Balageru TV

Balageru TV Balageru television, promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism..
(1)

Our Channel Frequency
NSS12 57 Degree East HD, Freq - 11105, Pol - Horizontal, S/R - 45000
or
DSTV Channel - 484

ሸገር ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቋል!የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሊጉ ከተባለ በኋላ 48ኛው የሸገር ደርቢ ጨዋታ ያለምንም ግብ አቻ ተጠናቋል።በአጠቃላይ በመጀመሪያው አጋማሽ  የተሻለ የጨዋታ እንቅ...
02/02/2025

ሸገር ደርቢ በአቻ ውጤት ተጠናቋል!

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሊጉ ከተባለ በኋላ 48ኛው የሸገር ደርቢ ጨዋታ ያለምንም ግብ አቻ ተጠናቋል።

በአጠቃላይ በመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ የጨዋታ እንቅስቃሴና ሙከራ ያሳዩት ፈረሰኞቹ ለባለሙያ ውሳኔ የሚተው የፍፁም ቅጣት ምት የጥፋት ጥያቄን አስከትሎ ጨዋታው ተጠናቋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ወጣቶቹን ባለተሰጥኦ ተጨዋቾች ኪሩቤል ደሳለኝና ሚኪያስ ፀጋዬን ቀይረው ያስገቡት ኢትዮጵያ ቡናዎች በበረከት ወልዴ ጉዳት የሳሳውን የመሀል ክፍል በመቆጣጠር የተሻለ የጎል እድል መፍጠር ችለዋል።

የጨዋታውን አጠቃላይ እንቅስቃሴና ብዙ መልኮች የነበሩትን ጨዋታና የታክቲክ ፍልሚያ በመደበኛ የባላገሩ ሜዳ ፕሮግራም በዝርዝር እናቀርባለን።

ባላገሩ ስፖርት

ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ(ባላገሩ ቴሌቪዥን ጥር 25፣ 2017ዓ.ም)ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/...
02/02/2025

ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ጥር 25፣ 2017ዓ.ም)

ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ከፍተኛ በሆነ ድምጽ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶች አድርጎ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መምረጡን የፓርቲው ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።

ሁለቱ ምክትል ፕሬዚዳንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ መፈጸማቸውም ተገልጿል።

ፕሪሚየር ሊግ ሳይባል በፊት የሸገር ደርቢ እውነታዎች!(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም)⚽️ ለመጀመርያ ጊዜ ሁለቱ የአዲስ አበባ ክለቦች የተገናኙት በ1975 ዓም  ጥር 11 ነ...
01/02/2025

ፕሪሚየር ሊግ ሳይባል በፊት የሸገር ደርቢ እውነታዎች!

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም)

⚽️ ለመጀመርያ ጊዜ ሁለቱ የአዲስ አበባ ክለቦች የተገናኙት በ1975 ዓም ጥር 11 ነው። ጨዋታውን የኢትዮጵያ ቡና 2ለ 1 አሸንፏል።

⚽️ በዋንጫ ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኙት በታችኛው ሁለተኛ ዲቪዚዮን እያሉ የኢትዮጵያ ቡና በደርሶ መልስ ጨዋታ 2ለ1 አሸንፏል።

⚽️ በ1977 በዋናው ዲቪዚዮን ተገናኝተው ቅዱስ ጊዮርጊስ አሸንፎ ዋንጫ አንስቷል።

⚽️ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ሁለቱ ክለቦት የተጨዋቾች ዝውውር የተካሄደው በ1978 ዓ.ም ብርሀኑ ገብረማርያም ነው ከፈረሰኞቹ ወደ ቡናማዎቹ ሄዷል።

⚽️ የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ሆኖ እስካሁን ቅዱስ ጊዮርጊስን ያሰለጠነ ማንም የለም ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫውቶ የኢትዮጵያ ቡናን ያሰለጠኑት ገብረመድንና ስዩም ናቸው ።

⚽️ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለቱም ጋር ተጫውቶ ዋንጫ ያሳካው ቴዎድሮስ ቦካንዴ ነው ።በጥሎ ማለፍ በ1990 ዓም ኢትዮጵያ ቡና እየተጫወተ ጊዮርጊስን አሸንፎ ፤ በ1991 ደግሞ ለፈረሰኞቹ እየተጫወተ ኢትዮጵያ ቡናን አሸንፎ ዋንጫ አሳክቷል።

⚽️ የማይረሱ ብዙ ጎል የተቆጠረባቸው ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ 1996 5_0 አሸንፏል።በ986 ዓም ኢትዮጵያ ቡና 5_3 አሸንፏል ።

ከገነነ መኩሪያ ሊብሮ ማህደር ለባላገሩ ስፖርት ። መልካም ጨዋታ ተመኘን!

ባላገሩ ስፖርት

ታላቁ የሸገር ደርቢ ቁጥራዊ እውነታዎች!(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም)⚽️ ሁለቱ የሸገር ደርቢ ተፋላሚዎች በተለያየ ዘመን ፕሪምየር ሊጉን ተቀላቅለዋል፡፡  ኢትዮጵያ ቡና በ...
01/02/2025

ታላቁ የሸገር ደርቢ ቁጥራዊ እውነታዎች!

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም)

⚽️ ሁለቱ የሸገር ደርቢ ተፋላሚዎች በተለያየ ዘመን ፕሪምየር ሊጉን ተቀላቅለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና በ1990 ቅዱስ ጊዮርጊስ በ1991 የሊጉን ጅማሮ አድርገዋል፡፡ የፕሪምየር ሊግ ቆይታ ኢትዮጵያ ቡና 27 ዓመት- ቅዱስ ጊዮርጊስ 26 ዓመት አስቆጥረዋል፡፡

⚽️ የፕሪሚየር ሊግ የእርስ በርስ ግንኙነት --- 47። ሸገር ደርቢ በደቂቃ ሲለካ- 4230 ደቂቃ። ጊዮርጊስ ያሸነፈው ---22 ።ኢትዮጵያ ቡና ማሸነፍ የቻለው ------8። የአቻ ውጤት -17።

⚽️ቅዱስ ጊዮርጊስ ያስቆጠረው ጎል 61። ኢትዮጵያ ቡና ያስቆጠረው 27 በድምሩ 88 ጎሎች በሸገር ደርቢ ተቆጥረዋል።
በአማካይ 1.8 ጎል ከመረብ አርፈዋል ማለት ነው፡፡

⚽️ያለ ጎል በአቻ ውጤት የተጠናቀቀ ጨዋታ 10 (የኢትዮጵያ ሪከርድ) ለ900 ደቂቃ ጎል ያልተቆጠረበት የደርቢ ጨዋታ በመባል ይታወቃል።

⚽️ኢትዮጵያ ቡና በ26 የሸገር ደርቢ ጨዋታ ጎል አላስቆጠረም። ቅዱስ ጊዮርጊስ ጎል ያላስቆጠረበት ጨዋታ 15።ሁለቱ ቡድኖች 5 ግዜ አንድ አቻ እንዲሁም 2 ግዜ ሁለት አቻ ፣10 ግዜ 0ለ0 ተለያይተዋል፡፡

⚽️ለመጨረሻ ግዜ ሁለት አቻ የተለያዩት በ1996 በ2ኛው ዙር ጨዋታ ነው።በሸገር ደርቢ በርካታ ጎል የተቆጠረው -- በ1997 /የተቆጠረው ጎል 7 /።

⚽️ለመጨረሻ ግዜ ጊዮርጊስ ደርቢውን ያሸነፈው በ2014 /2ኛው ዙር/።ኢትዮጵያ ቡና አንድ ግዜ (1993)፣ጊዮርጊስ ደግሞ 7 ግዜ በሁለቱም ዙር አሸንፈዋል።

⚽️በመጨረሻዎቹ አራት ግንኙነቶች ወይም ለ360 ደቂቃ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ቡናን አላሸነፈም።ጊዮርጊስ ባለፉት 26 ዓመታት አራት ግዜ በ4 ጎል ልዩነት አሸንፏል።

⚽️ኢትዮጵያ ቡና ባለፉት 26 ዓመታት በሰፋ ጎል ያሸነፈው በ2013 ዓ.ም ነው ውጤቱም 3ለ2 ነበር።

⚽️ በሸገር ደርቢ ታሪክ በፕሪሚየር ሊግ ሃትሪክ የሰራ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ቡና ተጨዋች አቡበከር ናስር ነው።

⚽️በ26 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ቡና አንድ ግዜ ጊዮርጊስ 16 ግዜ ሻምፒዮን ሆነዋል። በሸገር ደርቢ ታሪክ በቀይ ካርድ ከሜዳ የወጣው የመጀመሪያው ተጨዋች ከፍያለው ተስፋዬ /ዲላ/ ከጊዮርጊስ።

⚽️ብዙ ቀይ ካርድ የተመዘገበበት ጨዋታ በ1995 የ2ኛው ዙር ጨዋታ ሲሆን 4 ቀይ ካርድ ተመዞበታል በፕሪምየር ሊግ ዘመን ጊዮርጊስ በ10 ኢትዮጵያ ቡና በ5 የውጭ ሃገር አሰልጣኝ ተመርተዋል፡፡

⚽️ ሸገር ደርቢ ከአዲስ አበባ ከራቀ 4 ዓመት አስቆጥሯል።

ጋዜጠኛ ጥሩነህ ካሳ ለባላገሩ ስፖርት

በዜናዎቻችን ከተካተቱ የዕለቱ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ Balageru TV✅  ኢትዮጵያዊቷ ለጨረታ ቀረበች✅  የኤርትራው መሪ ስለ ህብረቱ✅  የህክምና ባለሙያዎች እስር ✅  ብሪክስና የትራም...
31/01/2025

በዜናዎቻችን ከተካተቱ የዕለቱ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ Balageru TV

✅ ኢትዮጵያዊቷ ለጨረታ ቀረበች
✅ የኤርትራው መሪ ስለ ህብረቱ
✅ የህክምና ባለሙያዎች እስር
✅ ብሪክስና የትራምፕ ዛቻ
እሸት እሸት መረጃዎችን ለማግኘት ፤ በጥበብና በተሰጥዖ ለመርካት፤
• የድረገፅ | https://www.balagerutv.com/
• የዩቲዩብ | https://www.youtube.com/c/BalageruTV?sub_confirmation=1
• የፌስቡክ | https://www.facebook.com/tvbalageru
• የኢንስታግራም | https://www.instagram.com/balageru.tv/
• የቲክቶክ | https://www.tiktok.com/
• የቴሌግራም | https://t.me/BalageruTv_OfficialChannel
• የቲውተር |
ገፆቻችንን ሼርና ላይክ በማድረግ ይጎብኙን፡፡ ባለ ሃገር ሆነው ከባላገሩ ጋር አብረውን ስላሉ እናመሰግናለን፡፡
አስተያየታችሁንም በአጭር የስልክ መስመራችን 7544 ማስተላለፍ አይርሱ፡፡
ነቃ ነቃ!!!
https://youtu.be/DVjTkoEKLtU

በዜናዎቻችን ከተካተቱ የዕለቱ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ ✅ ኢትዮጵያዊቷ ለጨረታ ቀረበች✅ የኤርትራው መሪ ስለ ህብረቱ✅ የህክምና ባለሙያዎች እስር ✅ ብሪክስና የትራምፕ ዛቻ .እሸት እ...

ትክክለኛ ውጤት ይሞክሩ ፤ ተሻላሚ ይሁኑ !!!በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂውን የሸገር ደርቢ ጨዋታ በመገመት ተሻላሚ ይሁኑ !!!ውጤቱን በትክክል ለገመቱ የመጀመሪያ አምስት የባላገሩ ቤተሰ...
31/01/2025

ትክክለኛ ውጤት ይሞክሩ ፤ ተሻላሚ ይሁኑ !!!

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂውን የሸገር ደርቢ ጨዋታ በመገመት ተሻላሚ ይሁኑ !!!

ውጤቱን በትክክል ለገመቱ የመጀመሪያ አምስት የባላገሩ ቤተሰቦች ሽልማት እናበረክታለን

ለሁለቱም ቡድኖች ባላገሩ ሜዳ መልካም እድልን ይመኛል፡፡
እሸት እሸት መረጃዎችን ለማግኘት ፤ በጥበብና በተሰጥዖ ለመርካት፤
• የድረገፅ | https://www.balagerutv.com/
• የዩቲዩብ | https://www.youtube.com/c/BalageruTV?sub_confirmation=1
• የፌስቡክ | https://www.facebook.com/tvbalageru
• የኢንስታግራም | https://www.instagram.com/balageru.tv/
• የቲክቶክ | https://www.tiktok.com/
• የቴሌግራም | https://t.me/BalageruTv_OfficialChannel
• የቲውተር |
ገፆቻችንን ሼርና ላይክ በማድረግ ይጎብኙን፡፡ ባለ ሃገር ሆነው ከባላገሩ ጋር አብረውን ስላሉ እናመሰግናለን፡፡
አስተያየታችሁንም በአጭር የስልክ መስመራችን 7544 ማስተላለፍ አይርሱ፡፡
ነቃ ነቃ!!!

የደርቢውን ጨዋታ በቀጥታ ስርጭት ይመልከቱ!(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም)በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተወዳጁ የሸገር ደርቢ እግር ኳስ ፍልሚያ በሱፐር ስፖርት የቀጥታ ስርጭት ...
31/01/2025

የደርቢውን ጨዋታ በቀጥታ ስርጭት ይመልከቱ!

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም)

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተወዳጁ የሸገር ደርቢ እግር ኳስ ፍልሚያ በሱፐር ስፖርት የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል።

በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የገቡት በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝና ረዳቶቹ የሚመሩት ፈረሰኞቹ በአዲሱ ትውልዳቸው አስደናቂ ጉዞ ወሳኙን ጨዋታ ያደርጋሉ።

ቡናማዎቹ አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬና ረዳቶቹ እየተመሩ ከተከታታይ ነጥብ ከመጣል በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሰው በስነ ልቦና ከፍ ብለው የሚመጡበት ጨዋታ ነው።

ዋና አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ከነፃነት ክብሬ ፣ ረዳት አሰልጣኝ ሳምሶን ሙልጌታ ከ አብይ ካሳሁን ፣ የጀርባ አጥንቶቹ ሌጀንዶች አዳነ ግርማ ከ ታፈሰ ተስፋዬ .....። ማን ያሸንፋል ግምታችውን አእንድትፅፉ ጋብዘናል።

ባላገሩ ስፖርት

የዓለማችን ውዷ ሴት እግር ኳስ ተጨዋች ናኦሚን ግርማ ለቢቢሲ ስለ ኢትዮጵያ ሀሳቧን አካፍላለች። (ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም)ከሰሜን አሜሪካ ሳንዲያጎ ዌቭ ወደ  ምዕራብ ...
30/01/2025

የዓለማችን ውዷ ሴት እግር ኳስ ተጨዋች ናኦሚን ግርማ ለቢቢሲ
ስለ ኢትዮጵያ ሀሳቧን አካፍላለች።

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም)

ከሰሜን አሜሪካ ሳንዲያጎ ዌቭ ወደ ምዕራብ ለንደኑ ቼልሲ ክለብ በ1ሚ ፖውንድ ዝውውር ማድረጓን ተከትሎ ቢቢሲ ስፖርት ስለ ናኦሚን ግርማ ማወቅ ያለብን ጠቃሚ አምስት ነገሮች በማለት ዘገባ ሰርቷል። ከአምስቱ ውስጥ ዋናው ስኢትዮጵያና ወላጆቿ የተናገረችው ነው።

የ24 ዓመቷ ናኦሚን ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ በተጓዙ ወላጆች ነው የተገኘችው ። አባቷ አቶ ግርማ አወቀ ጦርነት ሽሽት በስደትን አሜሪካ ገብቶ :እናቷ ሰብለ ደምሴ ለተሻለ ትምህርት አሜሪካ መጥታ ነው የተዋወቁት።

እኔ የተገኘውበትን ማህበረሰብ እወዳለው እኮራለውም ለብዙዎች አርአያ መሆን እፈልጋለው በተለየ በአሜሪካ ለሚወለዱ አዲሱ ትውልድ ስትል ትናገራለች በካሊፎርኒያ ሳን ሆሴ ተወልዳና አድጋ እንግሊዘኛና አማርኛ አቀላጥፋ የምትናገረው ናኦሚን ግርማ ።

ዝነኛዋ የአሜሪካ ሌጀንድ ተጨዋች አሌክስ ሞርጋን በህይወቴ ካየኋቸው ምርጥ የመሀል ተከላካይ ተጨዋቾች አንዷ በማለት የመሰከረችላት ናኦሚን :- እኔ ላሁኑ ማንነቴ የኢትዮጵያ ባህል ፣ምግብ ፣ ቋንቋ ሁሉም ነገር ትልቅ ቦታ በህይወት አላቸውም ትላለች።

እኛ ኢትዮጵያውያን በሳን ሆሴ ውስጥ አንድ ትልቅ ማህበረሰብ ነን በወላጆቼ በመጡበት ቦታ በጣም እኮራለው ይህ ለኔ በጣም አስፈላጊ ነው።እዚህ ያሉ አዲሱ ትውልዶች እንደኔ የሚፈልጉትን እንዲያሳኩ አርዓያ መሆን አለብኝ ትላለች ።

የአባቷን እግር እተከተለች በሰሜን አሜሪካ በመሰረተው ማለዳ የእግር ኳስ ፕሮጀክት ኳስን መጫወት የጀመረችው ናኦሚን ወላጅ አባቷ መነሻ እንደሆናት መስክራለች።

ናኦሚን ግርማ ለቢቢሲ ስለ አሌክስ ሞርጋን ፣ስለ ቡድን ጓደኛዋ፣ የልጅነት ጊዜዋና ስለ ህልሟ በርካታ ሀሳቧን ተናግራለች ...።

ባላገሩ ስፖርት

በህንድ ኦርቶዶክስ ሀገረ ስብከት የሜትሮፖሊታን ጳጳስ ገቫርጌሰ ዩልዮስ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኢትዮ ኢስታምቡል ሆስፒታልን ዛሬ ጎበኙ (ባላገሩ ቴሌቪዥን፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም)ብፁዕ...
30/01/2025

በህንድ ኦርቶዶክስ ሀገረ ስብከት የሜትሮፖሊታን ጳጳስ ገቫርጌሰ ዩልዮስ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኢትዮ ኢስታምቡል ሆስፒታልን ዛሬ ጎበኙ

(ባላገሩ ቴሌቪዥን፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም)

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቴዎስ ሣልሳዊ የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ መልዕክተኛ የልዑካን ቡድን ሜትሮ ፖሊታን ማር ዩልዮስና ፋዘር ጆሲ ጃኮብ በኢትዮጵያ እያደረጉ ያሉትን ጉብኝት ቀጥለዉ በዛሬዉ እለት የኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።

አቶ ብርሃን ተድላ ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈፃሚ በጉብኝቱ መርሐግብር ወቅት ለመገናኛ ብዙሃን እንደተናገሩት ከሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጋር መቀራረቡ በተለይ ከፍተኛ ሕክምናዎችን በሀገር ውስጥ ለማድረግ ሆስፒታሉ ያለውን ራዕይ ለማሳካት የሚረዳ ነው።

ሆስፒታሉ በቴክኖሎጂ በታገዙ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችና ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ ስፔሻሊስትና ሰብ-ስፔሻሊስት ባለሙያዎች በመታገዝ ዜጎቻችንን ለህክምና ወደ ውጭ አገር በመሄድ የሚያወጡትን ከፍተኛ ወጪና እንግልት ለማስቀረት እና ውጭ አገር የሚያስኬዱ ሕክምናዎችን በሀገር ውስጥ ለመስጠት አላማው አድርጎ የተነሳ በዋናነት በአዋቂና በህፃናት የልብ ቀዶ ህክምና ላይ የተሰማራ የሕክምና ተቋም ስለመኾኑ አብራርተዋል።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ብርሃን ተድላ በበኩላቸው የጳጳሱ ጉብኝት በኢትዮጵያ በተለይ በልብ ህመም ወረፋ እየጠበቁ ያሉ ህፃናትን ህንድ ሄደው እንዲታከሙ አልያም የህንድ ዶክተሮች እዚህ መጥተው ቀዶ ጥገና እንዲያደርጉ እገዛ ያደርጋል ብለዋል።
ሆስፒታላቸው ከ ሰላሳ ስድስት ሚልየን ብር በላይ ወጪ አውጥቶ ለ አርባ ህፃናት የልብ ህምምተኞ ህክምና እንዳደረገ ተናግረው በማሽን እና በባለሙያ እጥረት ህክምና ላላገኙ ሰዎች እንደ ህንድ ካሉ ሀገራት ጋር የህክምና አገልግሎት ልምድ መለዋወጥ እንዲሁም ድጋፍ ማግኘት ትልቅ ጥቅም አለው ብፅዕነታቸው ሆስፒታሉን ስለጎበኙና ድጋፍ ለማድረግ ቃል ስለገቡ እናመሰግናለን ብለዋል።

ኢትዮ ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል በዋናነት በአዋቂና በሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና በተጨማሪም የደረትና የሳንባ ቀዶ ሕክምና፣ የጭንቅላትና ኅብለ ሰረሰር ሕክምና፣ የነርስ ሕክምና፣ የኩላሊት እጥበትና ሕክምና የአጥንት ቀዶ ሕክምና እየሰጠ ይገኛል ።

ጤና ይስጥልኝ ይህ ሸገር ደርቢ ነው!(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓም)በኢትዮጵያ ትልቅ ከሆኑት የእግር ኳስ ፍልሚያዎች የሸገር ደርቢ የፊታችን እሁድ ይጠበቃል። በቅርብ አመታት...
30/01/2025

ጤና ይስጥልኝ ይህ ሸገር ደርቢ ነው!

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ ጥር 22 ቀን 2017 ዓም)

በኢትዮጵያ ትልቅ ከሆኑት የእግር ኳስ ፍልሚያዎች የሸገር ደርቢ የፊታችን እሁድ ይጠበቃል። በቅርብ አመታት በከተማቸው አልተጫወቱም ስደተኛ የሆነው የደርቢ ጨዋታ አሁንም በአዳማ ይደረጋል።

የሸገር ደርቢ የጨዋታ መዳረሻ ቁጥራዊ መረጃዎች ፣አይረሴ የጨዋታ ትዝታዎች፣የተጨዋቾች ንፅፅር ፣የዝውውር ታሪኮቻቸውና ወቅታዊ አቋማቸውን በተከታታይ አጫጭር መረጃዎች እናቀርባለን ።
የተከበራችሁ የእግር ኳስ ቤተሰቦች የማትረሱትን ትዝታችውን በፎቶ አስደግፋችው ፃፋልን የተመረጡትን እናቀርባለን።

ሁለቱ ቡድኖች በፕሪሚየር ሊጉ የተገናኙት በኢትዮጵያ በ1991 ዓ.ም ነበር ።ጨዋታውን ቅዱስ ጊዮርጊስ አራት ለአንድ አሸንፏል።
ለመጀመርያ ግዜ የተፋለሙት በ1975 በጥር ወር ነበር ጨዋታውን ኢትዮጵያ ቡና ሁለት ለአንድ አሸንፏል.። ይቀጥላል...


ባላገሩ ስፖርት

አዋሽ ባንክ የ''ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊዎችን ሸለመ።(ባላገሩ ቴሌቪዥን ጥር 20,2017ዓ.ም) አዋሽ ባንክ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ...
28/01/2025

አዋሽ ባንክ የ''ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊዎችን ሸለመ።

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ጥር 20,2017ዓ.ም)

አዋሽ ባንክ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ለሁለተኛ ጊዜ ሲያካሂድ የነበረውን 2ኛው ምዕራፍ የ''ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር የማጠቃለያ መርሃ ግብር አካሂዷል።

የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው
መርሐግብሩን በንግግር በከፈቱት ወቅት እንደገለጹት
በዛሬው እለት የ''ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር ፍጻሜ ላይ ለሚደርሱ እና በዳኞች ውሳኔ መሰረት ከ1ኛ እስከ 5ኛ ደረጃ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች ከ200 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት የሚበረከትላቸው ሲሆን በተጨማሪም ፕሮጀክታቸውን እውን የሚያደርጉበት እስከ ብር 5 ሚሊዮን ብድር ያለዋስትና እንደ የፕሮጀክታቸው ሁኔታ እንደሚመቻችላቸው ገልጸዋል።

ለእንደኛው ምዕራፍ የስራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊዎች ባንኩ በገባው ቃል መሰረት አሸናፊዎቹ የተመቻቸላቸውን ከዋስትና ነፃ የሆነ ብድር በመጠቀም በአሁን ወቅት ፕሮጀክታቸውን ወደ ተግባር በመቀየር አመርቂ ውጤት እያስመዘገቡ እንደሚገኙ እና ለዚህም ባንኩ የግንኙነት ስራ አስኪያጆችን (Relationship Managers) መድቦ ተገቢው ክትትልና ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል።

''አሁን የምንጫወተው ሊጉ ይኑር በማለት እንጂ የኛ ሜዳዎች አስቸጋሪ ናቸው::'' አቶ ክፍሌ ሰይፈ (ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 20 ቀን 2017 ዓ.ም)የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ይኑር በማለት እ...
28/01/2025

''አሁን የምንጫወተው ሊጉ ይኑር በማለት እንጂ የኛ ሜዳዎች አስቸጋሪ ናቸው::'' አቶ ክፍሌ ሰይፈ

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 20 ቀን 2017 ዓ.ም)

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ይኑር በማለት እንጂ የምንጫወተው ሜዳ አስቸጋሪ እንደሆነ አቶ ክፍሌ ሰይፈ የሊግ አክሲዮን ማህበሩ ስራ አስኪያጅ ተናገሩ ።

በመጫወቻ ሜዳ ችግር የእግር ኳስ ተጨዋቾች ክህሎታቸውን አውጥተው ማሳየት በጣም ይከብዳቸዋል። በዚህ ሁኔታ የተሻለ ብሄራዊ ቡድን ለመፍጠር ከባድ ነው ሲሉ አቶ ክፍሌ በአዳማ በነበረው የእጣ ማውጣት መርሀ ግብር ተናግረዋል።

በክለብ ላይሰንሲግ ደረጃቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማቶችና አደረጃጀት ሲኖር ሁኔታው ይቀየራል ያሉት አቶ ክፍሌ በ2029 እ.ኤ.አ የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተዘጋጀ ሁኔታዎች እንደሚለውጡ ያላቸውን ሀሳብ አብራርተዋል ።

ከተሳካ የዛሬ ስድስትና ሰባት አመት የሜዳ ችግር አለብን የሚሉ ምክኒያቶች ይጠፋሉ የሚል ተስፋ አለኝ። በትንሹ ስድስት ስታዲየሞች ሁለት የልምምድ ሜዳዎች ቢኖሩት ነገሮች ተለውጠው የኢትዮጵያ እግር ኳስ አድጎ በአለም አቀፍ ደረጃ ወደፊት ተወዳዳሪ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል።

እኛ ለሁሉም ክለብ እኩል ነን በፍትሀዊነት እንሰራለን ያሉት አቶ ክፍሌ መሰረታዊ ለውጥ በኢትዮጵያ እግር ኳስ እንዲመጣ እንፈልጋለን ለዚህም እንደሚሰሩ በአፅንኦት ተናግረዋል ።

ባላገሩ ስፖርት

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በበቃ እርሻ ላይ የታፈሱ ወጣቶች በግዳጅ ይሰማሩበታል በሚል  የቀረበበትን ክስ "ሐሰት"ሲል አስተባበለ።(ባላገሩ ቴሌቪዥን ጥር 20,2017ዓ.ም)ድርጅቱ በቅርቡ ወ...
28/01/2025

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በበቃ እርሻ ላይ የታፈሱ ወጣቶች በግዳጅ ይሰማሩበታል በሚል የቀረበበትን ክስ "ሐሰት"ሲል አስተባበለ።

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ጥር 20,2017ዓ.ም)

ድርጅቱ በቅርቡ ወደ በበቃ ቡና እርሻ ታዳጊዎች እየተወሰዱ ነው በሚል የቀረበው ዘገባ "እጅግ ከእውነት የራቀና የተቋሙን መልካም ገፅታ የሚያጠለሽ" ብሎታል።

"በእርሻ ቦታው ስራ ለማሰራት ነው እንኳን እንዳይባል ይህ ወቅት የቡና ለቀማ ጊዜ እንዳልሆነ የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆኑ ማንኛውም ለዘርፉ ትንሽ ቀረብ የሚል ሰው በሚገባ ይገነዘበዋል"

ያለው ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የዜጎችን ክብር፥ ደህንነትና እድገት በማንኛውም ሁኔታ ከፍ ለማድረግ በሁሉም ድርጅቶቹ ብቻ ሳይሆን በሃገር አቀፍ ደረጃም ጭምር በሚያደርጋቸው አበርክቶዎቹና ሰው ተኮር ስራዎቹ ማረጋገጥ የቻለ ተቋም ነው ብሏል።

ሀዋሳ ከተማ የሊጉን ቀጣይ ጨዋታዎች ታስተናግዳለች!ሊጉ ወደ አዲስ አበባ አይመጣም !(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም)የኢትዮጵያ  ፕሪሚየር ሊግ 2ተኛ ዙር የእጣ ማውጣት መርሃ...
27/01/2025

ሀዋሳ ከተማ የሊጉን ቀጣይ ጨዋታዎች ታስተናግዳለች!

ሊጉ ወደ አዲስ አበባ አይመጣም !

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም)

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2ተኛ ዙር የእጣ ማውጣት መርሃ ግብር ዛሬ በአዳማ ከተማ ሲከናወን የቀጣይ ውድድር ከተማም ተለይቷል ።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ዘንድሮ 18 መሆናቸውን ተከትሎና ተስተካካይ ጨዋታችን ለማስቀረት የ2ኛውን ዙር አዲስ የእጣ ማውጣት ስነ ስርአት እንደተደረገም ሊግ አክሲዮን ማህበሩ አስታውቋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም የሁለተኛውን ዙር የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ለማስተናገድም ውድድር የሚደረግበትን ቀድሞ የመጫወቻ ሳሩን በመለወጥ በአዲስ አፈርና በአዲስ ሳር ሙሉ በሙሉ እንደተለወጠ ለማወቅ ተችሏል ።

በስታዲየሙ ዙሪያ፣ የመልበሻ ክፍሉን ማሻሻልና የልምምድ ሜዳዎችን በተሻለ ጥራት ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑም ተነግሯል።

የሊግ አክሲዮን ማህበሩ የዘንድሮ ጨዋታዎችን በአዲስ አበባ ለማድርግ ያደረገው ጥረት በመጨረሻ እንዳልተሳካም ታውቋል።

ባላገሩ ስፖርት

በዜናዎቻችን ከተካተቱ የዕለቱ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ ✅  የት/ቤቶች ውድመት✅  የአየር አምቡላንስ በኢትዮጵያ✅  የጋዛ ነዋሪዎች ጥያቄ✅  የሶማሊያና ግብጽ ስምምነት እሸት እሸት መረጃዎች...
27/01/2025

በዜናዎቻችን ከተካተቱ የዕለቱ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦

✅ የት/ቤቶች ውድመት
✅ የአየር አምቡላንስ በኢትዮጵያ
✅ የጋዛ ነዋሪዎች ጥያቄ
✅ የሶማሊያና ግብጽ ስምምነት
እሸት እሸት መረጃዎችን ለማግኘት ፤ በጥበብና በተሰጥዖ ለመርካት፤
• የድረገፅ | https://www.balagerutv.com/
• የዩቲዩብ | https://www.youtube.com/c/BalageruTV?sub_confirmation=1
• የፌስቡክ | https://www.facebook.com/tvbalageru
• የኢንስታግራም | https://www.instagram.com/balageru.tv/
• የቲክቶክ | https://www.tiktok.com/
• የቴሌግራም | https://t.me/BalageruTv_OfficialChannel
• የቲውተር |
ገፆቻችንን ሼርና ላይክ በማድረግ ይጎብኙን፡፡ ባለ ሃገር ሆነው ከባላገሩ ጋር አብረውን ስላሉ እናመሰግናለን፡፡
አስተያየታችሁንም በአጭር የስልክ መስመራችን 7544 ማስተላለፍ አይርሱ፡፡
ነቃ ነቃ!!!
https://youtu.be/PniN60azTVQ?si=a_BkcjBDCvSxGUDi

በዜናዎቻችን ከተካተቱ የዕለቱ ዐበይት ጉዳዮች መካከል ፦ ✅ የት/ቤቶች ውድመት✅ የአየር አምቡላንስ በኢትዮጵያ✅ የጋዛ ነዋሪዎች ጥያቄ✅ የሶማሊያና ግብጽ ስምምነት .እሸት እሸት መረጃ....

የመሬት መንቀጥቀጥ!በአዲስ አበባና በሊሎችም ከተሞች ከፍተኛ ንዝረት ያስከተለ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።ዛሬ ቀን 19/2017 ዓ.ም 4:38 ደቂቃ ላይ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ  ...
27/01/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ!

በአዲስ አበባና በሊሎችም ከተሞች ከፍተኛ ንዝረት ያስከተለ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ዛሬ ቀን 19/2017 ዓ.ም 4:38 ደቂቃ ላይ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል።

ባላገሩ ቴሌቪዥን

25/01/2025

ሰሜን አሜሪካ DMV በታሪኩና ጓደኞቹ የሚዘጋጀው ዓመታዊ የስፖርት ባለውለተኞች የምስጋና መርሀ ግብር ዘንድሮ ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚዘጋጅ ታውቋል። Balageru TV

በዋሽንግተን ታላላቆቹ የስፖርት ሰዎች እውቅና ሊሰጣቸው ነው!(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም)ሰሜን አሜሪካ DMV አካባቢ በታሪኩና ጓደኞቹ የሚዘጋጀው ዓመታዊ የስፖርት ባለውለ...
25/01/2025

በዋሽንግተን ታላላቆቹ የስፖርት ሰዎች እውቅና ሊሰጣቸው ነው!

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም)

ሰሜን አሜሪካ DMV አካባቢ በታሪኩና ጓደኞቹ የሚዘጋጀው ዓመታዊ የስፖርት ባለውለተኞች የምስጋና መርሀ ግብር ዘንድሮ ለሶስተኛ ጊዜ እንደሚዘጋጅ ታውቋል።

አዘጋጆቹ ለባላገሩ ስፖርት እንዳሳወቁት የ3ኛ አመት ዝግጅቱ በፈረንጆቹ አቆጣጠር መጪው ግንቦት 24- 25 ቀን ይካሄዳል።

በሰሜን አሜሪካ ታሪኩና ጎደኞቹ በመጀመሪያ ዓመቱ የእውቅና ዝግጅት ዝነኛው ሙልጌታ ወልደየስን ፣በሁለተኛው ዓመት የ3ኛው አፍሪካ ዋንጫ ባለታሪኮቹ አንጋፋዎቹ ፍስሀ ወልደ አማኑኤልና ሸዋንግዛው አጎናፍርን የምስጋና እውቅና መስጠታቸው ይታወሳል።

በዘንድሮ ዓመት በግንቦቱ ዝግጅት አለማየሁ ሀይለስላሴ ፊኛ፣ ካሳሁን ተካ፣ ፍቃዱ ፎሌና ሙልጌታ ብርሀኔ ለሀገር ላበረከቱት አስተዋፅኦና ውለታ የምስጋና እውቅና እንደሚሰጣቸው ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ከስድስት በላይ በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ የጤና ቡድኖች ለዝግጅቱ ድምቀት የእግር ኳስ ውድድር እንደሚያደርጉም ለማወቅ ተችሏል።

ባላገሩ ስፖርት

Address

Lancha Infront Of Global Hotel Meaza Desalegn Building 14th Floor
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 11:30
Friday 02:30 - 01:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Balageru TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Balageru TV:

Videos

Share

Category

Balageru TV

Balageru television, Television programming that promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism, current affairs, sports, and entertainment.