12/01/2026
አንድ ቀን የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ከቢሮው ወጣ ሲል፣ አንዲት ምግብ አቅራቢ ወጣት በላብ ተጠምቃና ዝልፍልፍ ብላ ከቢሮው ደጃፍ አጠገብ ወድቃ ተመለከተ።
ደንግጦም ወደ እርሷ ጠጋ አለና፤ "እመቤቴ፣ ደህና ነሽ? ምን ሆንሽ?" አላት ወደ ላይ ቀና እያደረጋት።
ወጣቷም ትንፋሽ እያጠራት፤ "ጌታዬ... እባክዎን ይሄ 35ኛው ፎቅ ነው?" ስትል ጠየቀችው።
እሱም በመገረም "አይደለም፣ ይሄ 30ኛው ፎቅ ነው። ቆይ ግን... 30 ፎቅ ድረስ በደረጃ ነው የወጣሽው?" አላት።
እሷም "አዎ ጌታዬ፤ በአስቸኳይ 35ኛው ፎቅ መድረስ አለብኝ። የህንጻው ሊፍት ብልሽት ስላለበት ለሰራተኞች ብቻ ነው የተፈቀደው። ይህ ምግብ የታዘዘለት ሰውዬ 'በአምስት ደቂቃ ውስጥ ካላመጣሽልኝ ከስራሽ እንዲያባርሩሽ አደርጋለሁ' ብሎ ዝቶብኛል። ወርደው እንዲቀበሉኝ ብማጸናቸውም ፈቃደኛ አልሆኑም" አለችው።
አለቃውም የታዘዘውን ሰው ስም ሲመለከት 'ሚስተር ኮስቢ' የሚል ነበር። በሁኔታው በጣም ተቆጣ። ምግቡን ከወጣቷ ተቀብሎ በቀጥታ ወደ 35ኛው ፎቅ ወጣ። ወደ ሚስተር ኮስቢ ቢሮ ዘልቆ በመግባት ምግቡን በጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው።
ሚስተር ኮስቢ በድንጋጤ ተነስቶ "ጌታዬ! እርስዎ ምግቡን ለምን አመጡት?" ሲል ጠየቀ።
አለቃውም በቁጣ አይን እያየው "አይዞህ... መጀመሪያ ምግብህን ብላ፤ ከዚያም እቃህን ጠቅልለህ ከዚህ ድርጅት ውጣ!" አለው።
ሚስተር ኮስቢ ግራ በመጋባት "ጌታዬ... ለአንዲት ተራ ምግብ አቅራቢ ብለው ያባርሩኛል? ምንም ይሁን ምን ምግቡን ማድረስ እኮ ስራዋ ነው!" ሲል ተከራከረ።
አለቃውም በረጋ ግን ቁርጠኛ በሆነ ድምፅ እንዲህ አለው፦ "እንግዲያውስ አንድ እድል ልስጥህ። አሁኑኑ ወርደህ ከአንደኛ ፎቅ እስከ 35ኛው ፎቅ በአምስት ደቂቃ ውስጥ በደረጃ ውጣ፤ ያኔ ስራህን ታስጠብቃለህ።"
ሚስተር ኮስቢ ጮክ ብሎ "ምን? ይሄ እኮ የማይቻል ነገር ነው!" አለ።
ቦሱም "ለአንተ የማይቻል የሆነውን ነገር ሌላው የሰው ልጅ እንዲያደርገው እንዴት ትገፋፋለህ? አንተ ሰው የመሆን ህሊና ጎድሎሃል። በሰው ላይ ጭካኔ የምታሳይ ሰው በዚህ ድርጅት ውስጥ ቦታ የለህም... ውጣ!" ሲል አባረረው።
አንዳንድ ስራዎች ክህሎትን ይገልጻሉ፤ እውነተኛ ማንነት ግን የሚታወቀው ደካማ ለምንላቸው ሰዎች በምናሳየው አያያዝ ነው።
-------------- ------------ -----------
የሰው ልጅን ክብር ከያዘው ስራና ከደረጃው ጋር አታያይዘው፤ ሰው መሆኑ ብቻ እንዲከበር በቂ ነው።
ራስህ ልትሸከመው የማትችለውን ከባድ ሸክም በሌሎች ላይ ለመጫን አትሞክር።
እውነተኛ ታላቅነት የሚለካው ዝቅ ያሉትን በማንሳት እንጂ በስልጣን ተጠቅሞ ሌሎችን በመጨቆን አይደለም።
🛑 ላይክ ሼር ፎሎ ማድረግ አይዘንጋ!!