Yihune Belay/fan

Yihune Belay/fan we will promote yihunes old work

በ50ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ተወሰነ  “ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በትጥቅ ትግል ለመቀየር” በመንቀሳቀስ የተጠረጠሩት አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ፣ የቴአትር አዘጋጅ ዳግማዊ ፈይሳ እ...
20/06/2024

በ50ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ተወሰነ

“ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓትን በትጥቅ ትግል ለመቀየር” በመንቀሳቀስ የተጠረጠሩት አርቲስት አማኑኤል ሀብታሙ፣ የቴአትር አዘጋጅ ዳግማዊ ፈይሳ እና ፍላጎት አብርሃምን ጨምሮ 17 ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በ50 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ፈቀደ።
ዛሬ በጉዳዩ ላይ ብያኔ ለመስጠት የተሰየመው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በመዝገቡ ከተካተቱት 20 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አስራ ሰባቱ እያንዳንዳቸው የ50 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ያሬድ ገብረፃዲቅ (በማኅበራዊ ሚዲያ ስሙ ያያ ዘልደታ)፣ ፍስሃ እያዩ እና ጌትነት ታከለ የተባሉት ተጠርጣሪዎች ግን 11 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንደተፈቀደባቸው ጠበቃ አያሌው ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ ነው የዘገበው።

https://youtu.be/XkQJaa8GosU
27/05/2024

https://youtu.be/XkQJaa8GosU

#ዜማ​​​​​​​​ ኢትዮጵያ | Zema Ethiopia ዜማ ኢትዮጵያ tube Hd Birhanu Mikee Vlogs ...

Subscribe በማድረግ እናግዛቸው።እስኪ ኮሜንት ላይ ስክሪን ሻት ላኩልኝ አድናቂዎቼ
02/05/2024

Subscribe በማድረግ እናግዛቸው።እስኪ ኮሜንት ላይ ስክሪን ሻት ላኩልኝ አድናቂዎቼ

News - Feta Daily News | Ethiopian Airlines | Abiy Ahmed Ali | Tewelede Gebremariam | EU on Ethiopia | Sileshi Bekele Tigrai...

29/04/2024

እንኳን አደረሰን ቤተሰብ

ያንን ዋሽንት አምጡት  ትካዜው ቢቀለኝመቼም ያለ ሐሳብ ምንም ዘመድ የለኝዋ!! ስንቱ ዋ!! ስንቱ ልበል በዋሽንቱእሷ ብርቱ ሰው ነች የማይጥላት ዘመንክፉ ቀን  የወጣች የገፋች በጎመን።አበበ ...
21/01/2024

ያንን ዋሽንት አምጡት ትካዜው ቢቀለኝ
መቼም ያለ ሐሳብ ምንም ዘመድ የለኝ
ዋ!! ስንቱ ዋ!! ስንቱ
ልበል በዋሽንቱ
እሷ ብርቱ ሰው ነች የማይጥላት ዘመን
ክፉ ቀን የወጣች የገፋች በጎመን።

አበበ ብርሃኔ ዜማ
ጸጋዬ ደቦጭ ግጥም
ድምጽ ይሁኔ በላይ

https://youtu.be/McCHjMfsr60?si=TVRe08Nk-b9ee-Ky
21/09/2023

https://youtu.be/McCHjMfsr60?si=TVRe08Nk-b9ee-Ky

music merabete traditional wedding song,የቆጥኣስር የሰርግ ጭፈራ መራቤቴ ፡ባል የሚስትን ቤተሰበ ካገለገለና ልጃቸዉን ካገባ በኋላ የሚካሄድ ሰርግ ክፍል ENTERTA...

ይች ጀግኒት ሪሀና ጀባሪ ትባላለችኢራናዊት ነችአንድ ወንድ ሊደፍራት ሲል ማምለጫ አማራጭ ስታጣ ገደለችውና ኢራን ፍርድ ቤት በሰው ገዳይ ክስ ተከሳ ቀረበችየፍርድቤቱም ዳኛ ለምን ገደልሺው አላ...
18/09/2023

ይች ጀግኒት ሪሀና ጀባሪ ትባላለች

ኢራናዊት ነች

አንድ ወንድ ሊደፍራት ሲል ማምለጫ አማራጭ ስታጣ ገደለችውና ኢራን ፍርድ ቤት በሰው ገዳይ ክስ ተከሳ ቀረበች

የፍርድቤቱም ዳኛ ለምን ገደልሺው አላት

እርሱዋም ሊደፍረኝ ብሎ ከክብሬ ስከላከል ሌላ አማራጭ ስላጣሁኝ ገደልኩት አለችው

ዳኛውም ከክብሬ ለመከላከል የሚለው ምክንያትሽ አሳማኝ አይደለም አላት

እርሱዋም እውነትህን ነው ምክንያቱም አንተ ክብር ስለሌለህ አለችው😭

የዚህን ጊዜ ዳኛው በስቅላት እንድትገደል የሞት ፍርድ ፈረደባት

ጀግኒትም ሪሀና በአደባባይ በገመድ ተሰቅላ ተገደለች

ነፍስ ይማር❤

16/09/2023

እንኳን አደረሳችሁ

https://youtu.be/TSVVXQ8HnvYወዳጆቼ ይህን ቻናል ሰብስክራይብ አድርጉልኝ።
10/04/2023

https://youtu.be/TSVVXQ8HnvY
ወዳጆቼ ይህን ቻናል ሰብስክራይብ አድርጉልኝ።

#ክላሲካል #ክላሲካል ምርጥ የክላሲካል ስብስብ ...

ያልታወቀችው የታሪክ ማኅደር!!!!*****  *****   *****  *******ገዳሟ ከአዲስ አበባ በ143 ከታሪካዊቷ የብርሃን አምባ ደብረ ብርሃን ከተማ ሰሜናዊ ምዕራብ በግምት 13 ኪሎ ሜ...
23/03/2023

ያልታወቀችው የታሪክ ማኅደር!!!!
***** ***** ***** *******
ገዳሟ ከአዲስ አበባ በ143 ከታሪካዊቷ የብርሃን አምባ ደብረ ብርሃን ከተማ ሰሜናዊ ምዕራብ በግምት 13 ኪሎ ሜትር በመኪና ሄደው በእግር ደግሞ የ50 ደቂቃ ይጓዛሉ።
ቁልቁለቱን እንደጨረሱ ከላይ በገደላማ ተራራ ከታች በወንዝ ዙሪያዋን ደግሞ የመሶበ ወርቅ ቅርጽ ባለው አረንጓዴ ልምላሜና በየብስ የተከበበች የቅርስ መርከብ የታሪክ ማኅደር የሆነችውን ሊታመን በማይችል መልኩ በሰው ትከሻ ድንጋይ ተመላልሶ በ2 ዓመት ተኩል የሰጎን ዕንቁላል መስላ የተገነባችውን ዐጼ ዋሻ ደብረ ጽዮን ማርያምን ያገኛሉ።
ይህን ጊዜ የወረዱትን ዳገት ፣ የተሰማዎትን ድካም ረስተው የገዳሟን የቦታ አቀማመጥ ፣ የአካባቢውን ልምላሜ ፣ የአእዋፋትን ዝማሬ ሲሰሙ መንፈሰዎት ወደ ሰማየ ሰማያት ይነጠቃል ልበዎት በመንፈስ ይመላል ዓለም ለምኔ ምን ትሆነኝ ለኔ ፣ ዓይኔ ዓለም አየ እግሬ ደርሶ የሚለውን ዝማሬ በደስታ ብዛት በህሊናዎም በአንደበተዎም ይዘምሩታል።
ነዋሪነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉት የአካባቢው ተወላጅ መሪጌታ ፍስሐ ክፍሌ በዚች ታሪካዊት ገዳም መስዋዕተ ኦሪት ይሰዋባት የነበረ ዋሻ መኖሩንና በዘመነ ኦሪት አገልግሎት ይሰጥ የነበረ ከቆዳ የተሠራ ድንኳን የድንኳኑ ተራዳና የክፈፉ እንጨት መኖሩን አንስተውልናል።
በ842 ዓ.ም ዮዲት ጉዲት የተባለች ፈላሻ የኢትዮጵያን ካህናትና ቅርሶች ልታጠፋ በተነሳችበት ጊዜ አባቶቻችን ታቦት ጽዮንን ከአክሱም ጽዮን ይዘው መጥተው እዚህ ዋሻው ውስጥ ለ5 ዓመታት ያህል አስቀምጠውበት እንደነበረና ለሚዲያችን ገልጸውልናል።
ዮዲት ጉዲት ወደ ዚህ አካባቢ ደረሰች በሚባልበት ጊዜ ታቦተ ጽዮንን ከዚህ አንስተው ወደ ዝዋይ ደሴት ይዘው ሲሄዱ ሌሎች ተረፈ ጽላት እና በርካታ ቅርሶች በዚሁ ዋሻ ትተዋቸው እንደሄዱ ገልጸው ብራና መጻሐፍት የተለያዩ ቅርሶች ትተው እንደሄዱ ነግረውናል።
እመቤታችንም በስደቷ ወቅት በኪደተ እግሯ ከረገጠቻቸውና ከባረከቻቸው ቦታዎች አንዷ አጤ ዋሻ ደብረ ጽዮን ማርያም መሆኗንና እመቤታችን የፈተለችበት እንዝርት እና ሌሎች በርካታ ቅርሶች በገዳሟ ይገኛሉ ብለዋል።
እመቤታችን በዚህ ገዳም ስለመገኘቷ ማስረጃ በትንሹ ተአምረ ማርያም ምዕራፍ 112 ሙሉውን በትልቁ ተአምረ ማርያም ምዕራፍ 40 ላይ 40 እና በድርሳነ ዑራኤል ዘታኅሳሥ ገጽ 51 ታሪኩ ተመዝግቦ ይገኛል ብለዋል።
የእመቤታችን ጽላት በዐጼ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት ከዋሻ እንደወጣች እና የሳር ቤተ ክርስቲያን ተሰርቶላት በዚያ ቤተ መቅደስ ለረጅም ዘመናት ትኖር እንደነበረ መሪጌታ ፍስሐ ገልጸዋል።
በኛው የጣሊያን ወረራ ጊዜ በ1928 ዓ.ም የአራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ1888 ዓ.ም በነበረው ጦርነት አባቶቻችን ድል ሲያደርጉ ቅዱስ ጊይርጊስን ነው የወጋን ብለው ያስቡ ስለነበር ጣሊያን አዲስ አበባ እንደገባ በቀጥታ የአራዳ ጊዮርጊስን ቤተ ክርስቲያን ሲያቃጠለው አባቶቻችን ቀድመው ይህ መረጃ ስለነበራቸው መምህር መኩሪያ ወልደ ዮሐንስ የሚባሉ ከወንድማቸው ጋር የአራዳ ጊዮርጊስን ጽላት ወደ ዐጼ ዋሻ ማርያም ይዘው መጥተው ለ5 ዓመታት ተደርቦ እንደቆየ ተረክዋል።
በ1933 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን ለቆ ሲወጣ ንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ሥላሴ ወደ ኢትዮጵያ በኋላ በ1936 ዓ.ም አዲስ አበባ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን አንዳስረከቡት ገልጸዋል፡፡
በዓመቱ በ1937 ዓ.ም ደግሞ የቅዱስ ጊዮርጊስን ጽላት በክብር በዚህች ገዳም በማቆየታቸው ለአካባቢው ምእመናንና ካህናት ውለታ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ንጉሠ ነገሥቱ ከንግሥት ዘውዲቱ ጋር የቀድሞውን ቤተ ክርስቲያን አሳንፀው በቀኝ አዝማች ድጋፌ አስተባባሪነት በወርቅ የተለበጠ የእግዚአ ለሰንበት ጽላት በአጤ ዋሻ ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስገብተው የደብረ ዘይት በዓል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መከበሩን መሪጌታ ፍስሐ ተናግረዋል።
ታቦተ ጽዮን በእስራኤላዊያን ጥፋት ምክንያት በፍልስጥኤማውያን እጅ ተላልፋ እንደነበረው ሁሉ የእግዚአ ለሰንበት ጽላትም በ1988 ጠፍቶ እንደነበረ አንስተው ቤተ ክርስቲያኑም አርጅቶ ስለነበረ አዲሱ ቤተ ክርስቲያን በ2002 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ በ2 ዓመተት ተኩል ግንባታው መጠናቀቁንና በ2005 ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱ ማከበሩን መሪጌታ ፍስሐ ገልጸዋል፡፡
በ2006 ዓ.ም ደግሞ ተሰውሮ የነበረው የእግዚአ ለሰንበት ጽላት በጅቡቲ በአንድ ሙስሊም ቤት በተአምር ተገኝቶ በጅቡቲ ገብርኤል መግባቱን በመስማታችን ከምእመናኑ ፣ ከቅዱስ ሲኖዶስና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ከጅቡቲ ቅዱስ ገብርኤል አምጥተን በቅድስት ማርያም ሙዚየም 3 ወር ከቆዬ በኋላ በ2007 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በታላቅ ክበር ተመልሶ አዲስ በተሠራው ቤተ መቅደስ መግባቱን አስረድተዋል፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን በርካታ ቅርሶች ለመንከባከብ ፣ ለመጠበቅ እና ለማስተዋወቅ የሚያስችል ዘመናዊ ሙዚም የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ግንባታ የጀመረ ሲሆን ለሙዚየሙ ግንባታ የተለያየ ደረጃ ያላቸው 301 ብረቶች ፣ 180 ኩንታል ሲሚንቶ ፣ 80 ቆርቆሮ ፣ 20 ጋሎን ቀለም ፣ 6 በር ፣ 10 መስኮት ፣ 32 ሲኖ አሸዋ ፣ 3 ሺህ 150 ብሎኬቶች ፣ 110 ከረጢት ጂብሰም እንደሚያስፈልግ እና ምእመናን አቅማቸው በፈቀደው ሁሉ ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ ሰበካ ጉባኤው ጥሪ አቅበዋል።
ዐጼ ዋሻ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያ በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ታላላቅ ገዳማት አንዷና የደብረ ናዝሬት ዱቢሳ መገኛ ስትሆን ለገዳሟ ዕድገት መሠረታዊ እንቅፋት የሆነው የመንገድ ችግር በመሆኑ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ ምእመናን መንገዱ ከ7 ኪሎ ሜትር እንደማይበልጥና ይህንን መንገድ በመገንባት የበረከቱ ተሳታፊ ትሆኑ በእመቤታችን ስም ጥሪ ቀርቦላችኋል።
መረጃው ፦የ አቡቀለምሲስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው!!!

Yihune Belay/fan follow, like shareድምጻዊት የዝና ነጋሽከተወለደችበት ጎንደር ዳባት ጥዋ ጊዮርጊስ በ1979 ነበር አባትዋ እርስዋን እና ወንድሟን መሳፍንት ነጋሽን ወደ አ...
23/03/2023

Yihune Belay/fan follow, like share

ድምጻዊት የዝና ነጋሽ
ከተወለደችበት ጎንደር ዳባት ጥዋ ጊዮርጊስ በ1979 ነበር አባትዋ እርስዋን እና ወንድሟን መሳፍንት ነጋሽን ወደ አዲስ አበባ ይዘው የሄዱት።ያኔ የ10 ዓመት ልጅ ነበረች። አባታቸው አዲስ አበባ የወሰዷቸው እንዲማሩ ነበርና ትምሕርት ቤት አስገቧቸው። ግን በትምህርቱ ብዙም አልገፉበትም። የዝናና ወንድሟ በምሽት ክበብ መዝፈን ጀመሩ።

በተለያዩ አልበሞቿ ደጋግማ የዘፈነችው ሰቆጣ መለያዋ ነው።በዚህና በሌሎችም ተወዳጅ የባህል ዘፈኖቿ የምትታወቀው ድምጻዊት የዝና ነጋሽ ኑሮዋን ለንደን ካደረገች 20 ዓመት ሆኗታል። ትዳር መሥርታ የልጆች እናት ከሆነች ወዲህ ሙዚቃውን እንደ ፍላጎቷ ማስኬድ ባትችልም ሁኔታዎች ሲመቻቹላት ነጠላ ዜማም ይሁን አልበም ታወጣለች።ከመካከላቸው በዚህ ዓመት ለህዝብ ያቀረበችው አንድ ነጠላ ዜማ ይገኝበታል።በቅርቡም አንድ አዲስ አልበም ለማውጣት ዝግጅቷን አጠናቃለችት።የዝና ከብዙ ዓመታት በኋላ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ለህዝብ ያቀረበችው ያዳመጣችሁት እናመስግናቸው የራስዋ ድርሰት ነው።ከቀደሙት ዘፈኖቿ ለየት ያለውን ይህን ዘፈን የደረስኩበት ምክንያት አለኝ ትላለች።የዝና የሙዚቃውን ዓለም የተቀላቀለችው በልጀነቷ ነው።ከተወለደችበት ጎንደር ዳባት ጥዋ ጊዮርጊስ በ1979 ነበር አባትዋ የዝና ነጋሽን እና ወንድሟን መሳፍንት ነጋሽን ወደ አዲስ አበባ ይዘው የሄዱት። ያኔ የዝና የ10 ዓመት ልጅ ነበረች። አባታቸው አዲስ አበባ የወሰዷቸው እንዲማሩ ነበርና ትምሕርት ቤት አስገቧቸው። ግን በትምህርቱ ብዙም አልገፉበትም። የዝናና ወንድሟ በምሽት ክበብ መዝፈን ጀመሩ።እንዲህ እንዲህ እያለች የዝና የመጀመሪያ ካሴትዋን በ16 ዓመቷ ለማውጣት በቃች። ከመጀመሪያው ካሴት በኋላ ቦለሎች በሚል ስም ከጓደኞችዋና ከሌሎች የቤተሰብ አባላት ጋር በከፈተችው የምሽት ክበብ የርስዋና የቡድኑ አባላት ዝና እየናኘ ሄደ።በወቅቱ ቦለሎች በህብረት ያወጡት ካሴት ታዋቂነትን አትርፎላቸዋል።ከዚያ በኋላም የዝና ዘፈኖች በሀገር ውስጥ በውጭም ለመታተም በቅተዋል። ከዚህ አጋጣሚ በኋላ ቦለሎች በተለያዩ የአውሮጳ ሀገራት እየተዘዋወሩ ሥራዎቻቸውን ቢያቀርቡም የጋራ ጉዞአቸው ግን ቀስ በቀስ እየከሰመ ሄደ።የዝናም ከጥቂት ዓመታት በኋላ ኑሮዋን ለንደን አደረገች።ትዳር መስርታ ልጆችም ከወለደች በኋላ እንደበፊቱ በዘፈኑ ብዙም መግፋት ባትችልም ጭርሱን ግን አልተወችውም።የዝና ከልጅነት አነስቶ በተሰማራችበት በዘፈኑ ዓለም በተለያዩ መድረኮች ከአድናቂዎቿ ልዩ ልዩ ስጦታዎች ተበርክተውላታል።ከመካከላቸው ለሁለቱ ልዩ ቦታ ትሰጣለች።
Yihune Belay/fan




music

 ❓ስለ  #ጎጃም መሬቱና ወንዙ ወንዱና ሴቱ ቁንጅና ውበቱ ባህሪው ፀባዩ ጀግንነቱ ደፋርነቱ ደግነቱ እንግዳ ተቀባይነቱ ብሉ ጠጡ ባይነቱ ቅኔ አዋቂነቱ ሰው አክባሪነቱ ሩህሩህነቱ ኩሩነቱ ጨዋታ...
23/03/2023



ስለ #ጎጃም መሬቱና ወንዙ ወንዱና ሴቱ ቁንጅና ውበቱ ባህሪው ፀባዩ ጀግንነቱ ደፋርነቱ ደግነቱ እንግዳ ተቀባይነቱ ብሉ ጠጡ ባይነቱ ቅኔ አዋቂነቱ ሰው አክባሪነቱ ሩህሩህነቱ ኩሩነቱ ጨዋታ አዋቂነቱ ሐገር ወዳድነቱ ፍቅር አሰጣጡ ሰርቶ አዳሪነቱ አትንኩኝ ባይነቱ ስለ ጠቢብነቱ ወጉ ባህሉ ትውፊቱ እምነቱ ለወደደው ለአፈቀረው ታማኝነቱ የተቀኙለት ብዙ ድምጻዊ ከያኒያን አሉ። ከብዙዎች የጥቂቱን በማድመጥ በዘፈን ስንኞቻቸው ጎጃምን የገለፁበትን ቅኔ ለማውጣት ሞክሬያለሁ። የጎጃም ተወላጅም ሆኑ ተወላጅ ያልሆኑ ጎጃምን በዜማቸው ያሽሞነሞኑ እልፍ አዕላፍ ናቸው ብል ማጋነን አይሆንብኝም ከብዙ ቦታዎች በተለዬ ብዙ ተብሎለታል። ድምጻዊያን ስለ ጎጃም የተቀኙትን በጥቂቱ አንድ በአንድ እናያለን።
የፀበል ዳር እኳይ ወንዝ ያወዛት ቅል
ተሸፍና ዋርካ ከልሏት የዛፍ ጠል
የት ነበር ያረኩት ቀፎዬን ስል ኖሬ
ንብ ተከትዬ ባይ ጎጃም ኑራ ማሬ።

እንዲህ ቅርብ ነው ወይ ጎጃም በጫቀታ
እንደ ነፍሰ ገዳይ የምትመጭው ማታ

የዋሸራን ቅኔ እዬዘረፍሽ
ሰምና ወርቅ ሆነና ፍቅርሽ
እንደዋዛ አትገኝ ተባልሽ
ያየሽ ሁሉ ስትሔጅ ከመንገድ
ከዬት ትሆን ሲል ሲወራረድ
እኔ አወኩሽ በአንገትሽ ግማድ።

የጎጃም ልጅ እና የልመና በሬ
ሳይመሽ አይፈታም ሳይደክም ገበሬ።
#ቻላቸው
የራቀን አቅርቦ ሰብስቦ ጎጃም
ወዳጅ ማገናኛ ብልሐት አያጣም።

አባይ ወዳማዶ የተወለዳችሁ
ምንድነው ነገሩ የመወደዳችሁ
ባለ ሚስጥር ሆኖ ልክ እንደ ቅኔያችሁ
ውሎ አድሮ ይገባል ይጥማል ፍቅራችሁ።

ማኛ ጤፍ እንጀራ በወተት የራሰ
ጎጃም ገብቶ አይወጣም እሱን የቀመሰ።

ሰው እንዳልክበት አባይ አልጎደለ
ያውስ እሽ ብሎ ብቅ ቢል አይደለ።

ከጎጃሜዋ ጋር ምሽቱን ሳወጋ
ማን ይገዝትልኝ ሌሊቱ እንዳይነጋ
አላይቶም አትበይ አልሰምቶም አትበይ
በተድላ ሞት አልኩኝ ጎጃሜዋ ነይ ነይ።

ልቤ ፍቅር ሰራ ከአባይ ወዳ ማዶ
የበላይዬን ዘር ጎጃሜዋን ወዶ
ልክ እንደ ጀግና ሰው ምንኛ በረታሁ
ጎጃም ተሻግሬ ጎበዝ ሆኜ መጣሁ
ጋሜዋ ነይ ጋምዬ
ደፋር አርጊው ልቤን እንደ በላይዬ
የበላይን ፀባይ ይዘዋል ሰዎቹም
ለፍቅር ነው እንጂ ለፀብ አይመቹም።

መቀነቴን ልሰር ጉልበቴን ላበርታ
አይቀሩበት ሐገር ወይ ሸበል በረንታ።

እንደ ጣና አጥርቶ አሳምሮ ሰርቶት
ደግነት ጀግንነት አፈስ አርጎ ችሮት
እንከን ማይወጣለት ደጉ የጎጃም ሰው
ቢከተሉት ኩራት ቢያስከትሉት ጌጥ ነው።

መርጦ ሚዘራ ሸጋ ወላጅ
ነጥሎ ሚጥል ጀግና ነው እንጅ
ከጀግናም ጀግና ሐገር ያወቀው
ጎጃም አይደል ወይ ጸሐይ የሞቀው።

የጎጃም ሰው ማር ነው አመሉ ገራገር
አንድ ቀን ያበላው ሁሌ የሚነገር
ወንድም ቢሆን ጋሻ ባል ቢያደርጉት ጌጥ
እንዲህ ነው ፈጣሪ አሟልቶ ሲሰጥ።

ጎጃም ላይ ቢጠቀስም ስሙ
ኢትዮጵያ ናት ህልሙ
አይደምቅም በላይ ካልተጠራ
የጎጃም ጭፈራ።

ታምቶ አይታወቅም ጎጃም በማተቡ
ፍቅር እንጂ ክፋትን አያውቅም በልቡ።

ቅኔው ከዋሸራ ሆኖ ከደጃቸው
ሰምና ወርቅ አለው ጎጃሞች ስማቸው
ከአፍ ላይ ማር ማር ይላል ልክ እንደ ፍቅራቸው።

የበላይ ዘር ሆነሽ የዛ የጀግናው
እንዳይሞት እንዳይሽር ልቤን አረግሽው።

የጎጃሙ ልጅ የተመናሸው
ለወደደውማ አፉ ማይዋሸው
ቢጠራ ደራሽ የማያሳፍር
ሁሌም ያበቅላል የጎጃም አፈር።

እስክስታ ዳንኪራ ዜማ መች ቸግሮት
ቢቸና ደብረ ወርቅ ዋሸራ አስተምሮት
እንዳገሩ ውኃ እንደ አባይ ጅረት
ፈሰሰለት ልቤ እሱን ያየ እለት።

ውቢቷ ጎጃሜ
ማስገር ከጣና ዳር ተምሬ ነበረ
እቴ አንቺን ማጥመጃው ዘዴው ጠፍቶ ቀረ።

የሸበሉ ወጣት ጉብል ኧረ እኔስ ናፍቆኛል
አፋልጉኝ እናንተው ሰው በሰው ይገኛል
እንክት ያልኩት ጎኔን
ህምም ድክም እስክል ትቸው ሰውነቴን
ስናፍቅ አድራለሁ አንተን እና እናቴን።

ጉዞ ጎንደር 2015
19/01/2023

ጉዞ ጎንደር 2015

ስለጥምቀት የሰራሁት ስራ ነው
09/01/2023

ስለጥምቀት የሰራሁት ስራ ነው

Yehunie Belay | ይሁኔ በላይ | ዘገሊላ | Zegelila | music video https://bit.ly/3c3uayeይህ የይሁኔ በላይ የዩቲብ ቻናል ነው:: በየጊዜው ለሚለቀቁ ስራዎች በቀጥታ እንዲላክላችሁ ቻናሉን ሰብስክራይብ ማድረግ አይር...

09/01/2023

እንኳን አደረሳችሁ ውድ አድናቂዎቼ
መልካም በዓል ይሁንላችሁ፡፡

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yihune Belay/fan posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share