Kaffa Regional state

Kaffa Regional state facebook
(1)

11/11/2023

የተመዘገቡ ውጤቶችን በማጠናከር ተግዳሮቶችን ለማለፍ አመራሩን በዕውቀትና በክህሎት የመገንባት ተግባር እየተከናወነ ነዉ:-አቶ ፀጋዬ ማሞ

የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማጠናከርና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በማለፍ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አመራሩን በእውቀትና በክህሎት ማብቃት ትኩረት የተሰጠው መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ ገለፁ።

"ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ቃል 3ኛ ዙር የመንግስት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ በቦንጋ የስልጠና ማዕከል ትናንት ተጀምሯል።

በመክፈቻው ላይ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶችን ለማጠናከርና መልካቸውን እየቀያየሩ የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን ለመሻገር አቅምን መሰብሰብና አመራሩን ማብቃት ያስፈልጋል።

በተለይም የፊት አመራሩ ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመራር ክህሎትና ብቃት በማዳበር ድሎችን በማጠናከርና ዕድሎችን በተሳለጠ መንገድ ወደ ውጤት መቀየር ይጠበቃል ብለዋል።

ከዚህ ባሻገር ፈተናዎችን በብልሃት በመሻገር የዕድገት ግቦችን የሚያሳኩ እንዲሆኑ አመራሩን የማብቃት ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።

የብልፅግና ፓርቲ መንግስት ሆኖ ሀገርቱን መምራት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ያስመዘገባቸው በርካታ ውጤቶች መኖራቸውን ገልጸው በሂደቱም ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ምክንያት ያልተሳኩትን በብቃት በመፈተሽ በሃላፊነት ስሜት ለመፈጸም ስልጠናው ተደማሪ አቅም እንደሚሆን ተናግረዋል።

ሀገሪቱ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ''ከእዳ ወደ ምንዳ'' የምንሸጋገርበት እና ዴሞክራሲን የማፅናት ምዕራፍ መሆኑንም አንስተዋል።

ለዚህም በየደረጃ ያለውን አመራር አቅም በመገንባት የጋራ አረዳድ ለመያዝ የሚያስችል ስልጠና መሆኑንም ገልጸዋል።

አመራሩ በዕውቀትና በክህሎት ዳብሮ በሀገሪቱ ያሉ ፀጋዎችን አውቆ በተሟላ ሁኔታ ወደ ብልፅግና ለመቀየር ለምናደርገው እንቅስቃሴ የማጠናከር ትጋት ይጠበቃል ብለዋል።

በቦንጋ ማዕከል ከ1 ሺህ በላይ የመንግስት ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ሲሆን ሥልጠናው እስከ ህዳር 12 ቀን 2016 ዓም እንደሚሰጥም ገልጸዋል።

ሀብትና ፀጋዎችን ማመንጨትና ማስተዳደር፣ ብሔራዊ አርበኝነትና ትርክትን በአግባቡ መገንባት፣ ድሎችና ውጤቶችን ማፅናት፣ ዘላቂ ሠላምን መገንባት የሚለውን ጨምሮ በስምንት ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠናው እንደሚሰጥም ጠቁመዋል።

ለሶስተኛ ዙር መሰጠት በጀመረው ስልጠና ላይ እንደ ሀገር በ17 ማዕከላት ወደ 22 ሺህ የሚጠጉ ሰልጣኞች እየተሳተፉ መሆናቸውንም አቶ ፀጋዬ ጠቁመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፦
ፌስቡክ ገፃችንን
https://www.facebook.com/kfzgca
የቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/ahkafaZGCAffairs ይወዳጁ ይከተሉ ይቀላቀሉ።

07/11/2023
31/10/2023
25/10/2023
25/10/2023

***አነጋጋሪው ሳይንቲስት ዶክተር _ኢንጂነር***
ዶክተር ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ የካቲት 25 ቀን 1948 (እ.ኤ.አ) ከአባታቸው ከአቶ እጅጉ ሃይሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ በላይነህ በአሁኑ ደቡብ ምዕራብ በቀድሞው በከፋ ጠቅላይ ግዛት በቦንጋ ከተማ ተወለዱ ። የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቦንጋ ፣ በዋከና በጅማ ከተማ ካጠናቀቁ በኋላ በባህር ዳር በሚገኘው ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የከፍተኛ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል ። ዶክተር ቅጣው ወደ ጃፓን አገር በመሄድ በኦሳካ ዪኒቨርስቲ በቋንቋና የጃፓን ኢኮኖሚ፣በሄሮሺማ ዩንቨርስቲ የኢንደስትሪና የአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ አጥንተው ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። በኋላም አሜሪካን ሀገር ስኮላር ሺፕ አግኝተው በቢዝነስ አድሚንስትሬሽን ማስትሬታቸውን በመጨረሻም ለትምህርት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት በኤሮ-ስፔስ ምህንድስና ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል። (በልጅነታቸውም የድቁና ትምህርትን ቀስመዋል ፡፡)
ዶክተር ቅጣው በናሳ (NASA) በሲስተም መሃንዲስነትና በጠፈር ሳይንቲስትነት የሰሩ ሲሆን ከሌሎች መሃንዲሶችና ሳይንትስቶች ጋር በመተባበር ለእኛ አለም (Planet Earth) እና ለተቀሩት ፕላኔቶች የምርምር ሳይንስ (Planetary Science Research and Exploration) የሚረዱ የጠፈር መንኮራኩሮችና ሮኬቶች ፈጥረዋል ። ዶክተር ቅጣው በዚህ ከፈጣሪ በተቸሩት ታላቅ ችሎታና እውቅት ለዚህች ለምንኖርባት ዓለምና ሕዝብ ታላቅ አስተዋፅዎ አበርክትዋል ።
ከነዚህም ጥቂቱን ለመጥቀስ ለናሳ(NASA) ሁለት የኤሮ-ስፔስ መወርወሪያ ሜካኒዝም ለቦይንግ ኩባንያ ሲሙሌተር (Flight Dynamic Simulator) እና አድቫንስድ ወይንም ኔክስት ጀነሬሽን (Advance or Next Generation) በመባል የሚታወቁትን ግሎባል ፖዚሽን ሳተላይት ሲስተም(Global Positioning Satellite System) ከፈለሰፉት ውስጥ አንደኛው ሰው እሳቸው ነበሩ ዶክተር ቅጣው Trans Tech International በመባል የሚታወቀውን ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅት በመመስረት የተለያዩ ሀገሮች የቴክኖሎጂ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ በአማካሪነት አገልገለዋል ።
ዶክተር ቅጣው ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ስቴላ እጅጉ ጋር በመልካምና በደስታ ጋብቻ ተጣምረው የኖሩ ሲሆን ቢንያም ፣ ያሬድና አቢጋኤል የተባሉ የሁለት ወንዶችና የአንድ ሴት አባት ነበሩ ። ዶክተር ቅጣው እጅጉ ወደ ኦስትን ቴክሳስ ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ መጥተው ድንገት በደርሰባቸው ሕመም ምክንያት በጥር 13 ቀን 2006 (እ.ኤ.አ) በ58 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል ። ዶክተር ቅጣው እጅጉ በመልካም ባህሪያቸው የተወደዱ ፣ በትህትናቸው የተመሰገኑ ፣ በስራቸው የተደነቁ ፣ በራዕያቸው ብዙ ተከታዮችን ያፈሩ ፣ የብዙዎች ተስፋና አርዓያ እንዲሁም የሀገር ኩራት የሆኑ ታላቅ ሰው ነበሩ ።
ኢንጂነር ቅጣውን የሚወድ ላይክና ሼር ያድርግ።
═════════❁✿❁ ═════════
አንብባችሁ # ሼር አላደርግ ስትሉ # ብሞት እንኳን # የማትቀብሩኝ አይነት ስሜት ነው
Follow 👇👇👇👇👇👇
.com
://www.facebook.com/kaffatube

21/10/2023
21/10/2023
21/10/2023

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር የዕጣ ማውጣት መርሐ-ግብር ተከናውኗል
ካፋ ቡና የውድድር ቦታ ሀዋሳ ደርሶታል

21/10/2023

Call for Scholarships!
**********************
Mizan-Tepi University Staff are invited to apply for this scholarship opportunity by our university's academic and research partner, Southern Federal University (SFedU) in Russia. To apply for a quota, students must register here https://education-in-russia.com/ .Detailed information on the competition can be found at https://sfedu.ru/press-center/news/73062 .The SFedU is ready to support applicants to Master's Degree by issuing support letters for obtaining the government quota. Please keep in mind that the deadline for application is November 1, 2023.
Mizan-Tepi University
Light of the green Valley!
facebook :https://www.facebook.com/p/Mizan-Tepi-University-MTU-100067612844902/
website: www.mtu.edu.et

20/10/2023

በካፋ ዞን 40 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸው ተገለጸ
*****************
ቦንጋ፡ ጥቅምት 05/2016 ዓ.ም (የካፋ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት)

በካፋ ዞን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተኑ 58 ትምህርት ቤቶች መካከል 40ቹ አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።

በቀጣይ የተማሪዎች ዉጤት ላይ እየተስተዋለ ያለዉን ችግር ማስተካከል ሁሉም አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ መምሪያዉ ጥሪ አስተላልፏል።

በካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ የፈተና አስተዳደር ቡድን መሪ አቶ በዛብህ ገ/ሚካኤል በዞኑ በ2015 ዓ.ም በማህበራዊና ተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስክ 6ሺ 490 ተማሪዎች ለብሔራዊ ፈተና መቀመጣቸዉን ገልጸዋል።

ከእነዚህ ተማሪዎች መካከልም ከተፈጥሮ ሳይንስ 66 እና ከማህበራዊ ሳይንስ 38 በድምሩ 104 ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ የሚያስገባቸውን ዉጤት ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል።

ይህም በትምህርት ላይ ከነበሩ ተማሪዎች ቁጥር ጋር ሲነጻጸር እጅግ ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዉ አጠቃላይ ተማሪዎቻቸዉን ለፈተና ካስቀመጡ 58 ትምህርት ቤቶች መካከል 40ቹ ምንም ተማሪ እንዳላሳለፉ አብራርተዋል።

በዞኑ የ12ኛ ክፍል ትምህርት ሲሰጥባቸዉ ከነበሩ 17 መዋቅሮች መካከል ቢጣ፣ አዲዮ፣ ጨና እና ዴቻ ወረዳዎች ምንም ተማሪ አለማሳለፋቸዉንም አቶ በዛብህ ጠቁመዋል።

አሁን ላይ የተማሪዎች ዉጤት ማሽቆልቆል አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የተናገሩት ቡድን መሪዉ ችግሩን ለመፍታት በየደረጃው የሚገኙ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል ሲል የደቡብ ሬ/ቴ/ድ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፦
ፌስቡክ ገፃችንን
https://www.facebook.com/kfzgca
ይወዳጁ ይከተሉ እንዲሁም ወቅታዊ መረጃዎችን ለማገኘት
የቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/ahkafaZGCAffairs
ይቀላቀሉ።

11/10/2023
11/10/2023

መስከረም 30/2016 ዓ.ም

ለቦንጋ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ፤4ኛ እና 5ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ!

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ 3ኛ፤4ኛ እና 5ኛ ዓመት ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የትምህርት መርሃግብር ምዝገባ የሚከናወነው ጥቅምት 10-11/2016 ዓ.ም ድረስ ሲሆን ትምህርት የሚጀምረው ጥቅምት 13/2016 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን በተጠቀሰው ቀን ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ማሳሰቢያ፡-

ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞና ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን::
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

በጋራ እንችላለን!!

06/10/2023

የሐዘን መግለጫ
******************
ሚቴዩ መስከረም 25/2016 ዓ.ም
በሚዛን -ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ስራ ክፍል ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ያገለገሉት አቶ ሳሙኤል ጉመር በገጠማቸው ድንገተኛ አደጋ መስከረም 24/2016ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል ።
በአቶ ሳሙኤል ጉመር ህልፈተ-ህይወት ሚዛን -ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተሰማውን ጥልቅ የሆነ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ ፣ወዳጅ ዘመዶቹና የስራ ባልደረቦቹ በሙሉ ፈጣሪ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል ።
አቶ ሳሙኤል ጉመር ባለትዳርና የ1ሴት ልጅ አባት ነበሩ ።
ፈጣሪ ነፍሳቸው በአጸደ ገነት ያኑርልን ።
Mizan-Tepi University
Light of the green Valley!
facebook :https://www.facebook.com/p/Mizan-Tepi-University-MTU-100067612844902/
website: www.mtu.edu.et

26/09/2023
26/09/2023

ለዩኒቨርሲቲያችን የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆናችሁ መምህራን ፣አስተዳደር ሰራተኞች ፣ተማሪዎቻችን እንዲሁም ለመላው የአገራችን ሙስሊም ማህበረሰብ በሙሉ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ እንኳን ለመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል ።
Mizan-Tepi University
Light of the green Valley!
facebook :https://www.facebook.com/p/Mizan-Tepi-University-MTU-100067612844902/
website: www.mtu.edu.et

የወባ በሽታ በሞቃታማ አካባቢዎች በስፋት በሚራቡ ትንኞች የሚከሰት ከዓለማችን ገዳይ በሽታዎች በቀዳሚነት የሚሠለፍ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥም የበርካታ ወገኖችን ሕይወት በየዓመቱ እየቀጠፈ ያለ...
25/09/2023

የወባ በሽታ በሞቃታማ አካባቢዎች በስፋት በሚራቡ ትንኞች የሚከሰት ከዓለማችን ገዳይ በሽታዎች በቀዳሚነት የሚሠለፍ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥም የበርካታ ወገኖችን ሕይወት በየዓመቱ እየቀጠፈ ያለው ይህ በሽታ በተለያዩ ክፍሎች በመዛመት ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሽታው በአማራ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል መከሰቱን ተከትሎ መንግሥት የተለያዩ አሠራሮችን ዘርግቶ እየሠራ ቢሆንም ችግሩ አሁንም አልተፈታም፡፡

24/09/2023
22/09/2023

Waama tooka shageton

22/09/2023
22/09/2023
21/09/2023

ለሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ
*******************************************
ሚቴዩ መስከረም 10/2016 ዓ.ም
የዩኒቨርሲቲያችን ነባር መደበኛ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ በተመለከተ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ፊስቡክ እና በኢትዮጵያ ቴሌቪዢን (ETV) ጥሪ ሲተላለፍላችሁ ብቻ ወደ ካምፓሶቻችሁ የምትንቀሳቀሱ መሆኑን በማወቅ በትዕግሥት እንድትጠባበቁ እናሳስባለን ።
Mizan-Tepi University
Light of the green Valley!
facebook :https://www.facebook.com/p/Mizan-Tepi-University-MTU-100067612844902/
website: www.mtu.edu.et

26/12/2022

አንድ ሰኞ ቀን ከሌጎስ አንድ ሰዓት ተኩል ብቻ የሚወስደው በኦዮ ክፍለ አገር ዋና ከተማ ኦቢዳን ዳርቻ ወደ ሚገኘው ዓለም አቀፍ የሞቃት አየር ንብረት ሰብሎች እርሻ ምርምር ጣቢያ ሄድኩ፡፡ በግቢው የሚታየው የዛፍ የሳር አበባ የምርምር ሥፍራ ትምህርታዊ መግለጫ የሚሰጥበት መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲኒማ ማሳያ ሥፍራ የአስተማሪዎቹ መኖሪያ የውስጥና የውጭ የስፖርት ሜዳዎች ምግብ ቤቱ ወዘተ. የናይጄሪያን ሳይሆን፣ የአውሮፓን ወይም የአሜሪካን የዩኒቨርሲቲዎች ግቢ አስመስለውታል፡፡ ስለዚህም የአጉ ተወላጆች ግቢውን ትንሿ አሜሪካን ብለው ሰይመውታል፡፡

እኔም በሁሉም ነገር የተመቻቸ በመሆኑ አብዛኛዎችን የኅብረት ሥራ ኮርሶችን የማዘጋጀው እዛ ነው፡፡ ፕሮፌሰር ምጂንዳዲና እኔ ስድስት ወር የወሰደ ጥናት ብዙ ጉዞና ብዙ ምርምር ካደረግን በኋላ ‹‹የእርሻ ኅብረት ሥራ በናይጄሪያ›› የሚል አንድ መጽሐፍ አሳተምን፡፡ መጽሐፉን በሚመለከት ከተለያዩ ክፍለ ዓለማት የተውጣጡ ታዋቂ የእርሻ ምርምር ባለሙያዎች በአብዛኛው ከዩኒቨርሲቲ የመጡ አስተማሪዎችና ፕሮፌሰሮች የተሳተፉበት የሦስት ቀን አገር አቀፍ ስብሰባ አካሂደናል፡፡ አዳራሽና መኝታ ቤት ተከራይተን ምግብም እዚያው ከፍለን እየተመገብን ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡

ማታ እራቴን ለመብላት ምግቡን ይዤ በረንዳ ስወጣ አንድ ትልቅ ሰው በጣታቸው ወደ እኔ እያመለከቱ ወደ እሳቸው እንድሄድ ጠሩኝ፡፡ በውጭ ዓለምና በአገር ውስጥ በልዩ ልዩ ሚዲያ መልካቸውን ስለማውቀው ማን እንደሆኑ ለማወቅ ጊዜ አልወሰደብኝም፡፡

ዞር አልኩና ‹‹እኔን ነው የሚጠሩኝ?›› አልኳቸው ‹‹አዎን! አንድ ጊዜ ና››! አሉኝ ምግቤን እንደያዝኩ ወደ ተቀመጡበት ጠረጴዛ ጠጋ አልኩና ‹‹ይቅርታ የምንተዋወቅ አይመስለኝም፡፡ ማን ልበል? አልኳቸው፡፡ ‹‹እኔ ጄኔራል ኦሊሴጉን ኦቦሳንጆ የቀድሞው የናይጄሪያ ፌዴራል መንግሥት ፕሬዚዳንት ነኝ፤›› አሉኝ ፈገግ ብለው፡፡ ‹‹ክቡር ፕሬዚዳንት ከማደንቃቸው ጥቂት የአፍሪካ መሪዎች ውስጥ እርስዎ አንዱ ነዎት፡፡ ምንም እንኳን እዚህ አገር ብዙ ብቀመጥም ዛሬ በአካል ስለተገናኘን ደስታዬ የላቀ ነው›› ስላቸው እጃቸውን ዘረጉልኝና ጨበጥኳቸው፡፡ ከዚያም አብሬያቸው እንድቀመጥ ጋበዙኝ፡፡

አብራቸው የተቀመጠችው አንደኛዋ የፉላኒ ባለቤታቸው ቀላ ወፈር ያለች ከመሆኗም ባሻገር በጣም ቆንጆና ሳቂታም ናት፡፡ እሳቸውን እያየች ‹‹እኮ ጠይቀው! ›› አለቻቸው፡፡ ‹‹ቅድም ወደ እኛ እንድትመጣ የጠየቅሁህ ባለቤቴ ይህ ሰውዬ ከማሊ የመጣ ነው ስትል፣ እኔ ደግሞ ከኢትዮጵያ ነው ብዬ ስለተከራከርን ነው፡፡ ከየትኛው አገር ነህ?›› ብለው ጠየቁኝ፡፡ ‹‹እርስዎ የዓለም አቀፍ ሰው ስለሆኑ በትክክል ኢትዮጵያዊ መሆኔን አውቀውታል፤›› አልኳቸውና ‹‹ከአክብሮት ጋር ክቡርነትዎ እዚህ የእርሻ ምርምር ጣቢያ ምን ለመሥራት እንደመጡ መጠየቅ ቢፈቀድልኝ?›› ብዬ በትህትና ጠየቅኳቸው፡፡ ‹‹እኔ የገመትኩት ምናልባት ለሌላ ስብሰባ የክብር እንግዳ ሆነው ስብሰባውን ሊከፍቱ የመጡ መስሎኝ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት እዚህ አይአይቲኤ ውስጥ ስለሽንብራ ሰብል አተካከልና ምርት ኮርስ ስለሚሰጥ እሱን ለመከታተል ነው የመጣሁት፡፡ በመጭው ዓመት በብዙ ሔክታር ማሳ ላይ ሽንብራ ለማምረት ሐሳብ አለኝ፤›› አሉኝ፡፡ ጄኔራሉና የትልቁ የአፍሪካ አገር መሪ የነበሩት አዛውንት የሽንብራ ልማት ኮርስ እወስዳለሁ ሲሉኝ በጣም ገረመኝ፡፡

… ከኦቦሳንጆ ጋር ያለው ግንኙት አድጎ አንድ ወቅት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ካርተር ከኚሁ ሰው ጋር ተቀምጠው ወግ ጀመሩ፡፡ ካርተር በወሬ መሀል! ‹‹ኢትዮጵያውያን ስሞች በሙሉ ትርጉም እንዳላቸው ተነግሮኛል፡፡ ስምህን ምን አልከኝ?›› ‹‹ስሜ ጌታቸው ይባላል›› ‹‹ትርጉሙ ምን ይባላል?›› “Master of all“ እንደ ማለት ስላቸው፡፡ ‹‹እንዴ ያንተማ ጠንከር ያለ ነው›› ብለው ሁለቱም የቀድሞ ፕሬዚዳንቶች ከት ብለው ሳቁ፡፡

23/12/2022

🌀💠 የለውዝ /ኦቾሎኒ/19 የጤና በረከቶች 💠🌀

✅ ለውዝ ወይም ኦቾሎኒ ከ1,6ዐዐ ዓመት በፊት በፔሩ የተገኘ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከዛም በአሜሪካና በአውሮፓ ሀገራት ላይ ተሠራጭቶ በዓለም ታዋቂ ሆኗል፡፡ ለውዝ ከምግብነት ባሻገር ለጤናም ሰፊ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ይነገራል፡፡ እነዚህን ጠቀሜታዎች በዝርዝር አስቀምጠናል እንሆ…

1. በተለምዶ ከሚባለው ጋር በተዛመደ መልኩ በዕርግጥም ለውዝ ለተዋልዶ ስርዓት ጤንነት ተመራጭ ነው፡፡ በተለይም ከእርግዝና በፊትና በዕርግዝና ወቅት ለውዝ መመገብ በውስጡ የሚገኘው ፎሊክ አሲድ በእርግዝና ወቅት በጽንሱ ዕድገት ላይ ሊያጋጥም የሚችለውን ችግር 70 በመቶ ያህል ያስወግዳል፡፡

2. በደም ውስጥ ያለውን የስኳር መጠን ያስተካክላል – በለውዝ ውስጥ በከፍተኛ መጠን የሚገኘው ማንጋኒዝ ለስብና ለካርቦሀይድሬት መፈጨት፣ ለካልሲየም በሰውነታችን ህዋሳት መዋሀድና በደም ውስጥ ያለው የስኳር መጠን የተስተካከለ እንዲሆን ያስችላል፡፡

3. በሰውነታችን ውስጥ የሚገኘው ጥሩው ኮልስትሮል እንዲጨምርና መጥፎው የኮልስትሮል ዓይነት ደግሞ እንዲቀንስ ያደርጋል፡፡ በለውዝ ውስጥ የሚገኘው የመዳብ ማዕድን ሰውነታችን በልብ ህመም እንዳይጠቃ ይከላከላል፡፡

4. የሐሞት ጠጠር እንዳይከሰትና የሐሞት ከረጢት ጤናን ያስጠብቃል፡፡

5. ድብርትን ይከላከላል፡፡

6. የማስታወስ ችሎታን ይጨምራል፡፡

7. የልብ ህመም፣ ካንሰርን፣ የነርቭ ህመሞችን እንዲሁም ከቫይረስና ከፈንገስ ጋር ተያያዥነት ያላቸው በሽታዎችን ይከላከላል፡፡

8. የአእምሮ ብቃትን ከመጨመርም በተጨማሪ እንደ ፓርኪንሰንና አልዛይመር ዓይነት በሽታዎች እንዳይከሰቱ
ይረዳል፡፡

9. በካንሰር መጠቃትን ይቀንሳል፡፡

10. ሐይል ሰጪ ከመሆኑም በላይ ጥቂት በልተው ለረጅም ሰዓታት እንዳይርቦት ስለሚያደርግ የሰውነት ክብደትን ለመቀነስ ይረዳል፡፡

11. በእርግዝና ወቅት ለውዝ መመገብ የሚወለዱ ህጻናት እንደ አስም በመሳሰሉት በሽታዎች እንዳይጠቁ ያደርጋል፡፡

12. ለታዳጊዎች የአካል ግንባታ ለውዝ እጅጉን ተመራጭ ነው፡፡

13. በሰውነታችን ውስጥ ያሉ የተለያዩ መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ያስወግዳል፡፡

14. የጸጉር ስሮችን በማጠንከር ለጸጉር ጤንነት ተመራጭነው፡፡

15. ስትሮክ የሚሰኘውን ወደ አንጎል በሚሄደው የደም ፍሰት መዛባት ሳቢያ የሚከሰተውን የአንጎል ላይ አደጋ ይከላከላል።

16. ፍሪ ራዲካል በተሰኙት ሞሎክዩሎች ሳቢያ በሰውነት ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ይቀንሳል።

17. እብጠትና ሌሎችን ከቆዳ ጋር የተያያዙ ህመሞችን ይከላከላል። ቆዳን ከውስጥ በማለስለስ የተለያዩ የቆዳ ችግሮችን ይከላከላል።

18. ለውዝ በተለያዩ የቫይታሚን ዓይነቶች የበለጸገ ነው።

19. ለውዝ በፖታሲየም፣ ማንጋኒዝ፣ መዳብ፣ ካልሲየም፣ ማግኒዚየም፣ ብረት፣ ሴሬኒየም እና ዚንክ በመሳሰሉት ማዕድናት የበለጸገ ነው። ቡናን መጠጣት ከጤና አኳያ
ያለው ጠቀሜታ፡-
– የማስታወስ አቅምን ይጨምራል
– ድብርትን ያስወግዳል
– ለራስ ምታት እና አስም ፍቱን ነው
– በኩላሊት ጠጠር እንዳንጠቃ ይከላከላል
– ጉበታችን እንዳይታወክ ይከላከልልናል
– በሰውነታችን ላይ በስራ ብዛት የሚፈጠሩ ህመሞች እንዳንጠቃ ይረዳል
– ለድንገተኛ ሞት የሚያበቃ የልብ በሽታ እንዳንጠቃ ይጠብቃል
– በስኳር በሽታ ከመያዝ ይከላከላል
– በነቀርሳ በሽታ እንዳንያዝ ይረዳል


ሼርርርር

21/12/2022
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን አመራሮች አግኝተው የከተማውን የ2014 በጀት ዓመት እና የ2015 ሩብ ዓመት አፈጻጸም ገምግመዋል።አዲስ አበባ (ኢዜአ) ታህሳ...
20/12/2022

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን አመራሮች አግኝተው የከተማውን የ2014 በጀት ዓመት እና የ2015 ሩብ ዓመት አፈጻጸም ገምግመዋል።

አዲስ አበባ (ኢዜአ) ታህሳስ 11/2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን አመራሮች አግኝተው የከተማውን የ2014 በጀት ዓመት እና የ2015 ሩብ ዓመት አፈጻጸም ገምግመዋል።

ከተወሰኑ ወራት በፊትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር አመራሮችን ሰብስበው ነበር።

በስብሰባውም ለቀጣይ 100 ቀናት ዕቅድ ተግባራዊ የሚደረጉ ጉዳዮችን አቅጣጫ ማስቀመጣቸው ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በድጋሚ ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው የመስተዳድሩን አመራሮች አግኝተው የከተማውን የ2014 በጀት ዓመት እና የ2015 ሩብ ዓመት አፈጻጸም ገምግመዋል።

በመጨረሻም በከተማዋ የተጀመሩ መልካም የልማት ሥራዎችን እንዲስፋፉ፤ ችግሮችም እንዲስተካከሉ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

በኳታር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ አገር ሞሮኮ ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ከክሮሺያ ጋር ዛሬ ከምሽቱ 12 ሰአት በከሊፋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ጨ...
17/12/2022

በኳታር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 22ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ አገር ሞሮኮ ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ከክሮሺያ ጋር ዛሬ ከምሽቱ 12 ሰአት በከሊፋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ጨዋታዋን ታደርጋለች።

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ሕዳር 14 ቀን 2015 ዓ.ም አል በይት ስታዲየም በምድብ ስድስት ሞሮኮ ከክሮሺያ ያደረጉት የምድብ ጨዋታ ያለ ምንም ግብ አቻ መጠናቀቁ የሚታወስ ነው።

ታሪክ ሰሪዋ ሞሮኮ በግማሽ ፍጻሜ በወቅቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ፈረንሳይ 2 ለ 0 እንዲሁም ክሮሺያ በአርጀንቲና 3 ለ 0 ተሸንፈው ነው ለዛሬው የደረጃ ጨዋታ የበቁት።

የአትላስ አንበሶች ለዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የመድረስ ሕልማቸው ባይሳካም በውድድሩ ያሳዩት ተጋድሎ ለአፍሪካ ኩራት ለዓለምም ግርምት ነበር።

የሞሮኮ ታሪክ ሰሪው አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉዊ “በግማሽ ፍጻሜው ብንሸነፍም በዓለም ዋንጫው ካሳየነው ብቃት አንጻር ከሀዘን ይልቅ የተሰማን ኩራት እና ክብር ነው” ሲሉ ከግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በኋላ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

አሰልጣኙ ክሮሺያን አሸንፈን ሶስተኛ ደረጃ በመያዝ በዓለም ዋንጫው ምርጡ የአፍሪካ ብሔራዊ ቡድን መባል እንፈልጋለን ብሏል።

የአትላስ አንበሶች ለፍጻሜ ባይደርሱም የዓለም ዋንጫው አስደናቂ ብሄራዊ ቡድን መሆናቸውን ለማስመስከር እና አዲስ ታሪክ ማስመዝገብ የሚያስችል አጋጣሚ ከፊታቸው አለ።

የአትላንስ አንበሶች ክሮሺያን ካሸነፉ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀች የመጀመሪያ አፍሪካዊት አገር በመሆን ሌላ ታሪክ መስራት ትችላለች።

የ35 ዓመቱ ኳታራዊ ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ዳኛ አብዱልራህማን አል-ጃሲም የሁለቱን አገራት ጨዋታ በመሐል ዳኝነት ይመሩታል።

Address

Kaffa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kaffa Regional state posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Category