቀነስ ካምፓኒዎችን አሽከርካሪዎች ኢትዮጵያ ድንበር ላይ ጠብቀው ጭነት ሲደርሳቸው እንዲጭኑ ጠይቀናል" ያሉ ሲሆን፤ ለሚመለከተው አካል ማህበሩ ማመልከቱንም ለገበያ ሚዲያ አስረድተዋል።

በዚህም ይህንን ጥያቄ የተገበሩ እንደ 'ቶታል' እና 'ኦይል ሊቢያ' አይነት ካምፓኒዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፤ ኦይል ሊቢያ በሰፊው ናፍጣ እና ቤንዚን የሚጭኑ አስከርካሪዎች ላይ አሰራሩን ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ መዘግየቶችን እንዳሳየ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ከመዘግየቶች በኋላ ወረቀት እና ቀጠሮ ተሰጥቷቸው 3 ቀን ሲቀራቸው ለጭነት እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን አቶ ዳንኤል ገልጸው፤ ሌሎች ካምፓኒዎች ይህንን አሰራር ተከትለው ማለትም ኢትዮጵያ ድንበር ላይ ሹፌሩ ቆሞ ጭነቱ ሲደርስ ወደ ጅቡቲ እንዲገባ ቢደረግ "የሞት አደጋ"ን ስለሚቀንስ ተግባራዊ እንዲደረግ ጠይቀዋል፡፡

በቤተልሄም ሰለሞን

#ገበያ #ኢትዮጵያ #ጅቡቲ #ሙቀት #ጭነት

የእቴጌ ጥሩወርቅ የወርቅ የፀጉር ማስያዣ ወደ ኢትዮጵያ ሊመለስ መሆኑ ተሰማታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) እ.ኤ.አ በ1868 የእንግሊዝ ጦር ወደ መቅደላ ባደረገው ጉዞ ወቅት ከኢትዮጵያ ...
17/12/2025

የእቴጌ ጥሩወርቅ የወርቅ የፀጉር ማስያዣ ወደ ኢትዮጵያ ሊመለስ መሆኑ ተሰማ

ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) እ.ኤ.አ በ1868 የእንግሊዝ ጦር ወደ መቅደላ ባደረገው ጉዞ ወቅት ከኢትዮጵያ የተወሰደው የ19ኛው ክፍለ ዘመን የወርቅ የፀጉር ማስያዣ ከአንድ የጣሊያን የጨረታ ድርጅት ጋር በተደረገ ድርድር ወደ ኢትዮጵያ ሊመለስ መሆኑ ተሰምቷል።

ከንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ዳግማዊ ባለቤት እቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ ንብረቶች መካከል አንዱ ነው የተባለው ይህ የወርቅ የፀጉር ማስያዣ፤ ከንጉሱ ህልፈት በኋላ በእንግሊዝ ኃይሎች ከተዘረፉ በሺዎች የሚቆጠሩ ንጉሰ ነገስቱ ዕቃዎች መካከል አንዱ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ቅርሱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሰው አር ኢ ቲ (RET) በተባለ በልዑል ኤርሚያስ ሳህለ-ሥላሴ ሃይለ-ሥላሴ በተቋቋመ ድርጅት ሲሆን፤ ድርጅቱ የኢትዮጵያ ሕዝቦችን ባህላዊ፣ ትምህርታዊ እና ኢኮኖሚያዊ ደህንነት ለመጠበቅ እና ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።

የወርቅ የፀጉር ማስያዣው እ.ኤ.አ በ1868 የመቅደላ ጦርነትን ተከትሎ በእንግሊዝ ወታደሮች ከተያዙ በሺዎች ከሚቆጠሩ ቅርሶች አንዱ ሲሆን፤ በሮም ከቤርቶላሚ ፋይን አርት ጋር በተደረገው ድርድር የተገኘ ነው።

ድርድሩን የመሩት የኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ልዑል ኤርሚያስ ሳህለ-ሥላሴ ከአር ኢ ቲ የቦርድ አባል ኒኮላስ ሜሊሎ ጋር በቅርበት በመተባበር ሲሆን፤ በለጋሾች ድጋፍ ድርጅቱ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የተገኘውን በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተወሰዱ ጋሻዎች እና ሊሎች ባህላዊ ሀብቶችን መልሶ ማግኘት ችሏል።

"የወርቅ የፀጉር ማስያዣው ወደ ወደ ትውልድ ሀገሩ ለመመለስ መስራት ስንጀምር ከተባበርን ምን ልናከናውን እንደምንችል ያሳያል" ያሉት ልዑል ኤርሚያስ ሳህለ-ሥላሴ፤ "በእምነት እና በጋራ መከባበር ላይ በተመሠረተ ትብብር፣ ጉልህ የሆኑ የኢትዮጵያ ባህላዊ ሀብቶችን ማስመለስ እንችላለን" ብለዋል።

የእቴጌ ጥሩወርቅ የፀጉር ማስያዣ (ፒን) በቬልቬት በሳጥን ውስጥ ተጠብቆ የቆየ ሲሆን፤ ይህ ቅርስ የ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያውያን የተራቀቀ የእጅ ጥበብ ሥራ ብርቅዬ ምሳሌ መሆኑም ተገልጿል።

በሚሊዮን ሙሴ

#ገበያ #ኢትዮጵያ

በአማራ ክልል ወደ ገጸምድር የፈሰሰው ነዳጅ ሙሉ በሙሉ ወደላይ እንዳይወጣ በቅልጥ አለት መሸፈኑ ተግዳሮት ሆኗል ተባለታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ...
17/12/2025

በአማራ ክልል ወደ ገጸምድር የፈሰሰው ነዳጅ ሙሉ በሙሉ ወደላይ እንዳይወጣ በቅልጥ አለት መሸፈኑ ተግዳሮት ሆኗል ተባለ

ታህሳስ 08/2018 (ገበያ ሚዲያ) በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ ከሰሞኑ ወደ ገጸምድር የፈሰሰው የተፈጥሮ ነዳጅ የሚከማችበት የአለት አይነት በቅልጥ አለት መሸፈኑ፤ የተፈጥሮ ነዳጁ ሙሉ በሙሉ ወደላይ እንዳይወጣ አድርጎታል ተብሏል።

የዞኑ ማዕድን መምሪያ ኃላፊ አቶ አሕመድ አበባው ነዳጁ በወረኢሉ፣ ለገሂዳና ከለላ ወረዳዎች እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን፤ ነዳጁን ለማውጣት ከፍተኛ ቴክኖሎጂ እና የጂኦሎጂ ባለሙያ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።

ይህንን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ምድር ትምህርት የእሳተ ገሞራ መምህርና ተመራማሪ ደረጀ አያሌው (ፕ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ምላሽ፤ ነዳጁ መውጣቱን እና ከዚህ በፊትም እንደነበር ገልጸው፣ ነገር ግን አንዳንዴ ጎላ ብሎ የሚፈስበትና አንዳንዴም የሚጠፋበት ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል።

የወጣው የተፈጥሮ ነዳጅ ፍሳሽ በአካባቢው ድፍድፍ ዘይት እንዳለ የሚያሳይ መሆኑን የጠቆሙት ተመራማሪ እና መምህሩ፤ "ነገር ግን ትልቁ ችግር የተፈጥሮ ነዳጅ የሚከማችበት የአለት አይነት በቅልጥ አለት ተሸፍኗል። ያ ደግሞ የተፈጥሮ ነዳጁን ሙሉ በሙሉ ወደላይ እንዳይወጣ ያደርገዋል" ብለዋል።

አክለውም አለቱ በውስጡ ሰፊ ቀዳዳዎች ስለሌሉና ትልቁ ነዳጅ በቅልጥ አለት ስለተሸፈነ፤ ያን የግድ ቆፎሮ ማግኘት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።

ነገር ግን "ትልቁ ችግር እሱን ቆፍሮ የተፈጥሮ ነዳጅ የተከማቸበትን አካባቢ የአለት አይነት የማግኘት ነው እንጅ፤ ሌላም ሀገር እንደተለመደው ቆፎሮ ማውጣት ይቻላል" ሲሉ ገልጸዋል።

"እኛ ጋ ልዩነቱ ነዳጅ የሚፈጥረውና የሚያከማቸው የአለት አይነት በቅልጥ አለት የተሸፈነ ስለሆነ ነው፣ ግን ደግሞ በተፈጥሮ አነስተኛ እፍግታ ስላለው ወደላይ በመጠኑ ይወጣል" ያሉም ሲሆን፤ በአካባቢው ብዙ ጊዜ ሲወጣ የሚታየው ነዳጅ በቀለጠው አለት ውስጥ የሚፈስ መሆኑን አስረድተዋል። ያ የሆነው የተሰነጣጠቀ አለት ስላለ ነዳጁ የተወሰነ በዚያ ውስጥ ስለሚፈስ ነው ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው በዚህ ጉዳይ ላይ በተለያየ ጊዜ ጥናት ሰርቶ እንደነበር የገለጹት መምህርና ተመራማሪ ደረጀ አያሌው (ፕ/ር)፤ ምን ያህል ርቀት ላይ ይገኛል? መጠኑ ምን ያህል ነው? የሚለው ብዙ ዝርዝር ጥናቶች መኖራቸውን አስረድተዋል።

አክለውም ትልቁና ዋናው ቁልፍ ችግር የተፈጥሮ ነዳጁ አከማችቶ የሚይዘው አለት በቅልጥ አለት መሸፈኑ ብዙ ነገሮችን በትክክል ለማወቅ አዳጋች ማድረጉን በማንሳት፤ ነገር ግን በትንሹ ከ1 ኪሎሜትር የማያንስ ቅልጥ አለት የሸፈነ መሆኑን አብራርተዋል።

ከሰሞኑ በደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳና ወረኢሉ ወረዳዎችን በሚያዋስነው መቸላ ወንዝ አካባቢ የተፈጥሮ ነዳጅ በአለት ሰንጥቅ መውጣቱ የሚታወስ ሲሆን፤ ባለፈው ሳምንት ታህሳስ 1 ቀን 2018 ከፌዴራል እስከ ወረዳ ድረስ የተውጣጡ ከፍተኛ ባለድርሻ አካላት ቡድን በአካባቢው በመገኘት ከሚታየው ፈሳሽ ናሙና መውሰዳቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም በ2005 ዓ.ም ነዳጅ ሲያፈላልግ የነበረ ድርጅት ከፍተኛ ክምችት እንደሚገኝ አመላክቶት የነበረውን ጎራና ት/ቤት አካባቢ ከነዋሪዎች በተሰጣቸው ማብራሪያ በመነሳት በጂፒኤስ መረጃ መውሰድቸውን የለገሂዳ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን አስታውቋል።

#ገበያ #ኢትዮጵያ

መልካም ቀን!
17/12/2025

መልካም ቀን!

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gebeya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gebeya Media:

Share