Kaffa Regional state

Kaffa Regional state facebook

02/01/2025

, Kafa, Ethiopia - The origin of coffee❗️

Ethiopia is the world's fifth largest producer of coffee, and Africa's top producer, with 496,200 tonnes in 2022, and renowned for its high-quality coffee.

Many Large/Small-scale farmers cultivate coffee as a cash crop. According to the International Coffee Organization, Ethiopia has over 4 million small-scale coffee farmers.

Half of the coffee is consumed by Ethiopians, and the country leads the continent in domestic consumption.

23/12/2024
19/12/2024
ወቅታዊው የወባ ወረርሽኝ ይዞታኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የወባ ወረርሽኝ እየተባባሰ የብርካቶችንም ሕይወት እየቀጠፈ እንደሚገኝ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚደርሱን ዘገባዎች ያመ...
07/11/2024

ወቅታዊው የወባ ወረርሽኝ ይዞታ

ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የወባ ወረርሽኝ እየተባባሰ የብርካቶችንም ሕይወት እየቀጠፈ እንደሚገኝ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚደርሱን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ባሳለፍነው ሳምንት ሐሙስ ዕለት የዓለም የጤና ድርጅት ይፋ ባደረገው ዘገባም ሀገሪቱ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከከፋ የወባ ወረርሽኝ ጋር እየታገለች መሆኗን አመልክቷል። የድርጅቱ መረጃ እንደሚያመለክተው ካለፈው ዓመት ጥር ወር አንስቶ እስከያዝነው ጥቅምት 10 ቀን ድረስ በወባ በሽታ ከ7,3 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ተይዟል። 1157ቱ ደግሞ ሕይወታቸውን አጥተዋል። በአሁኑ ጊዜ 75 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ግዛት በወባ ወረርሽኝ የተመቻቸ መሆኑንም በጤናው ረገድ ከፍተኛ ተግዳሮት እንዳስከተለም ተገልጿል። በእነዚህ አካባቢም 65 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ ለወባ የተጋለጠ ሲሆን በተለይ ሕጻናት ለከፋ ጉዳት እየተዳረጉ መሆኑንም የዓለም የጤና ድርጅት አመልክቷል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ የውስጥ ደዌ እና ተላላፊ በሽታዎች ተመራማሪ እና ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ወንድወሰን አሞኘየወባ በሽታ የዝናብ ወቅት ሲያበቃ እንደሚመከሰት በማመልከት አሁን ወቅቱ እንደሆነ ነው ያስታወሱት።

የወባ ወረርሽኝ የተባባሰበት ምክንያት

የዓለም የጤና ድርጅት አሁን ለሚታየው የወባ ወረርሽኝ መባባስ አኖፖሊስ ስቴፋኒስ የተሰኘች አዲስ የወባ ትንኝ መስፋፋትን፤ ድርቅን፤ የምግብ ዋስትና አለመኖርን፤ የአየር ንብረት ለውጥን፤ እንዲሁም በሀገሪቱ የቀጠለውን ግጭት ጦርነት በምክንያትነት ገልጿል። ዶክተር ወንድወሰንም ይህን ይጋራሉ።

ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ የወባ በሽታን ስርጭት ለመቆጣጠር ትርጉም ያላቸው ተግባርት እየተከናወኑ ውጤት እየታዩባቸው ዓመታት የቅርብ ጊዜ ትዝታዎች ናቸው። ባደረጉት ጥረት ስኬት ያስመዘገቡ አካባቢዎችም በአርአያነት ይነገርላቸው ነበር። አሁን ግን በተለይ በኦሮሚያ ክልል፤ በአማራ ክልል፤ በምዕራብ፣ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ስርጭቱ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን፤ በወባ የሚያዙ ብቻ ሳይሆን የሚሞቱትም ቁጥር ከፍ እያለ መሆዱ እየተነገረ ነው። ከዚህ ቀደም ወባን ስለማጥፋት ይነገር የነበረው ዛሬ ወደኋላ ተመልሶ ካሉት ተደራራቢ ችግሮች ጎን ለጎን ወባ ዋነኛ የጤና ስጋት ሆናለች።

ያሉ ተግዳሮቶች

የዓለም የጤና ድርጅት በዘገባው እንዳመለከተው የወባ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት መኖሩን፤ በተለይ ደግሞ ግጭት ጦርነት በጠናባቸው አካባቢዎች የጤና ተቋማት በመጎዳታቸው ተገቢው የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ፈተና ሆኗል። የውስጥ ደዌ እና ተላላፊ በሽታዎች ተመራማሪ እና ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶክተር ወንድወሰንም እንዲሁ አንድም ለመከላከል የሚሠሩ ሥራዎች እንደቀድሞው መሠራት ያልተቻለበት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል፤ የወባ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል የሚያስፈልጉ ግብአቶች በበቂ ሁኔታ አልቀረቡ ከሆነ፤ አዲስ የወባ ዝርያ መምጣቱና መድኃኒት መቋቋም መቻሉና የመሳሰሉት ምክንያቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ በሳይንሳዊ አጠራሩ ፋልሲፈረም እና ቫይቫክስ የተሰኙት ናቸው የወባ አይነቶቹ። ፋልሲፈረም በብዛት የሰዎችን ሕይወት የምትቀጥፈው ስትሆን በብዛት የምትከሰተው ደግሞ ቫይቫክስ የተሰኘችው መሆኗን ነው ባለሙያው የገለጹልን። ሆኖም ፋልሲፈረም በፈጣን የደም ምርመራው ሂደት ወዲያው ይገኝ የነበረውን ምልክት አጠፋች። ሆኖም ግን መስተካከሉና የምትደብቀውን የሚያጋልጥ የመመርመሪያ ስልት መኖሩን እና ያንንም ለማዳረስ መሞከሩንም አስረድተዋል።

ጀነራል አስራት ዶንዬሮ በካፋ ህዝቦች የዘመን መለወጫ (ማሽቃሬ) ባሮ ተገኝተዋል እናመሠግናለን ።
24/09/2024

ጀነራል አስራት ዶንዬሮ በካፋ ህዝቦች የዘመን መለወጫ (ማሽቃሬ) ባሮ ተገኝተዋል እናመሠግናለን ።

22/09/2024

አዳነ ሙሉጌታ እባላለሁ። እ.ኢ.አ በ2009 ዓ/ም ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቄያለሁ። በሙያዬ የባንክ ቤት ሰራተኛ ነኝ። ከባንክ ቤት ስራዬ በተጨማሪ በግሌ "ከጀማሪ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ያሉ ነጋዴ የማህበረ ሰብ ክፍሎችን ከመሠረታዊ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ያሉ የንግድ ስራ ሙያ (Business) ስልጠናዎችን አሰለጥናለሁ፥ አማክራለሁ።"

በሒሳብ እና ንግድ (Business) ስራ ሙያዎች የማማክራቸዉ ደንበኞቼን ሁሌም አደራ ስል የምመክራቸው "የገበያ ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ሲሉ ማስታወቂያም ሆነ ሌሎች ገበያ ነክ ጉዳዮችን ሲያስቡ በተመሳሳይ ተቃዉሞች ምክንያት ኪሳራ አልፎም እጃቸውን አራግፈው ከገበያው ጨርሰው እንዳይወጡ
በቅድሚያ ስለ ደንበኞቻቸዉ እምነት እና ባህል በጥልቀት ማወቅ፣ ሲቀጥል ምን አይነት ምርት እና አገልግሎት ከእምነታቸው እና ከባህላቸው ጋር ተጣጥሞ ይሄዳል? ብለው ስለ ደንበኞቻቸዉ ማሰብ እንዳለባቸው እመክራለሁ።"

በሐይማኖቴም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ነኝ። እንደ እምነቱ ተከታይ ብቻም ሳይሆን እንደ ተማርኩት ትምህርት አስተምህሮት (Principle) እንዲሁም እንደ አለም አቀፉ የንግድ ማስታወቂያ ህግ (International Media Law) #የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ አምራች ለዘመናት የሠማዕቱን ምስል እና ስያሜ በተመለከተ ሲያደርግ የነበረዉን ድርጊት ከአስር አመት በፊት ጀምሬ ተቃዉሞዬን ሳሰማ ቆይቻለሁ። ነገር ግን ተቃዉሞዬ በወቅቱ ቢራዉ ላይ ሆነ ድርጅቱ ላይ ቀጥተኛ ለዉጥ ባያመጣም ቢራዉን ግን በግሌ አልጠጣም። ምርቱን ባለመጠቀም መቃወምም ይቻላል። ፈረንጆች እንዲህ አይነቱን ቀዝቃዛዉ ጦርነት ይሉታል። ምክንያቱም በተዘዋዋሪ ምርቱን አለመጠቀሜ በጅርጅቱ ላይ በሂደትም ቢሆን ተዘዋዋሪ አሉታዊ ጫና ማሳደሩ ሚስጥሩ ግልፅ ነዉ።

በወቅቱም ተቃዉሞ መነሳቱን፣ ጉዳዩም ለብፁዕ አቡነ ጳዉሎስ መድረሱን በመጨረሻም ምስሉ ላይ ማሻሻያ እንደተደረገበት ይወራ እንደነበር አስታዉሳለሁ።

ቢ.ጂ.አይ ራሱን ከዉድቀት ለመታደግ ሲል "ለዘመናት ደሀ ስረዳ ኖሬአለዉ፣ የታመመ አሳክሜአለዉ፣ አጠቃላይ ማህበራዊ ሀላፊነቴን ተወጥቻለዉ የሚል "ፋሽኑ ያለፈበት" ገበያ ተኮር እሳቤዉን ወደ ጎን ትቶ አሁን ላይ ዘመኑ የሚያስፈልገዉ ስልጡን እና የበቃ የገበያ ጥናት ባለሙያ (Marketing) በማፍራት የመጣበትን ቀዉስ የ Crisis Management and response እንዴት ተግባራዊ ላድርግ እና ቀዉሱን እንዴት ልቆጣጠረዉ? ማለት ይኖርበታል።

ኦርቶዶክስ ሀገር ናት፥ ተቃዉሞዉም ሀገራዊ ነዉ። ከሠሞኑን በቢ.ጂ.አይ የተነሳዉ ሀገራዊ ተቃዉሞ የድርጅቱን ሽያጭ ከፍተኛ በሚያስብል ደረጃ እንደሚጎዳዉ መገመት የሚከብድ አይመስለኝም። እንደ ቢ.ጂ.አይ በአለማችን በተለያዩ ምርቶች ላይ የእምነት እና ባህል ተኮር ተቃዉሞ ተነስቶ ያዉቃል። ዳሩ ግን ለነገሩ ተገቢዉን እና አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ስማቸዉን ከውድቀቱ ታድገዋል።

ለምሳሌ ያህል፦
#1. NIKE & Muslim. እ.ኤ.አ በ1997 ናይክ ባመረተዉ ጫማ ዲዛይን ላይ "Allah" የሚል ትርጓሜን ይመሳሰላል በሚል በመላዉ አለም ያሉ የእስላምና ተከታዮች ተቃዉሞ አስነስተዉ በፍጥነት በይቅርታ እንዲነሳ ተደርጓል።

#2 RED BULL & CATHOLIC: ሬድ ቡል የምርቱን የማበረታታት አቅም ለመግለፅ እየሱስን ተመሳሳይ ምስል በባህር ላይ ሲያቋርጡ የሰራዉ ማስታወቂያ በብራዚል ካቶሊክ ከፍተኛ ተቃዉሞ ገጥሞት ወዲያዉ በይቅርታ ተመልሷል።

#3. Dolce and Gabbana & China. እ.ኤ.አ በ2018 አንዲት ቻይናዊት የጣልያንን ምግብ በ ቾፕስቲክ ለመብላት ስትቸገር የተለቀቀዉ ማስታወቂያ ቻይናዉያን ባህሌን ማንቋሸሽ በሚል ትልቅ ተቃዉሞ አሰምተዉ D&G በፍጥነት ይቅርታ ጠይቋል፣ ማስታወቂያዉን አዉርዷል።

#4. Unilever and HINDU ዩኒሊቨር Magnum በተባለዉ የአይስክሬም ማሸጊያ ላይ የተጠቀሙት ምስል ሂንዱ አምልኮ ምስል አይነት (image of Hindu deity) ተመሳሳይ ነዉ በሚል በህንድ የሂንዱ አማኞች የመጣበትን ተቃዉም እንዲሁ በግዜ ፈትቷል።

27/08/2024

ብቻውን #ህዝብ ነው !🤟
እሱ #ንጉስ ነው 🤴።
ካፋነት ይለምልም 💪💞

20/08/2024
10/08/2024

Happy follow-versary to my awesome followers. Thanks for all your support! Teshager Assefa, Matiwos Ango, Wude Wude

The great picture
25/07/2024

The great picture

25/07/2024

Address

Bonga
Kefa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kaffa Regional state posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Category