አውድ ኀገር Awed Hager

አውድ ኀገር  Awed Hager የሬዲዮ ፕሮግራም

የሸዋል ኢድትንሹ ኢድ ተብሎ ስለሚጠራው፣ የረመዳን ወርና የረመዳን ጾምን ማብቃት ተከትሎ ዐስረኛ ወር በሆነው ሸዋል ስለሚመጣው፣ በሐረሪ ሰዎች ደግሞ በድምቀት ስለሚከበረው ስለ ሸዋል ኢድ ልና...
16/04/2024

የሸዋል ኢድ

ትንሹ ኢድ ተብሎ ስለሚጠራው፣ የረመዳን ወርና የረመዳን ጾምን ማብቃት ተከትሎ ዐስረኛ ወር በሆነው ሸዋል ስለሚመጣው፣ በሐረሪ ሰዎች ደግሞ በድምቀት ስለሚከበረው ስለ ሸዋል ኢድ ልናወሳ ነው። ከዛ ቀድመን ግን በዓሉ ከሁሉ መርጦ ስለከተመባት ሐረር ጥቂት እንበል።

ከአዲስ አበባ 525 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ሐረር፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማሳያ እንደሆነች ይነገርላታል። ለዘመናትም ከፍተኛ የንግድ ማዕከል ሆና አገልግላለች። በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ለጥበቃዋ ተብሎ የተሠራው የጀጎል ግንብ ዛሬ ቅርስና ውበቷ ሆኖ ይገኛል። አልፎም ይኸው የጀጎል ግንብ እንደ አውሮፓውያኑ የዘመን አቆጣጠር በ2006 በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ተቋም የዓለም ቅርስ ተብሎ ተመዝግቦላታል። ባለ አምስት በሩ የጀጎል ግንብ፣ የሐረር ከተማ በአነስተኛ የመሬት ስፋት በርካታ ጎብኚዎችን ከሚያስተናግዱ ጥቂት የዓለማችን ከተሞች አንዷ እንድትሆን አድርጓታል።

እንግዲህ ሸዋል ኢድ በድምቀት የሚከበረው በዚህች አንጋፋ፣ ጥንታዊትና ውብ ከተማ ነው። በዓሉ በሐረሪ ክልላዊ ሕዝባዊ እና ባህላዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር በአዋጅ የተደነገገው ጥቅምት 8/1999 ዓ.ም ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮና በኋላም ባህላዊ እሴቱ እየጎላና እየበረታ ሄዶ፣ ከሐረር አልፎ ለኢትዮጵያ፣ ከኢትዮጵያ ተሻግሮም የዓለም ቅርስ ለመሆን በቅቷል። የበዓል አከባበሩን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ በ2012 የተጀመረው ሥራና ጥረት ፍሬ አፍርቶ፣ ባሳለፍነው ዓመት የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የበዓሉን አከባበር ከዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች መካከል ጽፎታል።
በመግቢያችን እንዳነሳነው ሸዋል ኢድን አንዳንዶች ‘ትንሹ ኢድ’ ብለው ይጠሩታል። ምክንያቱ ደግሞ የጾሙ ቀናት ጥቂት መሆናቸው ነው፤ ስድስት። ‘ሸዋል’ የሚለው ዋና መጠሪያው ደግሞ የረመዳን ወር ማብቂያና የኢድ አልፈጥርን በዓል ተከትሎ የሚመጣውን ዐስረኛ ወር ሸዋልን መሠረት ያደረገ ነው።

የሸዋል ኢድ ባህላዊ ትርክትና ሥርዓቱ እንደሚያመዝን የሃይማኖቱ አዋቂዎች ይናገራሉ። ሃይማኖታዊ መሠረቱን በሚመለከት የሚያስረዱ ሰዎችም ሲናገሩ “ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የረመዳን 30 ቀን ጾም ሲያበቃ 6 ቀን ሸዋልን የጾመ ዓመቱን ሙሉ እንደጾመ ይቆጠርለታል ብለዋል።” ይላሉ። ይህንንም እንዲህ ሲሉ ያብራሩታል፥ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሰው መልካም ሥራ ሲሠራ፣ በአላህ ዘንድ ዐስር እጥፍ ይሆናል ተብሎ ይታመናል። ስለዚህ በዓመት 360 ቀናት አሉና፣ 30 ቀናት የረመዳን ጾም እንደ 300 ቀን፣ 6 ቀኑ ደግሞ እንደ 60 ይታሰባል። ‘ዓመቱን ሙሉ እንደጾመ ይቆጠርለታል’ የሚባለው ከዚህ የተነሳ ነው።

አበው ነገርን አንድም እያሉ በአንድምታ እንደሚያስረዱ፣ የሸዋል ኢድ አንድም ከላይ በተጠቀሰው ምክንያት መነሻነት የሚታሰብ ሲሆን፣ አንድም ነገረ ሴቶችን ያጣቅሳል። ይህም በእስልምና አስተምህሮ ሴቶች በረመዳን ጾም ወቅት የወር አበባ በሚያዩባቸው ቀናት ጾሙን ያቋርጣሉ። በዚህም የተነሳ ያጎድሉትን የጾም ቀናት ለማካካስ እንዲችሉ ለማድረግ የረመዳንን መጠናቀቅ ተከትሎ የሚመጡ ቀናትን በጾም ያሳልፋሉ። ወንዶችም ታድያ ተጨማሪ ትሩፋት ለማግኘት ጾሙን አብረው ይጾማሉ።

እናም እነዚህን መሠረት አድርጎ ሕዝበ ሙስሊሙ ሸዋልን ይጾማል። ከረመዳን ወር ጾም ባገኘው የመንፈስ ጥንካሬ ቀጥሎ፣ በኢድ ማግስት ሸዋልን ይጀምራል። ታድያ የስድስት ቀኗን ጾም ተከትሎ፣ የበዓል አከባበር ሥርዓቱ በጋራ መሰባሰብ፣ ስጦታ መሰጣጠትን የመሰለ ክዋኔን ያካትታል። እንደ ሃይማኖቱ መምህራን ገለጻ፣ እነዚህና እነዚህን የመሰሉ በዓሉን የተከተሉ ክዋኔዎች በባህል ተለምዶ የሚካሄዱ መሆናቸውን ሲያስረዱ፣ በሃይማኖት ‘እንዲህ ስለተባለ...’ ተብሎ የሚጠቀስ መደገፊያ እንደሌለው ይገልጻሉ።

ሸዋል ኢድ በአዋጅ ተደንግጎ በድምቀት በአደባባይ የሚከበርባት ሐረር፣ በዚህ ወቅት ከውጭም ከውስጥም በርካታ እንግዶችንና ጎብኚዎችን ታስተናግዳለች። ‘የሐረሪ ባህላዊ ኢድ’ ተብሎ እንዲጠራም ያደረገው ይህ ድምቀቱ ነው። ታድያ በበዓሉ ከሚታዩ ክዋኔዎች አንዱ በዝክሪ ለፈጣሪ ምስጋና በማድረስ ሲሆን፣ ዝክሪ በምስጋና ግጥሞች የተመላ ነው።

ልጃገረዶችም ታድያ በዓሉን ተከትሎ በሚኖሩ ሦስት ተከታታይ ቀናት ከሥራ ነፃ ሆነው የገንዘብ መዋጮ (መሐለቅ መታጫ) በማድረግ ድግስ አዘጋጅተው በመመገብና በመጨፈር በዓሉን ያከብራሉ። ከዝክሪውና ከዚህ የሴቶች የጎላ ሱታፌ በተጨማሪም፣ ባህላዊ ምግብ እና መጠጥም የበዓሉ አካል ነው። የበዓሉን መድረስ ተከትሎ የሚነሱና በበዓሉ ሰሞን ከሚዘወተሩ ምግቦች መካከል አቅሌል፣ ሐሸር ቃሕዋ፣ ቁጢ ቃሕዋ ይጠቀሳሉ። (አቅሌል፣ በቀይ ወጥ የተዘጋጀ ፍትፍት ሲሆን፣ ሐሸር ቃሕዋ እና ቁጢ ቃሕዋ ከወተት ጋር ተፈልቶ የሚጠጣ ቡና እና ሻይ ነው።)

በዚህ ሰሞን በየትኛው ቦታ ያለ ሰው ወደ ሐረር አቅንቶ ከቤተሰቡ ጋር ይዘያየራል፣ ያላገቡ ይተጫጩበታል። ሕዝብ በከፍተኛ ቁጥርና ማራኪ ባህላዊ ቀለም አልባሳት ይደምቃል።

ሸዋል ኢድ በሐረር በዚህ መጠን ይድመቅ እንጂ፣ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎችም ይከበራል። እንደውም እንደየ አካባቢው ክዋኔውም ይለያል። ለምሳሌ ሸዋል ኢድ በስልጤዎች ዘንድ ትዳር የያዙ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ቤተሰቦቻቸውን የሚጠይቁበት ቀን ነው። በወለኔዎች ደግሞ የኢድ ማግስት ጾም ስለሆነ ኢድ አልፈጥርን ብዙ አይዘጋጁበትምና ከስድስቱ ቀናት ጾም ፍቺ በኋላ የሚመጣውን የሸዋል ኢድ ሰፊ ዝግጅት አድርገው ያከብሩታል።

አምባሰል ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን

የሾንኬ መንደር የአርጎባ ብሔረሰብ ህያው ቅርስየሾንኬ መንደር በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከከሚሴ ከተማ በምስራቅ አቅጣጫ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ደዋ ጨፋ ወረዳ ጅሮታ ቀበሌ የሚገ...
11/04/2024

የሾንኬ መንደር

የአርጎባ ብሔረሰብ ህያው ቅርስ

የሾንኬ መንደር በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከከሚሴ ከተማ በምስራቅ አቅጣጫ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ደዋ ጨፋ ወረዳ ጅሮታ ቀበሌ የሚገኝ ታሪካዊ መንደር ነው፡፡ መንደሩ ከአርጎባ ብሔረሰብ መኖሪያ ቦታዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን ሸህ ፈቄ አህመድ የተባሉ የሀይማኖት አባት ከ900 ዓመትት በፊት እንደመሰረቱት ይነገራል፡፡

ሾንኬ መንደር ግዙፍ ተራራ ላይ አርጎባዎች በልዩ ጥበብ ድንጋይ፣ አፈር እና የወይራ እንጨት በመጠቀም የሰሩት መንደር ሲሆን ሦስት መስጅዶች እና አምስት መቶ የሚሆኑ መኖሪያ ቤቶችን ይዟል።

የአርጎባ ብሔረሰብ ታሪክ አዋቂዎች እንደሚናገሩት አርጎባዎች በ7ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ ቀደምት የእስልምና ሀይማኖት ተከታይዮች ጋር የዘር ሀረግ ትስስር እንዳላቸው ይናገራሉ፡፡ አርጎባዎች በአማራ ክልል (ደቡብ ወሎ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ሰሜን ሸዋ) በተጨማሪ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎችም ይኖራሉ፡፡

በድጋሜ እንኳን ለ1445ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!

ዒድ ሙባረክ!

11/04/2024
በአዲስ ነገር መጥቻለሁ !ዘሪሁን ግርማውብ ሀገር በቅዳሜ ምሽት /የፊታችን ቅዳሜ ይጀምራል/ሰላም ውድ ኢትዮጵያዊያን ወዳጆቼ እንደምን አላችሁልኝዘሪሁን ግርማ ነኝ የባህል የቱሪዝምና የሆስፒታሊ...
11/04/2024

በአዲስ ነገር መጥቻለሁ !
ዘሪሁን ግርማ

ውብ ሀገር በቅዳሜ ምሽት /የፊታችን ቅዳሜ ይጀምራል/
ሰላም ውድ ኢትዮጵያዊያን ወዳጆቼ እንደምን አላችሁልኝ
ዘሪሁን ግርማ ነኝ የባህል የቱሪዝምና የሆስፒታሊቲ ጋዜጠኛ
እና አማካሪ ነኝ።

ከአስር /10/ አመታት በላይ በሬዲዮ ዘርፍ በዛሚ 90.7 ኤፍ
ኤም በደቡብ ኤፍ ኤም 100.9 እና በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የሬዲዮ ጣቢያዎች እና በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የኢትዮጵያን
ባህል ቱሪዝም እና የሆስፒታሊቲ ዘርፍን ሳስተዋውቅ እና ግንዛቤ የሚያስጨብጡ ኘሮግራሞችን ሳቀርብ ቆይቻለሁ። ነገር ግን
የብዙ ወዳጆቼ እና የሬዲዮ አድማጮቼ ጥያቄ ያለኝን ልምድ እና ስለኢትዮጵያ በጉዞ ያወኳቸውን በምስል ማሳየት እችል ዘንድ በቴሌቪዥን ፕሮግራም እንድመጣ ነበር። ይሁንና ፈጣሪ የፈቀደው ነውና የሚሆነው አሁን ጊዜው ደርሷል።

ውብ ሀገርን ይዤ መጥቻለሁ !

የሀገራችንን ባህል ቱሪዝም እና የሆስፒታሊቲ ኢንቨስትመንት
ዘርፉን የሚያስተዋውቅ በየትኛውም አለም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን በተለይ ትውልዱ ስለ ሀገሩ ባህል ወግ እና እሴት እንዲሁም የቱሪዝም ሀብቶች እውቀት እንዲኖረው እና በሀገሩ የሚኮራ ትውልድ ማድረግ ይችላል ያልኩትን ውብ ሀገር የተሰኘ ፕሮግራም የፊታችን ቅዳሜ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ሜ ለመጀመር ዝግጅቴን ጨርሻለሁ።

ውብ ሀገር ለትውልዱ የቀረበ የቴሌቪዥን ፕሮግራም በኢሳት ቴሌቪዥን ዘወትር ቅዳሜ ምሽት ከ3:00 ጀምሮ ይተላለፋል።

ይከታተላሉ ! ያተርፉበታል !

በብዙ መልኩ ከጎኔ ለነበራችሁ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

አውደ ሐገር  በረዴኤት ዘነበ  እና በዘርይሁን አለማየሁ
28/03/2024

አውደ ሐገር በረዴኤት ዘነበ እና በዘርይሁን አለማየሁ

08/03/2024
በአደዋ ድል  በዋዜማው ዋዜማ ላይ እንገኛለን  ጋዜጠኛ Zerihun Girma አብሮን ያመሻል
29/02/2024

በአደዋ ድል በዋዜማው ዋዜማ ላይ እንገኛለን ጋዜጠኛ Zerihun Girma አብሮን ያመሻል

29/02/2024
29/02/2024
29/02/2024
The Ethiopian Wildlife Conservation Authority and Chengeta Wildlife USA signed a Memorandum of Understanding to establis...
26/02/2024

The Ethiopian Wildlife Conservation Authority and Chengeta Wildlife USA signed a Memorandum of Understanding to establish strategic law enforcement and capacity-building.

EWCA and CW agree to work together to improve the effectiveness of conservation law enforcement and capacity building for wildlife conservation in Ethiopia.

The MoU, which will be in effect for the next five years, plays a critical role in developing effective, long-term, and equitable solutions to today's environmental challenges.

EWCA
February 26/2024

CALL FOR PAPERSTourism Training Institute (TTI) is planning to conduct the 13th Annual Conference under the theme: “Buil...
26/02/2024

CALL FOR PAPERS
Tourism Training Institute (TTI) is planning to conduct the 13th Annual Conference under the theme: “Building a Sustainable Tourism and Hospitality Future." Hence, the Conference organizers cordially invite academicians, researchers, policy makers, practitioners, and consultants to submit papers on subthemes listed below.
Sub-themes:
1. Service quality and customer satisfaction in tourism and hospitality;
2. Tourism and hospitality organizations, management, and leadership;
3. Tourism products development, branding, and promotion;
4. Education and training in tourism and hospitality:
5. Indigenous knowledge and Community based tourism; and
6. Innovation and best practices in tourism and hospitality.
Decisions about paper selection will be made on the basis of the following criteria:
1. Relevance to the theme of the conference
2. Practical application of the paper's findings by policy makers and practitioners
3. Rigor of the evidence upon which the paper is based
4. Clarity of the papers' argument and clear conclusions
Note: Selected papers will be published as conference proceeding and modest honorarium will be paid for Presenters.
Important Deadlines
1. Manuscript submission: April 10, 2024
2. Notifying selected papers: April 25, 2024
3. Submission of Power Point for presentation: May 1, 2024
4. Conference date: 16th May, 2024
Contact Details
TTI Research & Consultancy Office Tel. +251115308123 +251 911396868 P.O. Box: 4350, Addis Ababa.
E-mail: [email protected] & [email protected]

አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት የጆርዳን ቱሪዝም ሚንስትር  መክራም ሙስጠፋ ጋር ተወያይተዋል::የካቲት 13/2016 ዓምአዲስ አበባበውይይታቸው ሁለቱ ሀገራት...
21/02/2024

አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት የጆርዳን ቱሪዝም ሚንስትር መክራም ሙስጠፋ ጋር ተወያይተዋል::

የካቲት 13/2016 ዓም
አዲስ አበባ

በውይይታቸው ሁለቱ ሀገራት በቱሪዝም ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እና የልምድ ልውውጥ ማድረግ በሚችሉበት ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል::

በተለይም በቱሪዝም ኢንቨስትመንት፣ ፕሮሞሽን፣ በቅርስ ጥበቃ እና በጤና ቱሪዝም ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል::
ሚንስትሩ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ በሀይማኖት ቱሪዝም እና ጤና ቱሪዝም ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ውይይቶችን ከተለያዩ ተቋማት ሀላፊዎች ጋር ያደርጋሉ::

በከተማዋ ያሉ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻዎችንም ይጎበኛሉ::

ለይፋዊ  ስራ ጉብኝት ኢትዮጵያ የሚገኙት የጆርዳን ቱሪዝም ሚንስትር መክራም ሙስጠፋ እና ልኡካን ቡድናቸው የአድዋ ሙዚየምን እና እንጦጦ ፓርክን ጎብኝተዋል::የካቲት 13/2016 ዓ.ምአዲስ አ...
21/02/2024

ለይፋዊ ስራ ጉብኝት ኢትዮጵያ የሚገኙት የጆርዳን ቱሪዝም ሚንስትር መክራም ሙስጠፋ እና ልኡካን ቡድናቸው የአድዋ ሙዚየምን እና እንጦጦ ፓርክን ጎብኝተዋል::

የካቲት 13/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የዓለምአቀፉ የቱሪስት አስጎብኚ ቀን  "ቱሪስት አስጎብኚ እና አረንጓዴ ቱሪዝም" በሚል ርዕስ በፓናል ውይይት ተከበረ ።**የካቲት 13/2016አዲስ አበባ፤የቱሪስት አስጎብኝ ባለሙያዎች የአገር...
21/02/2024

የዓለምአቀፉ የቱሪስት አስጎብኚ ቀን "ቱሪስት አስጎብኚ እና አረንጓዴ ቱሪዝም" በሚል ርዕስ በፓናል ውይይት ተከበረ ።
**
የካቲት 13/2016
አዲስ አበባ፤

የቱሪስት አስጎብኝ ባለሙያዎች የአገርን ገፅታ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና ያላቸው ሲሆን ነባርና አዲስ ወደ ሙያዉ የሚቀላቀሉ ባለሙያዎች ሙያው የሚጠይቀወን የራሱ መርህ፣ የሙያ ስነምግባር፣ መገለጫዎችና አሰራሮች ተከትሎ መስራት እንደሚገባ በፓናሉ ተገልጻል።

ዓለምአቀፉ የቱሪስት አስጎብኚ ማኅበራት ፌዴሬሽን እ. ኤ.አ ከ1990 ጀምሮ በዓለምአቀፍ ዙርያ የቱሪስት አስጎብኚ ቀንን በየዓመቱ እ. ኤ. አ ፌብርዋሪ 21 ያከብራል። በአኹኑ ጊዜ ከ70 በላይ ሀገራት በየዓመቱ ያከበራሉ። ይህን ተከትሎ ማህበሩ በቱሪዝም ሚኒስትር አዳራሽ በዛሬው እልት በፓናል ወይይት አክብሯል።

በፓናል ውይይቱ የቱሪስት አስጎብኝዎች፣ ኦፕሬተሮች፣ የዘርፉ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ከሆቴል ዘርፍ የተውጣጡ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል።የቱሪዝም ሚኒስቴርም " እንኳን ለዓለም አቀፍ የቱሪስት አስጎብኚ ቀን !"አደረሰን መልእክት ተላልፏል።

አለም አቀፉ የቱሪስት አስጎብኚዎች ቀን በተለያዩ መረሐግብር እንዱሁም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የማህበራት ተወካዮች የካቲት 13/6/16በቱሪዝም ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ተ...
21/02/2024

አለም አቀፉ የቱሪስት አስጎብኚዎች ቀን በተለያዩ መረሐግብር እንዱሁም የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የማህበራት ተወካዮች የካቲት 13/6/16በቱሪዝም ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ተከብሮዋል።

Venue: Ministry of Tourism Time: 03:00 Local time
19/02/2024

Venue: Ministry of Tourism
Time: 03:00 Local time

ዛሬ  ሐሙስ 7/06/16 አውድ እግዳችን  #ኤንዲ  #አሰፋ  የኢትዮጲያ ቱሪስት አስጎብኚዎች ማህበር ፕሬዝዳንት
15/02/2024

ዛሬ ሐሙስ 7/06/16 አውድ እግዳችን #ኤንዲ #አሰፋ የኢትዮጲያ ቱሪስት አስጎብኚዎች ማህበር ፕሬዝዳንት

የዓለም የሬዲዮ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ13ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ5ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል።ዓለም አቀፍ የሬዲዮ ቀን እንዴት መከበር ጀመረ?የዓለም ራዲዮ ቀን እንዲከበር በስፔን የራ...
13/02/2024

የዓለም የሬዲዮ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ13ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ5ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል።

ዓለም አቀፍ የሬዲዮ ቀን እንዴት መከበር ጀመረ?

የዓለም ራዲዮ ቀን እንዲከበር በስፔን የራዲዮ አካዳሚ አነሳሽነት ጥያቄው በፈረንጆቹ በ2010 ለዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ድርጅት የስራ አመራር ከቀረበ በኋላ የተባበሩት መንግስታት ጉዳዩን ተቀብሎ ዓለም አቀፍ የራዲዮ ቀን በየዓመቱ የካቲት 5 እንዲከበር ወስኗል።

በመሆኑም የመጀመሪያው የራዲዮ ቀን በፈረጆንቹ የካቲት 5/2011 የተከበረ ሲሆን ዘንድሮ “ሬድዮ የክፍለ ዘመን መረጃ ሰጪ፣ አዝናኝና አስተማሪ ” በሚል መሪ ሃሳብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ13ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ5ኛ ጊዜ በመከበር ላይ ይገኛል።

ሬዲዮ በኢትዮጵያ . . .

በኢትዮጵያ የያኔው የኢትዮጵያ ሬዲዮ የአሁኑ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ብሄራዊ ሬዲዮ ቀዳሚውን ሚና ሲጫወት ሬዲዮን በማስተዋወቅም ረገድ ፈር ቀዳጅ ነው።
በቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ “መልካም ፈቃድ” በ1920ዎቹ መጨረሻ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ ሬዲዮ መረጃ በቀላሉ ሊገኝ በማይችልበት በዛን ጊዜ ብቸኛ አማራጭ ሆኖ አገልግሏል።

የኢትዮጵያ ሬዲዮን ፈለግ በመከተልም ብዙ የሬዲዮ ጣቢያዎችም የተመሰረቱ ሲሆን አሁን ላይ ከ60 በላይ የተለያዩ ቋንቋዎች በአጭር፣ መካከለኛ እና ረጅም እንዲሁም በኤፍ.ኤም ሞገዶች የሚያሰራጩ ከ75 በላይ የራዲዮ ጣቢያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚገኙም መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በኢትዮጵያ ያለው የሬዲዮ ቁጥር ከ1990ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ እየተበራከተ ሲመጣ በአሁኑ ሰዓት በሃገሪቱ በተለይም በከተሞች ከሚገኙ የራዲዮ ጣቢያዎች መካከል አብዛኞቹ የኤፍ.ኤም ጣቢያዎች ናቸው። የመጀመሪያው ኤፍ.ኤም የሬዲዮ ጣቢያ ኤፍ.ኤም 97.1 ነው። የመጀመሪያው የግል የሬዲዮ ጣቢያ ሸገር ኤፍ.ኤም 102.1 ነው።

ሬዲዮ በዓለም አቀፍ ደረጃ . . .

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከዓመታት በፊት ባጣው መረጃ መሰረት በዓለም ዙሪያ ከ44 ሺህ በላይ የራዲዮ ጣያዎች እንዳሉ ጠቁሟል። በእነዚህ የራዲዮ ጣቢያዎች አማካኝነትም በዓለም ዙሪያ ያሉ ከ5 ቢሊየን በላይ ሰዎች ማለትም ከዓለም ህዝብ ከ70 በመቶ በላይ በየእለቱ ከሬዲዮን እንደሚያዳምጡም ነው መረጃው የሚጠቁመው።

መረጃው የአል አይን ነው።

08/02/2024

አዉድ ሀገር የሬድዮ ፕሮግራም

የእለተ ሐሙስ እንግዳችን አቶ መላኩ ሲማ ይሰኛሉ በቱሪዝሙ ዘርፍ እውቅ ባለሙያ ናቸው የረዥም አመት የስራ ልምድ እና ገጠመኛቸውን ያካፍሉናል መልካም ቆይታ እንዲሆንልን ልባዊ ምኞታችን ነው።T...
08/02/2024

የእለተ ሐሙስ እንግዳችን አቶ መላኩ ሲማ ይሰኛሉ በቱሪዝሙ ዘርፍ እውቅ ባለሙያ ናቸው የረዥም አመት የስራ ልምድ እና ገጠመኛቸውን ያካፍሉናል መልካም ቆይታ እንዲሆንልን ልባዊ ምኞታችን ነው።Tirta FM - ትርታ FM 96.7
አውድ ኀገር Awed Hager

Address

Addis Ababa
5133

Telephone

+251926219169

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አውድ ኀገር Awed Hager posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አውድ ኀገር Awed Hager:

Videos

Share